Get Mystery Box with random crypto!

ዘማሪ ዲ/ን ፍፁም ከበደ

የቴሌግራም ቻናል አርማ zdfitsumkebe — ዘማሪ ዲ/ን ፍፁም ከበደ
የቴሌግራም ቻናል አርማ zdfitsumkebe — ዘማሪ ዲ/ን ፍፁም ከበደ
የሰርጥ አድራሻ: @zdfitsumkebe
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 22.71K
የሰርጥ መግለጫ

ዘማሪ ዲያቆን ፍፁም ከበደ

Ratings & Reviews

5.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 20

2022-10-07 22:53:14 +++ "ያልተሞቁ ትንንሽ ፀሐዮች" +++

ሕፃናት በአካል መጠን አንሰው ቢታዩም በልባችን ውስጥ የሚይዙት ስፍራ ግን እጅግ በጣም ሰፊ ነው፡፡ ቃል ከአፋቸው ሳያወጡ በፊታቸው ብቻ በሚያሳዩን ፈገግታ ሕይወታችን ላይ ደስታን መዝራት ይችላሉ፡፡ ከዓይናቸው የምትወርደው አንዲት የእንባ ዘለላ ደግሞ ስሜታችንን በኃዘን ምስቅልቅሉን የማውጣት ኃይል አላት፡፡ ሕፃናት ለዚህች ቀዝቃዛ ዓለም የተሰጡ ፀሐዮች ናቸው፡፡ ታዲያ እነዚህ ትንንሽ ፀሐዮች ገና ከመውጣታቸው ብዙም ሳንሞቃቸው መልሰው ሊጠልቁ፣ የልጅነት ቡረቃዎቻቸውን ሳንጠግብ ፈጥነው ሊያንቀላፉ ይችላሉ፡፡ ይህ ሲሆን ኃዘኑ ከባድ ነው፡፡ 

ከአዋቂ ይልቅ የሕፃን ልጅ ሞት ኃዘን ይጠብቃል። በቤተሰብ ውስጥ ከሁሉም መጨረሻ ይሞታል ተብሎ የሚጠበቀው የቤቱ ሕፃን በመሆኑ ልጁ ከወላጆቹ ቀድሞ ሲሞት እጅግ አስደንጋጭ ይሆናል። ወላጆቹ ከልጃቸው ጋር በነበራቸው ያለፈ ግንኙነት ብቻ ሳይሆን፣ እርሱ ላይ የጣሉት የወደ ፊት ተስፋና ሕልማቸው ሁሉ ከንቱ እንደ ቀረ አስበው አንጀታቸው በኃዘን እሳት ይነዳል፡፡ በተለይ ሟቹ ሕፃን ለወላጆቹ አንድ ወይም ብቸኛ ከሆነ በቤተሰቡ ላይ የሚደርስባቸው የኃዘን ስብራት በቃል የማይገለጽ ጥልቅ ነው። ከአገኛቸውም የውስጥ ሕመም እና የልብ መታወክ የተነሣ ቶሎ ለመጽናናት ይቸገራሉ። ከአብራካቸው ወጥቶ ወደዚህ ዓለም የመጣው ሕፃን እንደ ሌሎቹ ሰዎች ሟች እንደ ሆነ ቢያውቁም እንኳን ሞቱ ግን ጨርሶ የማይታመን ይሆንባቸዋል፡፡

በወዳጁ በአልዓዛር ሞት መንፈሱ ታውኮ ያለቀሰ የክርስቶስ አካሉ የሆነችው ቤተ ክርስቲያን ይህ ዓይነቱ ኃዘን ለገጠማቸው ቤተሰብ "አታልቅሱ" ብላ አታስተምርም። ለሰውነት የማይስማማውን ሕግ ጠብቁ ብላ በልጆቿ ላይ ጨካኝ አትሆንባቸውም። የቤተ ክርስቲያን መምህር የሆነው ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ በአንድ ወቅት :- "በልጆቻችሁ ሞት አታልቅሱ ብዬ አላስተማርኩም። እንደዚህ ተናግሬ እንደሆን የማይቻለውን ነገር እላለሁ። እኔ ልክ እንደ እናንተ ከአንዲት እናት የተወለድኩ መዋቲ ፍጥረት ነኝ። ባሕሪያችሁንም ስለምጋራ በሰው ያለውን ስቃይ እረዳለሁ። የአባቶችን ኃዘን የእናቶችን ማቃሰት አያለሁ። ... በሕሊናቸውም የልጃቸውን ልማዶች፣ የሰውነት እንቅስቃሴዎቹን እና ንግግሮቹን እያስታወሱ እንዴት እንደሚሆኑ አውቃለሁ" ሲል ተናግሮ ነበር።

