Get Mystery Box with random crypto!

ፉርቃን ኦንላይን ቁርኣን ማዕከል

የቴሌግራም ቻናል አርማ yeilmkazna — ፉርቃን ኦንላይን ቁርኣን ማዕከል
የቴሌግራም ቻናል አርማ yeilmkazna — ፉርቃን ኦንላይን ቁርኣን ማዕከል
የሰርጥ አድራሻ: @yeilmkazna
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 8.91K
የሰርጥ መግለጫ

በየቀኑ የተለያዩ ኢስላማዊ እውቀቶችን ይሸምቱበታል። ይቀላለቀሉ፣ ለሌሎችም ያሰራጩ።

Ratings & Reviews

3.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 55

2022-09-09 17:51:51 ረሱል-ﷺ-እንዲህ ብለዋል:-
➧አዋጅ ! እኔ ቁርአንን ተሰጥቻለሁ እንዲሁም ከርሱ ጋር ሌላም የርሱን አምሳያ «ሀዲስን» ተሰጥቻለሁ።
ምንጭ፦ አቡ ዳውድ (4604)
1.2K viewsFurqan Online Quran, 14:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-09 11:57:58 የ “ዘመን መለወጫ” ኮተቶች
~
ኢትዮጵያ በምትከተለው ክርስቲያናዊው የዘመን አቆጣጠር መሰረት አዲስ አመት ሊገባ የያዝነው አመት እየተጠናቀቀ ነው። ታዲያ ይህን ክስተት ተከትሎ የሚፈፀሙ ከሃይማኖትችን ጋር የማይሄዱ በርካታ ጥፋቶች አሉ። ከነዚህም ውስጥ
1. ቀዳሚው ድግምትና ጥንቆላ ነው፡፡ በሃገራችን የተለያዩ አካባቢዎች ነሀሴ ሊጠናቀቅ ሲል በየጠንቋዩ ቤት የሚልከሰከሱት እጅግ ብዙ ናቸው። ከዚያም አምስቱ ወይም ስድስቱ የጳጉሜ ቀናት መንገዶች በድግምት ስራዎች ይሞላሉ። በነዚህ ቀናት ማልዶ የወጣ ሰው እንዲራመዳቸው ታስቦ በጎረቤት መተላለፊያ እና ህዝብ በሚያዘወትራቸው መንገዶች ላይ ፍየሎች፣ ዶሮዎች፣ ድመቶች፣ ጥንቸሎች ወዘተ ታርደው ይጣላሉ። በደም የተነከሩ ሳንቲሞች፣ ብሮች፣ ጌጣ-ጌጦች፣ የተለያዩ ቁሳቁሶች እዚህም እዚያም ወድቀው ይታያሉ። ጥንቆላና ድግምት:-

* ከኢስላም የሚያስወጡ ከባባድ ወንጀሎች ናቸው፡፡
وَاتَّبَعُوا مَا تَتْلُو الشَّيَاطِينُ عَلَى مُلْكِ سُلَيْمَانَ وَمَا كَفَرَ سُلَيْمَانُ وَلَكِنَّ الشَّيَاطِينَ كَفَرُوا يُعَلِّمُونَ النَّاسَ السِّحْرَ
“በሱለይማን ዘመነ-መንግስት ሸይጧኖች የሚያነቡትንም (ድግምት) ተከተሉ። ሱለይማን ግን አልካደም (ድግምተኛ አልነበረምና።) ግና ሸይጧኖች ሰዎችን ድግምት የሚያስተምሩ ሲሆኑ ካዱ።” [በቀራህ፡ 102]
ነብዩም ﷺ እንዲህ ብለዋል፡- {ጠንቋይ ዘንድ ሄዶ በሚናገረው ያመነ፣ በሙሐመድ ላይ በወረደው ክዷል።} [አሶሒሐህ፡ 3387]

* ደጋሚዎችና ከነሱ ዘንድ የሚመላለሱ ሰዎች መቼም ቢሆን ስኬት የላቸውም። ጌታችን እንዲህ ይላል፡- “ድግምተኛም በመጣበት ስፍራ ሁሉ አይቀናውም።” [ጦሃ፡ 69]

* ደጋሚዎች የሰዎችን ገንዘብ በማታለል የሚበዘብዙ መዥገሮች ናቸው። ገንዘቡን ለነሱ የሚሰጥ አካልም አላህ ፊት ተጠያቂ ነው። ነብዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል፡- {የኣደም ልጅ በቂያማህ ቀን አምስት ነገሮችን ሳይጠየቅ እግሮቹ አይንቀሳቀሱም። እድሜውን በምን እንዳጠፋው፤ ወጣትነቱን በምን እንደጨረሰው፤ ገንዘቡን ከየት እንዳመጣው፤ እንዲሁም በምን እንዳወጣው፤ ባወቀው ምን እንደሰራ።} [አሶሒሐህ፡ 946]

