Get Mystery Box with random crypto!

The Ethiopian Economist View

የሰርጥ አድራሻ: @wasealpha
ምድቦች: ኢኮኖሚክስ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 19.90K
የሰርጥ መግለጫ

Wase.belay12@gmail.com(0913243956)

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 35

2022-09-08 19:54:49 መረጃው ከብሄራዊ ባንክ፤ ከፋይናንስ ሚኒስትር ተሰብስቦ በሲቨስ የጥናት ተቋም የተጠቃለለ ነው፡፡ ሰነዱን ለማንበብ ለምትፈልጉ ሰዎች ከታች አስቀምጫለሁ፡፡
6.0K viewsWasyhun Belay, 16:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-08 19:53:11 በ2014 ጠቅላላ የውጪ ንግድ (Export and Import) ሪፖርት

የውጪ ንግድ (Export)፡- የኢትዮጲያ የውጪ ንግድ 4.1 ቢሊየን ዶላር የደረሰ ሲሆን ከባለፈው አመት የ600 ሚሊየን ዶላር ጭማሪ አለው፡፡ የውጪ ንግድ ግኝት 20 % ያድጋል ተብሎ የታቀደ ቢሆንም በ14 % ጭማሪ ያለው ግኝት ተገኝቷል፡፡

ወደ ውጪ የተላኩ ቁሳቁሶች የደረሱበት ሀገር ድርሻ ሲታይ ሲዊዘርላንድ 13%፤ ኔዘርላንድ 9%፤ አሜሪካ 9% ድርሻ፤ ሶማሊያ 8%፤  ሳውዲ አረቢያ 7% እና ጀርመን 7% በመሸመት ቀዳሚ ሲሆኑ በጠቅላላ ኢትዮጲያ ከ30 በላይ ለሆኑ የዓለም ሀገራት ምርቶቿን ልካለች፡፡

ከ2013 የውጪ ንግድ አንጻር በ2014 የተገኘው የ600 ሚሊየን ዶላር ጭማሪ ምክንያት የጎረቤት ሀገር ሶማሊያ የጫት ፍላጎት ማደግ (27%)፤ ጀርመን ለቡና ያላት ፍላት ማደግ (24%) እና ኔዘርላንድ ለአበባ የነበራት ፍላጎት ማደግ (19%) የፈጠረው ነው (እነዚህ ሶስት ሀገራት ያላቸው ፍላጎት ማደግ 70% የኢትዮጲያ የውጪ ንግድ እንዲያድግ አግዟል)፡፡ 

ወደ ውጪ የተላኩ ምርቶች ዝርዝር ሲታይ ቡና (1.4 ቢሊየን ዶላር)፤ ወርቅ (546 ሚሊየን ዶላር) እና አበባ (544 ሚሊየን ዶላር) ድርሻ አላቸው በድምሩ ሶስቱ ምርቶች ብቻ ከጠቅላላው ግኝት የ60% ድርሻ አላቸው፡፡

ወደ ውጪ የተላኩ ምርቶች መጠን ሲታይ ወደ ውጪ ከተላኩት መካከል ቡና በ57%፤ ስጋ በ45% ፤ ፍራፍሬ በ27% እና ጨርቃጨርቅ በ19% ወደ ውጪ የተላከው ከ2013 አንጻር እድገት ሲኖራቸው በተቃራኒው የቅባት እህል እና ጥራጥሬ በ26%፤ ወርቅ በ16% እና የቆዳ ውጤቶች በ9% ከ2013 አንጻር የቀነሰ ምርት ወደ ውጪ ተልኳል፡፡ ለውጪ ገበያ ከሚቀርቡ 18 ምርቶች መካከል 10 የሚሆኑ ምርቶች ጠቅላላ አቅርቦት በ2014 ዝቅተኛ ሆኗል፡፡

ይህ የሚያሳየው የውጪ ምንዛሬ ግኝት እድገቱ የተገኘው ከፍተኛ መጠን ያለው ምርት በመላክ ሳይሆን በዓለም ገበያ የመሸጫ ዋጋዎች በመጨመራቸው ነው፡፡ #ለምሳሌ፡- የቡና መሸጫ ዋጋ በዓለም ገበያ በ30% አድጓል፡፡ የውጪ ንግድ አፈጻጸም መለኪያ ዋነኛው በየዓመቱ ወደ ውጪ የሚላኩ ምርቶች መጠን እየጨመረ መሄዱ ቢሆብም ወደ ውጪ የሚላከው መጠን ቀንሶ የዓለም ገበያ ዋጋ በመጨመር የሚገኝ የትርፍ እድገት ውስን ድክመት አለበት፡፡