ምንም ሕፃናትን በሥጋ የማጣት ሕመሙ ከባድ ቢሆንም ወላጆቻቸው ግን ‹‹ተስፋ እንደ ሌላቸው እንደ ሌሎች ደግሞ›› ኃዘን እንዲያበዙ አይፈቀድላቸውም።(1ኛ ተሰ 4፥13) ልጆቻቸው ከዚህ ዓለም ወደ ተሻለው ዘላለማዊ ቤት እንደ ሄዱ በማመን መጽናናት አለባቸው። የሞቱት ልጆቻቸውን መቃብር ሰውራ አታስቀራቸውም። በሰማይም አቀባበል ይደረግላቸዋል። ብዙ ጊዜ ልጆቻቸው በትምህርትም ሆነ በሌሎች ጉዳዮች ከአጠገባቸው ሲርቁ ትልቁ የወላጆች ጭንቀት ባይመቻቸውስ፣ ቢጎሰቁሉስ፣ ፊት ቢነሷቸውስ፣ ክፉ ነገር ቢያገኛቸውስ ... የሚሉት ናቸው። ይሁን እንጂ ከዚህ ዓለም አንቀላፍተው ወደ አምላካቸው ስለ ሄዱት ሕፃናት ግን እንዲህ ብለው ሊያስቡ አይችሉም፡፡ ምክንያቱም ልጆቻቸው ርቀው የሄዱት አመሉን በየሰከንዱ እየቀያየረ ከሚያስቸግር እንግዳ ሰው ዘንድ ሳይሆን፣ በጎነቱ ተሰፍሮ የማያልቅ ቸርነቱ የማይለወጥ ፈጣሪያቸው ጋር ነው። ከእርሱ ጋር ሆነው ማን ያስፈራቸዋል? ማንስ ያስደነግጣቸዋል?!

ሕፃናት የሞቱባቸው ወላጆች ከሚጸጸቱባቸው ምክንያቶች ውስጥ ‹ያለ ጊዜው› መሞታቸውና ልጆቻቸውን አድገው አለማየታቸው ነው፡፡ ይሁን እንጂ የሰውን ሁሉ የዕድሜ ዝርዝር ሰንጠረዥ በእጅ የጨበጡ ይመስል ‹ያለ ጊዜው ነው› እያሉ በድፍረት መናገር አግባብ አይደለም፡፡ እግዚአብሔር ያለ ጊዜው የሚያደርገው ሕይወትም ሞትም የለም፡፡ ነገሩ እኛ በምናስበው ጊዜ ስላልሆነ ‹ያለ ጊዜው›/‹ያልጠበቅነው ነው› ብለን እየተናገርን ካልሆነ በቀር፣ ለእርሱ ሁሉን የሚያከናውንበት ‹‹የሥራ ጊዜ አለው››፡፡(መዝ 119፡126)

"አድጎ ሳላየው" ስለሚለው ጸጸትም፣ እውነት ነው የሕፃናትን እድገት ማየት ደስ ያሰኛል፡፡ ነገር ግን ዋናው ቁም ነገር የልጁ ማደግ ሳይሆን አድጎ የሚኖረው ሰብእና ነው፡፡ የዛሬው ንጹሕ ሕፃን ነገ ሲጎለምስ ቀማኛ እና ደም አፍሳሽ ከሆነ ማደጉ የሚያስቆጭ ይሆናል፡፡ ዛሬ በሕይወት ያሉ ሕፃናት ነገ አድገው ምን ዓይነት ሰዎች እንደሚሆኑ ገና አልታወቀም። "ልጄ በዚሁ በጎነቱ ይቀጥል ይሆን? ወይስ ነገ ከአጉል ሰዎች ጋር ገጥሞ ክፋት ያስተምሩብኝ ይሆን?" የሚለው የብዙ ወላጆች የየቀን ሐሳብ ነው። ሕፃን ልጁ የሞተበት ወላጅ ግን ስለዚህ ነገር አይጨነቅም። የተፈጥሮ ንጽሕናውን ሳያጣ ክፋትን የሚጸየፉ የቅዱሳን ማኅበር ካሉበት፣ የጨለማ ወሬ ከማይወራበት ሰማያዊ እልፍኝ አንድ ጊዜ ገብቶለታልና።