* ደጋሚዎች የነገር ቋቶች የማህበራዊ ህይወት ጠንቆች ናቸው። የተቸገረ ደንበኛቸው መፍተሄ ፈልጎ ሲመጣባቸው በብዛት የችግሩ መንስኤ የሆነው ወይ ጎረቤቱ፣ ወይ ዘመዱ ወይ ደግሞ የቤተሰቡ አባል እንደሆነ በመጠቆም ሰዎች ውስጣቸው እንዲሻክር አለመተማመን እንዲነግስ ያደርጋሉ። በድግምቶቹ ምክንያት የጤና መጓደል፣ የትዳር መፍረስ፣ የዝምድና መቆራረጥ፣ የጎረቤቶች በጎሪጥ መተያየት አልፎም ደም የሚያቃባ ግጭት እንዲከሰት ሁሉ ሰበብ ሊሆኑ ይችላሉ።

* ጠንቋይና ደጋሚ ዘንድ የሚሄድ ሰው የተነገረውን ባያምን እንኳን ከባድ ቅጣት ይከተለዋል። ነብዩ ﷺ እንዲህ ይላሉ፡- {ጠንቋይ ዘንድ ሄዶ ስለሆነ ነገር የጠየቀው የአርባ ቀን ሶላቱ ተቀባይነት የለውም።} [ሙስሊም፡ 5957]

2. ሌላው በ “ዘመን መለወጫ” አካባቢ የሚፈፀመው ጥፋት በአንዳንድ አካባቢ ያለው ጳጉሜን ተከትሎ ለዱዓህ መሰባሰብ ነው። እነዚህ አካላት የጳጉሜ ዱዓህ “መቅቡል ነው” (ተቀባይነት ያለው ነው) በማለት ነው ወቅቱን በዱዓእ የሚያሳልፏት። በጣም የሚገርመው ለዱዓህ የሚጥጠሩት እስልምናን ያውቃሉ ሰዎችን ያስተምራሉ የሚባሉት ሰዎች መሆናቸው ነው። ነብዩ ﷺ “አላህ እውቀትን ከባሪያዎቹ መንጠቅን አይነጥቅም። ይልቁንም ዑለማዎችን በመውሰድ (በመግደል) እውቀትን ይወስዳል። ከዚያም ዓሊም እስከማይቀር ድረስ። በዚያኔ ሰዎች መሀይማንን መሪዎች አድርገው ይይዛሉ። ሲጠየቁም ያለ እውቀት ፈትዋ ይሰጣሉ። በዚህም ይጠማሉ፣ ያጠማሉም” ማለታቸው ምንኛ የሚደንቅ ሐቅ ነው?! ዲን ያስተምራሉ ተብለው የሚታሰቡት አካላት ክርስቲያናዊ አቆጣጠርን መሰረት ያደረገ ዒባዳህ እየፈፀሙ ሰዎችን ወደ ጥፋት ሲወስዱ በገሃድ ይታያሉ።

3. ሌላኛው የ “ዘመን መለወጫን” ተከትሎ የሚፈፀመው ጥፋት መስከረም አንድን ወይም እንቁጣጣሽን ማክበር ነው። አቆጣጠሩ ሀገራዊ እንጂ እምነታዊ መሰረት እንደሌለው ሊያሳምኑ በከንቱ የሚዳክሩ ሰዎች አሉ። ነገሩ ሲበዛ ግልፅ ከመሆኑ ጋር በዚህ ላይ የሚሸወድ መኖሩ እጅጉን የሚደንቅ ነው። ብቻ ለማንም እንደማይሰወር ባስብም ለማስታወስ ያክል:-

* አቆጣጠሩ ወደ ሀገር ውስጥ የገባው በሚሲዮናውያን መሆኑ፣
* አመቱ ሲፃፍ መጨረሻ ላይ “ዓመተ ምህረት” መባሉ፣
* የነብዩ ዒሳን (ሰላም በሳቸው ላይ ይስፈንና) መወለድ መሰረት ያደረገ እንደሆነ መሞገታቸው
* እንዲሁም ይበልጥ ለማረጋገጥ የ “ዘመን መለወጫ” ወቅት ላይ ለምሳሌ “እንኳን ከዘመነ ማቲዎስ ወደ ዘመነ ማርቆስ፣ ከዘመነ ሉቃስ ወደ ዘመነ ዮሐንስ፣ ... አደረሳችሁ” ማለታቸው አቆጣጠሩና በአሉ ሃይማኖታዊ መሆናቸውን አጉልተው የሚያሳዩ ነጥቦች ናቸው፡፡ ይህንን ስንል የሚደብራቸው ክርስቲያኖች አሉ። እኛኮ ዒድን አብራችሁን ካላከበራችሁ አላልንም። ሰው እንዴት የኔን እምነት ካልተከተላችሁ ብሎ ሌሎችን በአክራሪነት ይፈርጃል?!
የእምነታችንን ጉዳይ ለኛ ብትተውልን። እምነታችን ሌሎች ህዝቦች በሚልለዩባቸው እምነቶች፣ ባህሎችና ልማዶች መመሳሰልን አይፈቅድም። ነብያችን ﷺ “በሰዎች የተመሳሰለ ከነሱው ነው” ብለዋል።
=
(ኢብኑ ሙነወር፣ ነሐሴ 26/2007)
የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/IbnuMunewor
1.3K viewsMohammed Jud, 08:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-08 20:03:01 እነዚህን ከ [ክፍል 4] የተጅዊድ ትምህርት የወጡትን ፈተናዎች በመስራት ራስዎን ይፈትሹ።

