Get Mystery Box with random crypto!

The Ethiopian Economist View

የሰርጥ አድራሻ: @wasealpha
ምድቦች: ኢኮኖሚክስ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 19.90K
የሰርጥ መግለጫ

Wase.belay12@gmail.com(0913243956)

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 31

2022-10-27 19:25:52 ከአንድ ሰው ጋር እያወራን ይህንን ሃሳብ አነሳን፡- አብዛኛው ሃብታም (ቢሊየነር እና ሚሊየነር የሆኑ)፤ ታዋቂ አርቲስቶች፤ አትሌቶች፤ በተለያየ ዘርፍ ምሁራን፤ ከፍተኛ የስልጣን ደረጃ የደረሱ (ባለስልጣን መሆን እድል ይሁን ጥረት ግልፅ አይደለም!)፤ ወዘተ የህይወት ታሪካቸውን ሲናገሩ የልጅነት እና የወጣትነት ጊዚያቸውን በኢኮኖሚ ችግር እንዳሳለፉ ሲናገሩ መስማት የተለመደ ነው (ከዝቅተኛ ቤተሰብ በመውጣቴ ተቸግሬ፤ ለፍቼ፤ ተስፋ ሳልቆርጥ፤ ወዘተ ይላሉ) ከተባባልን በኋላ ምክንያቱ ምን ሊሆን እንደሚችል የየራሳችንን ምልከታ አስቀመጥን…..


1. "የዝቅተኛ ቤተሰብ አባል የሆነ ልጅ በጥረት ማደጉ የሚፈጥርለት ጥንካሬ ስለሚኖር ኑሮን ለማሸነፍ ሲል በሚያደርገው የተለያዩ የኑሮ መደጎሚያ ጥረቶች በአብዛኛው የስራ ዘርፍ ውጤታማ ነው! ስለዚህ በድህነት ያደገ በመጨረሻ ተሳክቶለት ይታያል ነገር ግን የሃብታም ልጅ በህይወት መንገዱ የኑሮ ጫና ስለማይገጥመው ውጤታማ ሆኖ ልምዱን ሲናገር አይታይም" የሚል፡፡


2. "ኢትዮጲያ ውስጥ ከጥቂት አስርተ ዓመታት በፊት (ለምሳሌ፡- 1960 እና 1970ዎቹ) የነበረ ቤተሰብ በአብዛኛው ተመሳሳይ የኑሮ ደረጃ ላይ ስለነበር የሃብታም እና የድሃ የሚባል የቤተሰብ ክፍፍል በብዛት አልነበረም! በተጨማሪም በቀደሙ ጊዚያት በአንድ ቤተሰብ ውስጥ የቤተሰብ ብዛት ከፍተኛ የመሆን እድል ስለነበረው የብዙ ሰዎች ታሪክ ከዝቅተኛ ቤተሰብ የመገኘት እድሉ ሰፊ ነው! ስለዚህ አብዛኛው ቤተሰብ ተቀራራቢ ኑሮ ከመኖሩ የተነሳ በምቾት አድጌ እዚህ የስኬት ደረጃ ላይ ደረስኩ የሚል ሰው ለማግኘት አስቸጋሪ ነው" የሚል ነበር!

3. "እኔ ግን ከዚህ ውስጥ ዋናው ቁምነገር ነው ብዬ እማስበው ነገር። ማንኛውም ትልቅ ደረጃ የደረሰ ሰው በየትኛውም አለም ላይ እስቲ በጣም የምታስታውሰው ነገር ወይም እንደ ትላንት ቀን ቁልጭ ብሎ የሚታይህን አንድ ነገር ንገረኝ ብትለው። ስላሳለፋቸው ምርጥ ምርጥ ጊዚያት፥ ስላሳለፋቸው የመዝናኛ ቦታዎች እና ቀናት አይደለም የሚነግርህ። የሚነግርህ ስላሳለፋቸው የፈተና ጊዜያት እና እንዴት በተሃምር ያንን ቀን እንዳለፈ ነው። ይህም የሚያሳይህ የችግር ጊዜያት መቶ እጥፍ ከስኬት ጊዜያት ጎልተው እንደሚታወሱ ነው። ይህም የሰው ልጅ ለሰርቫይቫል መጥፎ ጊዚያት ማስታወሱ ምን ያህል በህይወት እንዲቆይ እንደረዱት እና እራሱንም ለማስቀጠል ያንን ጊዜያት እንዳይረሳቸው በተፈጥሮ ዋየር እንደተደረገ ነው። ስለዚህ የድህነት ጊዜ የውጣ ውረድ ጊዜን ማስታወስ የሰው ልጅ ከመሆንና ከሰርቫይቫል ኢንስትኒክት ጋር የተገናኘ እንጂ ለኛ ኢትዮጵያውያን የተለየ ክስተት አለመሆኑን መረዳት ተገቢ ነው" (በቴሌግራም ከመጣ አስተያየት (ክበር አለማየሁ)።