ቡና በከፍተኛ ሁኔታ በዓለም ገበያ ዋጋው በመጨመሩ የውጪ ግኝቱ ሲያድግ ጨርቃጨርቅ፤ አበባ እና ስጋ በከፍተኛ ሁኔታ መጠናቸው በመጨመሩ የውጪ ምንዛሬ ግኝቱ እንዲያድግ ሆኗል፡፡

#ለምሳሌ፡- የAGOA ክልከላ የጨርቃጨርቅ ምርትን ለጥቂት ወር የቀነሰው ቢሆንም ቀድሞ የነበሩ ትዛዞችን በመሸጥ፤ ከነታሪፉ በአሜሪካ ገበያ ማቅረብ የቻሉ አምራቾች መኖር እንዲሁም የጨርቃጨርቅ አምራቾች በአማራጭ የቻይና፤ የካናዳ እና የቱርክ ገበያዎች ላይ ሽያጭ መጀመራቸው መጠኑ እንዲያንሰራራ አድርጓል)፡፡

#ለምሳሌ፡- የአበባ ምርቶች ላይ አዳዲስ ማሳዎች መዘጋጀት እና ነባር የአበባ አምራቾች የማስፋፊያ ቦታ ማዘጋጀት (የአበባ ማሳዎች ስፋት በ12% ጨምሯል)፤ የማጓጓዣ ስርዓት መስተካከል እና የቀጠለ የአውሮፓ ሀገራት የአበባ ፍላጎት መኖር፤ ከአውሮፓ ውጪ ያሉ ሀገራት እንደ መካከለኛው ምስራቅ፤ እስያ እና አፍሪካዊያን የኢትዮጲያን አበባ ለመግዛት ያላቸው ፍላጎት በ19 % ማደጉ የአበባ ምርት መጠን በ2014 እንዲጨምር አድርጓል፡፡

#ለምሳሌ፡- የስጋ ምርት በመካከለኛው ምስራቅ ሀገራ ያለው ፍላጎት ካለፈው ሁለት ዓመታት ወዲህ በማደጉ 67 ሚሊየን ዶላር ይገኝበት የነበረው መጠን በ2014 ወደ 100 ሚሊየን ዶላር ግኝቱ አድጓል፡፡

በ2014 ጠቅላላ 22.7 ቢሊየን ዶላር ከተለያዩ ምንጮች የውጪ ምንዛሬ የተገኘ ሲሆን የቁሳቁስ ሽያጭ 4.1 ቢሊየን ዶላር፤  የአገልግሎት ሽያጭ 6.2 ቢሊየን ዶላር፤ ሬሚታንስ 5.3 ቢሊየን ዶላር፤ FDI 3.2 ቢሊየን ዶላር፤ ብድር 1.1  ቢሊየን ዶላር (ብድሩ በመንግስት እና በመንግስት የልማት ድርጅቶች በጋራ የተወሰደ ነው) እና እርዳታ 1  ቢሊየን ዶላር ነው፡፡

ከ2013 አንጻር ለውጪ ምንዛሬ ግኝቱ መጨመር የቁሳቁስ ሽያጭ በ13% የአገልግሎት ሽያጭ በ21% እና ሬሚታንስ በ2% እድገት የነበራቸው ቢሆንም የመንግስት ብድር በ100 ሚሊየን፤ የመንግስት የልማት ድርጅቶች ብድር በ900 ሚሊየን ዶላር እና እርዳታ በ300 ሚሊየን ዶላር ከ2013 አንጻር በ2014 ቀንሷል፡፡

በ2014 ጠቅላላ የተገኘ የውጪ ምንዛሬ 22 ቢሊየን ዶላር ቢሆንም ከውጪ የተሸመተው የ18 ቢሊየን ዶላር ወጪ ልዩነት 4 ቢሊየን ዶላር ያለፈ ሲሆን የ Balance of Payment ልዩነቱ በ2014ዓ.ም 2 ቢሊየን ዶላር ደርሷል፡፡ በ2013 ከነበረው የ2.9 ቢሊየን ዶላር ልዩነት አንጻር መሻሻል ያለው ሲሆን ክፍተቱን ለመሙላት የብሄራዊ ባንክ እና ከባንኮች ከነበረው ከጠቅላላ የውጪ ምንዛሬ ክምችት ተሸፍኗል፡፡