ቀጣይ ትምህርቶችን ለመከታተል
https://t.me/furqan_school
https://t.me/furqan_school
1.3K viewsFurqan Online Quran, 17:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-08 20:03:01
ከሚከተሉት መካከል የመድ (የመሳቢያ) ፊደል የሆነው የቱ ነው?
Anonymous Quiz
22%
ئ
11%
ء
55%
ا
11%
ؤ
645 voters1.2K viewsFurqan Online Quran, 17:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-08 20:03:01
ጀውፍ ማለት ምን ማለት ነው?
Anonymous Quiz
15%
የመጨረሻው መውጫ ቦታ
25%
የጉሮሮ ክፍቱ ክፍል
48%
ከአፍ እስከ ጉሮሮ ድረስ ያለ ክፍት ቦታ
11%
የአፍ ክፍል
580 voters1.2K viewsFurqan Online Quran, 17:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-08 14:58:23 "ቁርአንን መቅራት አላህ የሰው ልጅን ያከበረበት ትልቅ ፀጋ ነው፡ ቁርአንን መቅራት«መላኢኮች ያልተሰጡት የሰው ልጅ የተመረጠበት ፀጋ ነው»፡ለዚያም ነው የሰው ልጅ ሲቀራ ለመስማት በጣም ይጓጓሉ።"
ኢብኑ ሶላህ ረሒመሁሏህ
አል ኢትቃን ሊሲዩጢይ (275-1)
1.2K viewsFurqan Online Quran, 11:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-08 08:38:18 አሳሳቢ መልዕክት ስለ ጤንነትዎ

ማንኛውም ሰው በእለት ከእለት ህይወቱ ውስጥ

-
አልፎ አልፎ የሆድ መጮህ/መገለባበጥ
- ሰገራ መድረቅ
- አንዳንድ ጊዜ ሆድ መንፋት/በአየር መሞላት
- ልብ ማፈን/የድካም ስሜት መሰማት
- የምግብ ፍላጎት መቀነስ ወይንም በብዛት አለመስማማት
- ጀርባ ማቃጠል
- ኩላሊት አካባቢ ቁስለት መሰማት
- ጨጓራ ማቃጠል እና ሌሎችም ......
ምልክቶች ካሉበት በተለይም ዘመናዊ ህክምና ሂደው ፈውስ ካጡ

በምግብ የተበላ ወይንም የተጠጣ ሲህር /ድግምት መኖሩን የሚያሳዩ ምልክት ስለሆነ በአስሱና የሩቃ ህክምና መጥተው ይታከሙ ፣መድሃኒት ይጠጡ....

"ኢንሻአላህ ፈውስ ያገኛሉ"

➲ወደ ቻናሉ  ይቀላቀሉ ይጠቀማሉ!
➘➘➘➘➘➘➘➘ ➘➘➘➘➘➘➘
https://t.me/As_Sunah_Yeruqa_telegramgroup

https://t.me/As_Sunah_Yeruqa_telegramgroup
➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴

በስልክ ለማነጋገር ወይንም መፃፍ
የምትፈልጉ ከሆነ

በ 09-85-04-94-20 ወይንም 09-30-32-05-04 ይደውሉልን ፣ ይፃፉልን።

አሊያም በአካል ማግኘት ለምትፈልጉ
➘➘➘➘➘➘➘➘➘➘➘➘➘➘➘➘➘

ደሴ መላኩ - ኢትዮ ሆስፒታል ዝቅ ብሎ ላቭሊ ካፌ ፊትለፊት ያገኙናል።

⌲ ↶ለሌሎች ትምህርቱን ያስተላልፉ!
282 viewsMohammed Jud, 05:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-07 21:13:19 የተጅዊድ ትምህርት : 04

ከ ( التجويد المصور ) ከተሰኘው የታዋቂው የተጅዊድ ሊቅ ዶ/ር አይመን ኪታብ አጠር ባለ መልኩ የቀረበ

በወንድም ሙሀመድ ሀሰን (ጁድ)
┄┄┉┉✽‌»‌✿»‌✽‌┉┉┄┄
በOnline ተመዝግቦ ለመቅራት
@FurqanOnlineQuran
ይቀላቀሉን ፣ ሌላም ይጋብዙ
https://t.me/furqan_school
371 viewsFurqan Online Quran, 18:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-07 21:13:19
375 viewsFurqan Online Quran, 18:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-07 12:18:10 "ከቁርአን አንድን አንቀፅ አስተንትኖ እና ተገንዝቦ ማንበብ ሳይገነዘቡ እና ሳያስተነትኑ ሙሉ ቁርአኑን ከማኽተም ይሻላል!!!"
ኢብኑል ቀዪም ረሒመሁሏህ
(ሚፍታሁ ዳሪስ ሰዓደህ (187/1))
743 viewsFurqan Online Quran, 09:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