#ውይይት፡- እናንተ ምን ትላላችሁ?
4.7K viewsWasyhun Belay, edited  16:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-26 19:35:13 ሀገራት ብራቸውን ለምን በብዛት አያትሙም? ሀገራት የራሳቸውን ገንዘብ የማተም መብት አላቸው? ሀገራት ለምን ገንዘባቸውን በሌሎች ሀገራት እዲታተም ያዛሉ? ኢትዮጲያ ገንዘቧን የት ነው የምታሳትመው?

ገንዘብ ለአንድ ኢኮኖሚ አስፈላጊም አደጋም ነው! ለዚህም ሲባል የገንዘብ ፖሊሲ (Monetary policy) በጠንካራ ተቋማት በከፍተኛ ክትትል እንቅስቃሴው እንዲመራ ይደረጋል፡፡

ብዙ የዓለማችን ሀገራት የራሳቸውን ገንዘብ በሌሎች ሀገራት ውስጥ እንዲታተም አዘው ይጠቀማሉ እንዲሁም ጥቂት ሀገራት ደግሞ የራሳቸው ገንዘብ በሀገር ውስጥ አትመው ይጠቀማሉ፡፡

#ለምሳሌ፡- ከአፍሪካ ናይጄሪያ፤ ሞሮኮ፤ ኬንያ፤ አልጄሪያ፤ ደቡብ አፍሪካ፤ ኮንጎ፤ ግብጽ፤ ሱዳን እና ዝምባብዌ በግል እና በመንግስት ማተሚያ ቤቶች በመጠቀም ገንዘባቸው በራሳቸው አትመው ይጠቀማሉ፡፡

#ለምሳሌ፡- አሜሪካ እና ህንድ የራሳቸውን የገንዘብ ኖት አትመው ይጠቀማሉ፤ ራሽያ የራሷን ኖት ከማተም አልፋ አንጎላ፤ ርዋንዳ፤ የመን፤ ሊባኖስ፤ ወዘተ ለሚባሉ ሀገራት ብሮቻቸውን ታትማለች፡፡

በዋናነት እንግሊዝ፤ ፈረንሳይ፤ ሲዊድን እና ጀርመን የበርካታ ሀገራት ገንዘብ በሃላፊነት ወስደው የሚያትሙ ሀገራት ናቸው፡፡ በተለይ ታዋቂ የሆነው እና የኢትዮጲያን ብር የሚያትመው የእንግሊዙ De La Rue ማተሚያ ቤት የ140 ሃገራትን ገንዘብ የሚያትም ሲሆን የዓለምን የገንዘብ ህትመት 11 ከመቶ ድርሻ የያዘ ከ162 ዓመት በላይ ልምድ ያለው ማተሚያ ቤት ነው፡፡ ኢትዮጲያ አዲሱን ገንዘብ ለማሳተም ከተለያ ማተሚያ ቤቶች ጋር የማተሚያ ዋጋ እንዲሁም በፍጥነት ማድረስ ከሚችል ማተሚያ ቤት ጋር ተነጋግራ እና አወዳድራ እንዳሳተመች ሲገለጽ ታስታውሳላችሁ፡፡