በሕፃናት ልጆች ሞት ከመጠን በላይ ማዘንና በፈጣሪ ላይ መቆጣትን ቅዱሳን አበው በጽኑዕ ያወግዛሉ። በተለይ ቅዱስ ዮሐንስ አፈርቅ በፈጣሪ ላይ የሚደረገው ማጉረምረም "ትልቅ ኃጢአት" እንደ ሆነ ይገልጻል። ድርጊቱም የአምላክን ሥራ ፍጹምነት አለመቀበል በመሆኑ ፈጣሪን ከመስደብ አይተናነስም ይለናል።

ሰባት ወንዶች እንዲሁም ሦስት ሴቶች ልጆቹን በቅጽበት ሲያጣ ፈጣሪውን ያላማረረ ጻድቁ ኢዮብን እስኪ ለአፍታ እናስበው፡፡ ልጆቻቸውን ያጡ ወይም የሚያጡ ብዙ ወላጆች ልጆቹ ከመሞታቸው በፊት የመጨረሻ ቃላቸውን የመስማት፣ እጆቻቸውን የማሻሸትና ጥልቅ በሆነ ቤተሰባዊ ፍቅር የመሳም፣ ከሞቱም በኋላ እንደ ሥርዓቱ ዓይኖቻቸውን የመክደን እና አስከሬናቸውን አጥቦ የመገነዝ እድል አላቸው። ጻድቁ ኢዮብ ግን ከእነዚህ ውስጥ አንዱን እንኳን አላገኘም። ልጆቹ በታላቅ ወንድማቸው ቤት ሲበሉና ሲጠጡ ድንገት ዐውሎ ነፋስ ተነሥቶ ቤቱን ደርምሶ ስለ ገደላቸው እነርሱን ተንከባክቦ የማስታመም እድል አላገኘም። ነፍሳቸውም በወጣችበት ደቂቃ ዓይኖቻቸውን አልከደነም፡፡ የሞቱት ድንጋይ ተጭኗቸው ስለሆነና አስከሬናቸውን ለማውጣት በሚደረገው ቁፋሮ ወቅት አንዳንዶቹ ሕዋሳቶቻቸው በጣም ስለሚጎዱ ሙሉ አካላቸውን የመቅበሩ ነገር ያጠራጥራል፡፡ ታዲያ እነዚህ ሁሉ መከራዎች በአንድ ጊዜ ቢደራረቡበትም ጻድቁ ኢዮብ ግን ‹‹እግዚአብሔርን አልሰደበም፣ መላእክትን አልረገመም››። ይልቅ ወደ ምድር ሰግዶ ‹‹እግዚአብሔር ሰጠ፣ እግዚአብሔርም ነሣ፤ የእግዚአብሔር ስም የተባረከ ይሁን›› ብሎ አምላኩን አመሰገነ። ትንሣኤ ባልተሰበከበት፣ የሰው ተስፋ በቀጨጨበት፣ ሞት ጥላውን ባጠላበት በኦሪት ዘመን የነበረ ኢዮብ እነዚያን ሁሉ ልጆች በአንድ ጊዜ አጥቶ እንዲህ ካመሰገነ፣ ስለ ትንሣኤው የተማርንና "የሙታንን መነሣት ተስፉ እናደርጋለን" ብለን የምንጸልይ፣ የኢዮብን ሩብ ያህል እንኳን መከራ ያልደረሰብን እኛ የሐዲስ ኪዳን ምእመናን ምን ያህል አመስጋኞች ልንሆን በተገባን?

ልጆቻቸው በለጋነት እድሜያቸው የሞቱባቸው ወላጆች ‹‹ልጅህን ሠዋልኝ›› ተብሎ ሲጠየቅ ፈጣሪው ላይ ያላጉረመረመ አብርሃምን ሊያስቡ ይገባቸዋል። የገዛ ልጁን በገዛ እጁ መሥዋዕት አድርጎ እንዲያቀርብለት የተጠየቀው አብርሃም በፈጣሪው ላይ አልተቆጣም። "አባት ያደረከኝ የልጄ ገዳይ እንድሆን ነውን? ከዚህ ሁሉ ባትሰጠኝ በተሻለ ነበር" አላለም። "ከይስሐቅ በሚወለዱት ልጆች ዘርህን አበዛለሁ ብለኸኝ አልነበር። ታዲያ ዛፉን ነቅለህ እንዴት ፍሬውን ልትሰጥ ትችላለህ?" እያለም ፈጣሪውን አልተፈታተነም። አብርሃም ልጁ ይስሐቅን የመሥዋዕት እንጨት አሸክሞት ሲሄድ፣ ‹‹የመሥዋዕቱ በግ ግን
247 viewsወሰንየለው ባህሩ, 19:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-07 17:20:33 ንጻሬ ታሪክ2