2014 ዓ.ም ሲጀምር የመንግስት የውጪ ምንዛሬ ግኝት እቅድ 5.4 ቢሊየን ዶላር ለማድረስ ቢሆንም የተሳካው 4.1 ቢሊየን ዶላር ነው፡፡ ይህም ግኝት የተገኘው የቡና እና የወርቅ ዋጋ በዓለም አቀፍ ገበያ በከፍተኛ ሁኔታ ስለጨመረ  (#ለምሳሌ፡- የኢትዮጲያ ቡና ዋጋ በዓለም አቀፍ ገበያ ከ2013 አንጻር በ25% ጨምሯል) አንዲሁም የአበባ እና የፍራፍሬ ምርት መጠን መጨመር ለግኝቱ አስተዋጾ አድርጓል፡፡ #ለምሳሌ፡- የጫት አቅርቦት በ21% ቢቀንስም በዓለም አቀፍ ገበያ (ጅቡቲ) ያለው የጫት ዋጋ በ23% በመጨመሩ የመቻቻል አይነት አዝማሚያ አለው ማለት ነው፡፡

የውጪ ንግድ (Import)፡- በ2014 ኢትዮጲያ ከፍተኛ ሸቀጦች ከውጪ ሀገራት ሸምታለች፡፡ በ2013 ከነበረው 14.2 ቢሊየን ዶላር በ2014 ወደ 18.1 ቢሊየን ዶላር የደረሰ ሸመታ አድርጋለች ይህም ላለፉት 10 ዓመታት ከነበረው የእድገት ትሬንድ አንጻር በ27% ጨምሯል፡፡

ኢትዮጲያ የሸመተችባቸው ሀገራት ስብጥር ስንመለከት፡ ቻይና 18% ድርሻ እና ህንድ 15% ድርሻ ይዘው ቀዳሚዎች ላኪ ሀገራት ሲሆኑ የተባበሩት አረብ ኢምሬት፤ ሳውዲ፤ ኪዌት፤ ቱርክ እና አሜሪካ እያንዳንዳቸው ከ1 ቢሊየን ዶላር በላይ ቁሳቁስ ወደ ኢትዮጲያ ልከዋል፡፡
ኢትዮጰያ ከውጪ ላስገባቻቸው ቁሳቁሶች ወጪ መጨመር አንዱ ምክንያት ከፍተኛ የዓለም አቀፍ ዋጋ መናር ነው፡፡ #ለምሳሌ፡- የነዳጅ ዋጋ በ83%፤ የእህል ዋጋ በ63% እና የአፈር ማዳበሪያ ዋጋ በ98% ዋጋቸው ንሯል፡፡ ዋና ዋና ወጪዎች ሲታዩ ነዳጅ 3.3 ቢሊየን ዶላር ወጪ፤ እህል 2.2 ቢሊየን ዶላር ወጪ እና የአፈር ማዳበሪያ  1.4 ቢሊየን ዶላር ግዢ ተከናውኗል፡፡ እነዚህ ግዢዎች በሙሉ የተከናወኑት በመንግስት ነው፡፡

የግል ሴክተሩ ሸመታዎች በአብዛኛው በ2014 ቀንሰዋል፡፡ #ለምሳሌ፡- የማምረቻ ግብዓት ግዢ በ22%፤ መኪኖች በ17% እና የግል መጠቀሚያዎች በ1% ከ2013 አንጻር ቀንሰዋል፡፡ ይህ የሚያሳየው ሸመታዎች ምርት እና ምርታማነት ማሳደግ ያለባቸው የ Capital goods ላይ ሳይሆን ወደ ሌሎች ቁሶች ላይ ያዘነበለ ነው፡፡ በተጨማሪም በተለያዩ ምክንያቶች ለግል ሴክተሩ የቀረበው የውጪ ምንዛሬ አናሳ በመሆኑ በግል ሴክተሩ የተደረገ ሸመታ ድርሻ ቀንሷል፡፡ #ለምሳሌ፡- የግብርና እና የማኒፋክቸር ተቋማት የማምረቻ ግብዓቶች (Capital goods) ሸመታ ከ2013 አንጻር በ1 ቢሊየን ዶላር ያህል ቅናሽ አላቸው፡፡ በርግጥ የውጪ ሸመታ መጠን ከጠቅላላ ሀገራዊ ምርት አንጻር ሲታይ ከነበረበት 13% ወደ 16% አድጓል፡፡
5.6K viewsWasyhun Belay, 16:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-08 10:51:06 የኢትዮጲያ የወጪ ንግድ አፈጻጸም!
በ2014 ኢትዮጲያ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ያገኘችው እንዴት ነው?