ገንዘብ በሀገር ውስጥ ማተም እና አለማተም ገንዘብ ሊኖረው የሚችለውን ጥራት እና የደህንነት መገለጫዎች አካቶ ማተም የሚችል ማተሚያ ከመኖር እና ካለመኖር ጋር ብቻ የሚገናኝ ነው፡፡ ሌላ ኢኮኖሚያዊ ምክንያት የለውም (አንዳንድ ሰዎች IMF ሀገራት ገንዘብ እንዲያትሙ የሚከለክል እና የሚፈቅድ ይመስላቸዋል)፡፡

#ለምሳሌ፡- አንዳንድ ሀገራት ብራቸውን ማተም ቢችሉም የማምረቻ ወጪው ከውጪ አሳትመው ቢያስገቡ ከሚኖረው ወጪ (የትራንፖርትን ወጪ ጨምሮ) ጋር በማወዳደር ቅናሽ ሆኖ ካገኙት ሌላ ሀገር ሊያሳትሙ ይችላሉ (ከአውሮፓ ፊንላድ እና ዴንማርክ ይሮ ከመምጣቱ በፊትም በኋላም ገንዘቦችን በሌሎች ሀገራት አንዲታተም ያደርጋሉ)፡፡

በኢኮኖሚክስ አስተምሮት ገንዘብ በዘፈቀደ ሊታተም እና ሊሰራጭ አይችልም (በኢኮኖሚ እና በፖለቲካ አስተዳደር ደካማነት ብዙ ገንዘብ ማተም የፈለገ ሀገር መብቱ ነው! ነገር ግን በዋጋ ንረት ዋጋ የሚከፍለው ኢኮኖሚው ነው)፡፡ የገንዘብ ኖት መጠን የሚወሰነው ጠቅላላ የሀገሪቱ ኢኮኖሚ ከሚኖረው እድገት እና እንቅስቃሴ አንጻር ከ3 ከመቶ ያልበለጠ ህትመት እንዲሆን ይመከራል፡፡

ብዙ ገንዘብ በኢኮኖሚ አለ ማለት የኢኮኖሚ እድገት ያመጣል ማለት አይደለም! ኢኮኖሚው በአምራች ክፍሉ በኩል ያለው የቁሳቁስ እና የአገልግሎት አቅርቦት ደረጃ ሳይጨምር ብዙ ገንዘብ ታትሞ በኢኮኖሚው ተሰራጨ ማለት ገንዘብ የያዙ ሰዎች ማለትም ፍላጎት ሲያድግ በአነስተኛው አቅርቦት ላይ ሽሚያ እንዲከሰት በማድረግ የዋጋ ንረትን ጣሪያ ያስነካል በቅስፈት የገንዘብ የመግዛት አቅም ይወርዳል፡፡

#ለምሳሌ፡- በኢትዮጲያ ብርሃን እና ሰላም ማተሚያ ቤትን አቅም በማሳደግ የብር ወረቀቶችን ደረጃውን ጠብቆ እንዲያትም ማድረግ ይቻላል፡፡ ማንም ብራችሁን እንዳታትሙ የሚል የለም ነገር ግን ብርን በኢኮኖሚያዊ አመክንዮ እንደፈለግን የፈለግነውን ያህል መጠን ማተም ጉዳቱ ስለሚታወቅ አይቻልም፡፡

#ለምሳሌ፡- የሌሎች ሀገራትን ገንዘብ በሀገር ውስጥ በማተም መጠቀም ግን አይቻልም! በሀገር ውስጥ ምንም ዘመናዊ ማሽን ቢኖር ዶላር እና ይሮ ሊታተም አይችልም! የየሀገራት ገንዘቦች በብሄራዊ ባንኮቻቸው በኩል የተመዘገቡ መሆን ግዴታቸው በመሆኑ ያልተመዘገበ ገንዘብ ወደ ዝውውር ሊገባ አይችልም፡፡

ለብዙ ሀገራት ገንዘብ በውጪ ሀገራት የማሳተም ወጪ እና ገንዘቡን በከፍተኛ ጥበቃ የማጓጓዝ ወጪ ከፍተኛ እንደሆነ ይታወቃል (ለምሳሌ፡- በ2018 ላይቤሪያ የታተመ ገንዘቧን ወደ ሀገር ውስጥ ከመግባቱ በፊት ተዘርፎ እንደተሰራጨባት ታስታውሳላችሁ)፡፡