ታሪክ ዳቦ ላይሆን ለምን ትተርካላችሁ?ለሚሉ ያሉኝ ጥያቄዎች፡፡
እኛ ኦርቶዶክሳውያን ታሪክን የምንረዳው መሠረተ ፍኖት ስለሆነ ነው እንጂ በዳቦ ልክ አናይም ፡፡ ያማ ቢሆን እንደ ዔሳው በመብል በቀየርነው ነበር፡፡
ታሪክ ትናንት ነው ግን ያላለፈ ዛሬም ነው፡፡ በእኛ እና በአባቶቻችን መካከል ዘመን እንጂ ልዩነት የለም የጴጥሮስ ሕይወት ሕይወታችን ነውና፡፡ታሪክ የልለው ሰው ከመሆን በላይ ምን ጨለማ ይኖራል?
ትናንት አንድ ዓይናችን ከዛሬ ጋራ ሲጨመር ደግሞ ሁለት ዓይናችን ነው፡፡ለነገ ስናስብ ሥስተኛ ዓይን ይኖረናል ማለት ነው፡፡
ታሪክ ከህሊና ቀውስ እና ከልቡና መንሸራተት ያድናል፡፡
አቡነ ዮሐንስ እንዳሉት ፦ የሞላ ታሪካችንን በጎደለ ሆዳችን አንቀይረውም፡፡ለመሆኑ፦
1 በዓለም ዓቀፍ ደረጃ በባህል እና ቅርስ ታሪክ ዙሪያ እንደ ባህል ሚኒስተር ባለው ተቅዋም ተቀጥረው ዳቦ የሚያገኙ ስንት ናቸው?
በሀገራችንስ?ከፊድራል እስከ ቀበሌ በባህል ወስጥ ዳቦ የሚያገኙ ስንት ናቸው?
2በዓለም ዐቀፍ ታሪክ ለመጎብኘት የሚንቀሳቀሱ የዓለም ህዝቦች ስንት ናቸው? በሀገራችንስ? እነሱን ለማስጎብኘት የተቀጠሩ ስንት ናቸው?
3 በተለያዩ የትምህርት ተቅዋማት የታሪክ መምህር ሁነው ዳቦ የሚያገኙ ስንት ናቸው?
4በተለያየ ቅርጽ አይነት በታሪክ ዙሪያ ላይ ጥናት የሚሠሩ እና መጽሐፍ ያሳተሙ ስንት ናቸው?
5በተለያየ ሚድያ ታሪክ እያወሩ ኑሯቸውን የሚመሩ ስንት ናቸው?
6ታሪክ ባይኖር ይህ ሁሉ በምን ይኖራል ብለው ያስባሉ?የዓለም ቅርጽስ ምን ይመስል ነበር?
የእኛው ሀገር ችግር የሞላ ህሊናንም ሆድንም የሚያጠግበውን ታሪክ በመጥላት ላይ የተመሠረተ የቀነጨረ አስተሳስብ ነው፡፡
በዚያውስ ላይ ከታሪክ በላይ መምህር አለ?የለም? ከታሪክ እና ከሥነ ፍጥረት የበለጠ መምህር በምድር ላይ የለም፡፡


(መምሕር ገብረ መድኅን እንየው)



https://t.me/zdfitsumkebe
https://t.me/zdfitsumkebe
https://t.me/zdfitsumkebe
1.2K views✞£iŧsûm✞, edited  14:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-06 21:41:27
እንደዚህ ውብ የሆኑ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ስዕሎችንና ፎቶዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉ

https://t.me/+YkS5xznutqNjZTE0
https://t.me/+YkS5xznutqNjZTE0
451 views🄴🄻🄰, 18:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-06 20:28:38
እንኳን ደስ አላችሁ በዩቲዩብ የምናውቀው ማኅቶት ቲዩብ አሁን ደግሞ በቴሌግራም መጥታል ለመቀላቀል ከስር ያለውን ሊንክ ንኩት።