የኢትዮጲያ ጠቅላላ ወደ ውጪ የተላኩ ምርቶች መጠን እና የዓለም አቀፉ ገበያ ዋጋ ሁኔታ የኢትዮጲያ Export ገቢ እና Import ወጪ መጠንን እንዴት እንደወሰኑት የብሄራዊ ባንክ፤ የገንዘብ ሚኒስትር እና የሲቨስ ሪፖርት ዳሰሳን ትንታኔ

አቅርቤላችኋለሁ እስከመጨረሻ ተከታተሉት፡፡
5.4K viewsWasyhun Belay, 07:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-05 19:22:13 #መረጃ

ኢትዮጵያ በ2014 ከሁሉም ዘርፎች 22 ቢሊዮን ዶላር አግኝታለች፡፡


7.89 ቢሊየን ዶላር በውጭ አገር የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን እና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን እንዲሁም አለም አቀፍ ተቋማት በኩል የመጣ።


4.12 ቢሊየን ዶላር ከሸቀጦች ወጪ ንግድ የተገኘ፤ 3.31 ቢሊየን ዶላር ከውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት የተገኘ እና 6.3 ቢሊየን ዶላር ከአገልግሎት ዘርፍ የተገኘ ሲሆን የተቀረው ከሌሎች ምንጮች የተገኘ ነው፡፡


ኢትዮጵያ በ2014 ከውጪ ሀገር ምርቶችን ሸምቶ ለማስገባት 18.1 ቢሊየን ዶላር አውጥታለች በተጨማሪም ከውጪ ለተሸመተ አገልግሎት 4.9 ቢሊየን ዶላር አውጥታለች።


#መረጃው፦ የፕላን እና ልማት ሚኒስትር፤ የፋይናንስ ሚኒስትር እና የብሄራዊ ባንክ ነው!


#ለማስታወስ፦

Balance of payment፦ ኢትዮጵያ እንደመንግስት፤ እንደግለሰብ እና እንደተቋም የተወሰደ ብድር እና የተደረገ ክፍያን፤ ከውጪ ንግድ የተገኘ እና ከውጪ ለተሸመተ የሚደረግ ክፍያ፤ የውጪ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት ግኝት እና ክፍያ፤ ወዘተ ያጠቃልላል!


Trade balance፦ ከኢትዮጵያ ወደ ውጪ የተላከ (Export) ከውጪ ወደ ኢትዮጵያ ከገባ (Import) ሲቀነስ ያለ ልዩነት ነው።


ስለዚህ ገቢ ከወጪ አነሰ ማለት በሀገር ውስጥ ከነበረ የውጪ ምንዛሬ ክምችት ወይም በብድር የተደረገ ግዢ/ክፍያ አለ ማለት ነው።
2.0K viewsWasyhun Belay, edited  16:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-03 14:32:53 ዛሬ የሚኒስትሮች ም/ቤት ባካሄደው 13ኛ መደበኛ ስብሰባ የባንክ ዘርፍን #ለውጭ_ኢንቨስተሮች ክፍት ለማድረግ በቀረበ ረቂቅ ፖሊሲ ላይ ተወያይቶ በሥራ ላይ እንዲውል ወስኗል።


የባንክ ዘርፍን ለውጭ ኢንቨስተሮች ክፍት ማድረግ የዘርፉን አገልግሎቶች በእውቀት እና በቴክኖሎጂ ለመደገፍ፣ የአገራችን ኢኮኖሚ ከዓለም አቀፍ ገበያ ጋር ያለውን ትስስር ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር፣ የፋይናንስ ዘርፉን ተወዳዳሪነት፣ ውጤታማነትና ቀልጣፋነት በመጨመር በቂ የፋይናንስ አቅርቦት እንዲኖር የሚያስችል ረቂቅ ፖሊሲ በዛሬው ዕለት ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ቀርቧል፡፡