@Mahtot_Tube
@Mahtot_Tube
734 views✞£iŧsûm✞, 17:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-06 16:45:50
የተበተነ ሕሊና

አንድ ወጣት መነኩሴ አረጋውያኑን ልቡናዬ ይታወክብኛል በበአቴ መቀመጥ አልቻልኩም ስለዚህ ነገርም አዝናለሁ ብሎ ጠየቃቸው። ሽማግሌው መነኩሴም በበአትህ ተቀመጥ ሐሳብህም ወደ አንተ ይመለሳል አለው። አህያዋ የታሰረች ከሆነች ውርንጭላዋ ከቦታ ወደ ቦታ ይዘላል። በራቀ ጊዜም ወደ እናቱ ይመለሳል። እንደዚኹም ሐሳባችን በራሳችን ላይ ይነሣብናል ስለ እግዚአብሔር ብለን ከታገስን በጊዜው ቢበተን ወደ ባለቤቱ ይመለሳል ጸጥም ይላል። 

+++++
ከአባቶች መነኮሳት አንዱ እንዲህ ብሎ ጠየቀ ለምን ልቤን ያስጨንቀኛል ልቡናዬ ይጨነቃል። አንድ ቀን እንኳ አርፍ ዘንድ አይተወኝም። ስለዚኽ ነገር ነፍሴ ታዝናለች። ሽማግሌውም አለው:- ሰይጣን እንዲኽ ያለ ሐሳብ ሊያሳድርብህ ወደ አንተ ሲመጣ አትመልስለት የተለያዩ ቃላትን ያሳድርና ያበሳጭሃል። ነገር ግን መግዛት አይቻለውም። ትቀበለው ዘንድ አንዲቱን እንኳ ላንተ አያዝም (አንተን ማስገደድ አይችልም)። ….

መነኩሴውም ይኽ ነገር ይርቅልኝ ዘንድ እጸልያለው እሰግዳለሁ ነገር ግን ልቤ አያርፍም የምለውን (በቃሌ የምጸልየውን) አላውቅምና። ሽማግሌውም አለው ልጄ አንተ የምትችለውን ያህል አንብብ (ጸልይ) አባ ሙሴና ሌሎች አባቶችን ሁሉ ይኽንን ነገር ሲሉ ሰምቸዋለሁና። ሰነፍ ሰው የያዘውን የቃሉን ትርጓሜ አያውቀውምና ተበሳጭቶ ይተዋል። ነገር ግን እኛ የምንለውን (የምንጸልየውን) ካላወቅን ሰይጣን ቃላችንን ያውቃልና አፍሮ ከእኛ ይሸሻል አለው። 

መጽሐፈ ገነት

መ/ር ንዋይ ካሳሁን

https://t.me/akanim1wasen2
https://t.me/akanim1wasen2
https://t.me/akanim1wasen2
1.3K views✞£iŧsûm✞, 13:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-06 13:03:46 ስለ ሀይማኖቴ ማወቅ ግዴታዬ ነው የሚል ሊቀላቀሉት የሚገባ ቻናል ነው።
በቻናሉ ጥያቄ ይጠየቃል ምዕመኑም ይሳተፋል
ቻናሉን ለመቀላቀል)

ቤተ ክርስቲያን ከሕግ በላይ ናት
ኢየሱስ ክርስቶስ የሕግ ፍጻሜ ነው ማለት ምን ማለት ነው
ሕግ መቼ ተመሠረተ
ለምንስ ተመሠረተ

@EOTC_-OPEN_channel
@EOTC_-OPEN_channel
@EOTC_-OPEN_channel
291 views✞£iŧsûm✞, 10:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-05 22:59:31 መናፍቃን ከሚያነሷቸው 3 ጥያቄዎች መካከል
1)የጌታችን እኔ የአዳም የውርስ ኃጢአት/ጥንተ አብሶ/አለበት።
2)የጌታችን እናት አልተነሳችም
3)እየሱስ ክርስቶስ አማላጅ ነው።
ለነዚህ ጥያቄዎች እና ለመሳሰሉት መልስ የሚያገኙበት ቻናል ነው። አሁኑኑ ይቀላቀሉ።


@EOTC_-OPEN_channel
@EOTC_-OPEN_channel
@EOTC_-OPEN_channel
@EOTC_-OPEN_channe
92 viewsማኔ ቴቄል ፋሪስ, 19:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-05 22:35:49 ኦርቶዶክስ ተዋሕዶን እንወቅ
100 viewsማኔ ቴቄል ፋሪስ, 19:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-05 21:17:10 ጡቶችዋ የድንግልናን ወተት ማመንጨት በጀመሩ ጊዜ በክንዷ ደግፋ የምታጠባው ሕፃን፣ ፀሐይን እያወጣ ዝናምን እያዘነበ ፍጥረቱን የሚመግብ አምላክ መሆኑን ታውቅ ነበር። በእርሷ ማኅጸን በዝምታ ያደረው ጽንስ፣ በሰማይ ኃይላት "ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ" እየተባለ የመድረኩ መሠረት እስኪናወጽ ድረስ በታላቅ ድምፅ የሚመሰገን መሆኑ አልተሰወራትም።(ኢሳ 6፥4) ስለዚህም ራሷን ወደ ሆዷ ዘንበል በማድረግ የመላእክቱን ቅዳሴ ታደምጥ ነበር።

ድንግል ወደ እርሷ ማኅጸን የገባው "የሚሳነው ነገር የሌለ የልዑል ልጅ" እንደ ሆነ ብታውቅም ሁሉን አልጋ በአልጋ እንዲያደርግላት ግን አልተማጸነችውም። የልጇን ሁሉን ቻይነት ወልደው በሚያሳድጉ ሁሉ ከሚደርሰው የእናትነት ጭንቅ ማምለጫ አላደረገችውም። ከጡቶቿ ወተት ፈልጎ እንደ ሕፃናት ሲያለቅስ "አምላክ አይደል አይርበውም" ብላ ቸል አላለችም። ክፉው ሄሮድስ ሊገድለው በፈለገ ጊዜ "የአሸናፊ የእግዚአብሔር እናቱ" እመቤታችን ድል ነሺነቱ ወዴት አለ? አላለችም። ስለ ሄሮድስ ሠራዊት አስጨናቂነት ጉንጮቿ እስኪቃጠሉ ድረስ አነባች፣ የበኩር ልጇንም አንዴ በጀባዋ አንዴ በጎንዋ እያዘለች የግብጽን ተራሮች እንደ ወፍ ዞረች እንጂ።

በእነዚያ የረሃብ ጊዜያት ድንግል ከሃሊ ልጇ ከሰማይ መና እንዲያዘንምላት ወይም ድንጋዩን ዳቦ እንዲያደርግላት ጠይቃ አልተፈታተነችውም። እስራኤላውያን በበረሃ ጉዟቸው ወቅት የሚከተላቸው (ይዘው የሚጓዙት) ዓለት ነበራቸው። እነርሱም በተጠሙ ጊዜ የሚጠጣ የሚያገኙት ከዚያ ዓለት ከሚፈልቀው ውኃ ነበር። ቅዱስ ጳውሎስም ይህን ታሪክ በማስታወስ በበረሃ ውኃ ያፈልቅላቸው የነበረው ዓለት በምሥጢር የክርስቶስ ምሳሌ መሆኑን ሲናገር "ያም ዓለት ክርስቶስ ነበረ" ይላል።(1ኛ ቆሮ 10፥3) እመቤታችን የማይቋረጥ የሕይወት ውኃ የሚፈልቅበትን ይህን መንፈሳዊ ዓለት ይዛ ስትሰደድ አንድ ቀን ስለ ጥሟ አላማረረችውም። ራሱን በፈቃዱ ባዶ ላደረገው አምላኳ ከሁሉ ይልቅ በሥጋ ባዶ መሆንን በደስታ ለመቀበል የተዘጋጀ ቆራጥ ኅሊና ነበራት። ስለዚህም በልጇ ምክንያት ከደረሰባት መከራ በአንዱ እንኳን አላማረረችም።

+++ ወደ ምሥራቅ ተመልከቱ +++

ዲያቆን አቤል ካሳሁን

https://t.me/akanim1wasen2
661 viewsወሰንየለው ባህሩ, 18:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-05 14:07:21
የማንቂያ ደውል በመምህር ምህረታብ አሰፋ የሚቀርብላችሁ የቴሌግራም ቻናል ነው ቻናሉን በዚ ያገኙታል።

@memihr_mhretab_assefa
@memihr_mhretab_assefa
@memihr_mhretab_assefa
117 views✞£iŧsûm✞, 11:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