ምክር ቤቱ በፖሊሲው ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብዓቶችን በማከል በሥራ ላይ እንዲውል ተወስኗል።


የውጪ ባንኮች መግባት በባንኮች እና በኢኮኖሚው ላይ ሊኖረው የሚችለው እድል እና ስጋት ምንድን ነው? የኢትዮጵያ የፋይናንስ ገበያ እስካሁን ለውጪ ገበያው ክፍት አይደለም! ነገር ግን የውጪ ባንኮች ወደ ሀገር ውስጥ እንዲገቡ የማድረግ አዝማሚያ አለ! ስለዚህ የውጪ ባንኮች መግባትን ተከትሎ በሀገር በቀል ባንኮች እና በኢኮኖሚው ላይ ሊኖር ስለሚችለው እድል እና ስጋት ይህንን

ቪዲዮ አዘጋጅቻለሁ ተከታተሉት።
2.3K viewsWasyhun Belay, edited  11:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-02 19:00:55 አንድ ሰው ሲመክረኝ "የቤተሰቦቼ ጊቢ ውስጥ አንድ ክፍል ቤት ሰርቻለሁ፤ ኮንደሚኒየም ቤት ደርሶኝ እዳውን ለመክፈል ብዙ ቢቀረኝም ለማደስ የሚስቴ ወንድም እያገዘኝ ነው!" አለኝ "እና ለልጆች አንድ ቋሚ ነገር ለማድረግ መጣር ግድ ነው ሲል ሊመክረኝ ሞከረ!


እድልን ተሞርኩዞ እንደ ውጤታማ ትጉ ሰው ሌሎችን ለመምከር መሞከር ሙሉ አይደለም!


የቤተሰቡ ግቢ ያለው ቤት ካኮረፉት የሚያባርሩት! በእድል እጁ የገባው ኮንደሚኒየም ቤት እዳውን ከፍሎ መጨረስ ካለመቻሉ በተጨማሪ ለዓመታት ለማደስ እንኳን የሚስቱን ወንድም ችሮታ እየጠበቀ ነው።


ውጤታማነት መለኪያው የተዛባ መሆን የለበትም! እድል አንድ ጥሩ ነገር ነው (ግን እሴት ካልተጨመረበት ለሌሎች እንደ ብቃት ሊቆጠር አይችልም) በተመሳሳይ ካደረጉት ባልተናነስ ያደርጉት የነበረን ክፍተት ማየትም ተገቢ ነው!


ባጠራቀመው 300ሺ ብር Ph.D የሰራ ሰው እና ባጠራቀመው 300ሺ ብር ገጠር ላይ መሬት የገዛ ሰው ለተሞክሮ ቢቀመጡ ስለሆነ ጥረት ስለተጨመረ እድል ሊለዋወጡ ይችላሉ።


በርግጥ በኢኮኖሚክስ አስተምሮት ውስጥ ይዞ መገኘት እንጂ ይዘው የተገኙበት መንገድ ዋጋ የለውም! ብዙ አትርፍ እንጂ ህጋዊ መንገድ ተከትለህ ተገቢውን ብቻ መጠን አትርፍ የሚል ግልፅ መርህ የለም!


በሎተሪ እድል 10 ሚሊየን ብር ያገኘ ሰው እድለኛ ነው! ነገር ግን ውጤታማ የሚሆነው ገንዘቡን ማባዛት ሲችል ነው! ስለዚህ ሌሎችን መምከር መጀመር ያለበት ያገኘሁትን ብር እዚህ ደረጃ ላይ አደረስኩት እያለ መሆን አለበት።


ስኬት ዘርፈ ብዙ ነው! ሰዎች ህይወትን የሚጀምሩት እኩል ላይሆን ይችላል (የሃብታም ልጅ ከውርስ ቢነሳ እና የድሃ ልጅ ታናናሽ ወንድሞችን ከማሳደግ ቢጀምር እንደማለት ነው) ስለዚህ ውጤታማነት አሳማኝ እንዲሆን በየአጋጣሚው የሚያገኙት እድል ላይ የጨመሩትን ውስን ጥረት ማሳየት አለበት ባይ ነኝ።
4.3K viewsWasyhun Belay, 16:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 19:29:24 የመስከረም ወር ለቤተሰቦች ከፍተኛ የወጪ ዝርዝር ያለበት አስጨናቂ ወር ነው! መስከረም ወር መግቢያ ላይ የወጪ ዝርዝሩ የሚዛነፍ ቤተሰብ ለተከታታይ ወራት ወደ ጤነኛ የወጪ መስመር ለመምጣት ስለሚቸገር ምን ያድርግ?




2.2K viewsWasyhun Belay, 16:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 20:41:29 ለሎጂክ ብዙ እሩቅ የሆነውን #ከገንዘብ እና #ከፍቅር የቱ ይበልጣል? የሚል የመከራከሪያ ርዕስ ለኢኮኖሚስት ብታቀርቡ መልሱ የፈለጉትን መሸመት የሚችል ገንዘብ ሊበለጥ የሚችለው #በሰላም ብቻ ነው የሚል ነው!
1.6K viewsWasyhun Belay, 17:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 18:41:23 የጦርነት ተፅዕኖ በሚወስደው ጊዜ እና በሚሸፍነው የቦታ ስፋት የሚወሰን ቢሆንም #ተደጋጋሚ_ጦርነት ኢኮኖሚ ላይ ስለሚኖረው ተፅዕኖ ይህንን

ቪዲዮ አዘጋጅቻለሁ ተመልከቱት!
2.5K viewsWasyhun Belay, 15:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 17:59:46 የምትኖሩት ኑሮ #ዋናውን ነው?


ልጅ እያለሁ እናቴ የነበረንን ጥሩ #ብርድ_ልብስ ለሙቀትም ሆነ ለምቾት እናውጣው ስላት ለክፉ ቀን ነው የተቀመጠው ትለኝ ነበር!


አንዳንድ ቤተሰቦች ቤት ጥሩ ሰሀን፤ ሲኒ፤ ብርጭቆ፤ መጥበሻ፤ ወዘተ በብፌ ውስጥ ተቆልፎበት በተጣመመ ሰሀን መመገብ፤  በተሸረፈ ሲኒ መጠጣት ልምድ ነው።


አንዳንዶች ጋር ልብስ ሳይቀር ቀን እየጠበቀ ቁም ሳጥን ውስጥ ተንጠልጥሎ በዓመት አንዴ ብቻ ሊለበስ ይችላል (በዓመት አንዴ ሲዘንጥ ለራሱም ለሌሎችም እንግዳ ይሆናል!)።


የተለያዩ የኢኮኖሚክስ አስተምሮቶች ውስጥ የሰዎች ህይወት ወደ ፊት ባሉ ቀናት እንደሚመጣ ነው የሚመስሉት!


በኢኮኖሚክስ ቁጠባ መሰረታዊ ምክር ነው! ስለዚህ ከወጪ ቀንሶ መቆጠብ ግድ ነው #ለምሳሌ፦ ከጥሩ ምግብም ሆነ መጠጥ መቀነስ፤ ጥሩ ከመልበስ መቀነስ፤ ከመዝናናት መቀነስ፤ ወዘተ ማለት ነው።



አብዛኛው ኢኮኖሚያዊ ጥናቶች ገቢ ትዳር ከመያዝ እና ከልጆች ቁጥር ጋር ያለው ግንኙነት ቀጥተኛ ነው! #ለምሳሌ፦ ለመሰረታዊ ወጪዎች ገቢ ካልበቃ ትዳር ገቢው እስኪገኝ መቆየት አለበት የሚል ስሜት አለው! የልጆች ቁጥርም በተመሳሳይ።


#ለምሳል፦ ትዳር ለመያዝ፤ ልጅ ለመውለድ፤ ልጅ ለመድገም፤ ወዘተ መጀመሪያ ማሟላት ስለሚኖርባቸው ጉዳይ የሚያስቡ ሰዎችን የምትመለከቱት እድሚያቸው የደረሰ ቢሆንም #ወደፊት የሚል ቃል አለው!


#ለምሳሌ፦ ደሞዛቸው ዝቅተኛ ሆኖ ምንም ሳይኖራቸው ከሚበሉት ከሚጠጡት ቀንሰው ከ4 ዓመት በኋላ ትምህርቱ የተሻለ ገቢ አስገኝቶኝ #ወደፊት የምፈልገውን አደርጋለሁ የሚሉም አሉ።


#ለምሳሌ፦ ብዙዎች ለጡረታ ጊዜዬ በሚል ከመዝናናቱም ከሌሎቹም ቀንሰው #ወደፊት ለሚባለው Undefined ለሆነው ጊዜ ቅድሚያ ይሰጣሉ።


የዚህ አይነቱ አስተሳሰብ ሰዎች #ወደፊት እንዳሉ ማሰባቸውን ያሳያል! የኢኮኖሚክስ አስተምሮቶችም ሰዎች እና ድርጅቶች #ዛሬ የሚያደርጉት ውሳኔ በሙሉ #ነገ እንዳለ በማመን ነው።


#ለምሳሌ፦ ገቢ ማሳደግ (Income Maximization)፤ ወጪ መቀነስ (Cost Minimization)፤ እርካታ መጨመር (Utility maximization) የሚሉ የኢኮኖሚክስ ሃሳቦች ከዛሬ በተሻለ ነገን እርግጠኝነት የጎደለው በመሆኑ ወደፊትን የሻለ ትኩረት ስለመስጠት ነው።


ይህንን አስተምሮት እየተከተሉ ከሆነ ግለሰባዊ ግብ እና ከተለመደው ማዕቀፍ የዘለለ ነገር ሊኖር እንደሚችልም ማሰብ ተገቢ ነው።



#ለምሳሌ፦ በሰፈራችሁ ወይም መስሪያቤታችሁ  "ያሰኘውን ሳይበላ!፤ እንደጓደኞቹ ደህና ልብስ ሳይለብስ እና በስራ ተወጥሮ አንድ ቀን ሳይዝናና ሞተ!" የተባለ ሰው አላጋጠማችሁም?


ጥያቄው ወደፊት መቼ ነው? ደግሞ ችግሩ ይህ ወደፊት መቼ እንደሆነ አለመታወቁ ነው!


የመኖሪያ እድሜ ጣሪያን ያለፈ ጎልማሳ ወደፊትን ማስቀደሙ አይቀርም! አዛውንቶችን ጠጋ ብላችሁ አውሯቸው ለወደፊት ሲሉ ዛሬ የሚተውት ብዙ ነገር አላቸው።


አንዳንድ ሰዎች በሰራሁት ገንዘብ የተሻለ ካልተመገብኩ፤ የተሻለ ቤት ውስጥ ካልኖርኩ፤ በተወሰነ ጊዜ ውስጥ ሰውነቴን እና አዕምሮዬ ዘና እንዲል ካላደረኩ፤ ጥሩ ስሜት የሚፈጥርልኝን ንፁህ እና አዲስ ልብስ ካለበስኩ፤ ወዘተ ህይወቴን መቼ እኖራለሁ ይላሉ።


አንዳንዶች እኔን ጨምሮ እየኖርኩ ያለሁት እና ይበልጥ ዋጋ የምሰጠው #ለዛሬ ነው ነገር ግን የዛሬ ምቾቴ በቀጣይ ጊዚያትም እንዳላጣው ስለወደፊት ማሰብም መዘጋጀትም ያስፈልጋል በሚል የሚኖሩ አሉ።


ዋናው ጉዳያቸው ወደፊት እንደሆነ በአመለካከትም ሆነ በተግባር የሚያምኑ ሰዎች ዛሬ እየኖሩ ያሉት ለመጪው ዋና ህይወታቸው ዝግጅት እንደሆነ ያስባሉ።



ወደፊት የሚለው ጊዜ ግብ ወይም መስፈርት ከሌለው ግልፅ ስለማይሆን ሰውየውን ህይወቱን ሙሉ እንደደካማ እየቆጠረ እንዲኖር ሊያደርግ ይችላል።


#ለምሳሌ፦ ትዳር የምመሰርተው ቤት እና መኪና ሲኖረኝ ነው ያለ ሰው በ40 ዓመቱ ቤትም መኪናም አግኝቶ በ45 ዓመቱ ቢያገባ እና ቢወልድ ልጁ 18 ዓመት ሲሞላው Already አዛውንት ሆኗል (63 ዓመት)!



በ30 ዓመቱ አባት ሆኖ ቢሆን የ48 ዓመት ጎልማሳ እና የ18 ዓመት ወጣት መዝናኛ ቦታ ቢሄዱ ጨዋታቸው ተቀራራቢ ይሆን ነበር! ዛሬውን እየኖረ ወደፊቱን ማሰቡን ባያቆም እንደማለት ነው!
4.7K viewsWasyhun Belay, 14:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