እንደሚታወቀው ገንዘብ ተራ ወረቀት አይደለም እዳይባዛ የሚረዳው የራሱ መለያ ያለው እና የመቆየት ጥንካሬ ያለው (በቆዳ ይሰራ የነበረ ብር አሁን በጥጥ ወደ መሰራት ተሸጋግሯል) እንዲሆን ይመከራል፡፡ ስለዚህ ይህንን ማሟላት የሚችል የማተሚያ ግብዓት እና ቴክኖሎጂው ያላቸው ሀገራት የራሳቸውን ገንዘብ ማተም ሲችሉ ሌሎች አቅም ባላቸው ሀገራት አዋጪውን መርጠው ማሳተም ይችላሉ፡፡ ነገር ግን መታተም ያለበትን የብር መጠን (ባለ ስንት ብር?) እና የብር ኖት ብዛት (ምን ያህል?) መሆን እንዳለበት የመወሰን መብት የየብሄራዊ ባንኮቻቸው ስልጣን እና ሃላፊነት ነው፡፡
5.1K viewsWasyhun Belay, 16:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-26 13:16:42 #ጠቅላይ_ሚኒስትሩ፡- የኢኮኖሚ አሻጥር፣ ሌብነትና ምርት ሥወራ፤ ወደ ውጭ መላክ የሚገባውን ምርት መደበቅ፣ ሕገ ወጥ የውጭ ምንዛሬ ዝውውርና መሬትን በአሻጥር መውረር ዋነኞቹ የኢኮኖሚ ፈተናዎቻችን ሆነዋል።


በመሰረታዊነት የነዚህ በሙሉ ችግሮች ምክንያት ሁለት እንደሆነ ይሰማኛል! አንደኛ የአብዛኛው ምርት፤ አገልግሎት እና የውጪ ምንዛሬ አቅርቦት ከበቂ በታች መሆን እና ሁለተኛ በተቋማዊ አሰራር ደካማነት ምክንያት የሚፈጠሩ ናቸው፡፡ ስለዚህ አቅርቦት ላይ በሰፊው መስራት እና የተቋማትን አቅም ማጠናከር ተገቢ ነው፡፡
5.2K viewsWasyhun Belay, 10:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-25 15:53:12 ሀገራት ብራቸውን ለምን በብዛት አያትሙም? ሀገራት የራሳቸውን ገንዘብ የማተም መብት አላቸው? ሀገራት ለምን ገንዘባቸውን በሌሎች ሀገራት እዲታተም ያዛሉ? ኢትዮጲያ ገንዘቧን የት ነው የምታሳትመው? ይህንን በተመለከተ ሰፋ ያለ ትንታኔ አዘጋጅቻለሁ እስከመጨረሻ ተከታተሉት፡፡

6.0K viewsWasyhun Belay, 12:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-23 20:17:28 በፅሁፍ ለመግለፅ አመቺ የማይሆኑ እና ሰፊ ትንታኔ የሚፈልጉ ሃሳቦች ሲኖሩ የማቀርብበትን የዩቲዩብ ቻናል ሰብስክራይብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ!


https://youtube.com/channel/UCzc8ISpZJ6RskJmd_DEx7WQ
6.7K viewsWasyhun Belay, 17:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-22 13:06:12
የኢትዮጵያ ስንዴን ወደ ውጪ የመላክ አመክንዮ! የሀገር ውስጥ ፍጆታ በምን ደረጃ ላይ ሲሆን ነው የአንድ ምርት Export የሚመከረው?


የግብርና ኢኮኖሚስት ደምስ ጫንያለው (ዶ/ር) እና ዋስይሁን በላይ የምጣኔ ሃብት ባለሙያ አስተያየት!









7.4K viewsWasyhun Belay, 10:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-21 19:30:53 በዚህ ወቅት የኢትዮጲያ የውጪ ምንዛሬ ክምችት ለ21 ቀን የሚያሸምት ነው! ምን ማለት ነው?

በዓለም ላይ ያሉ ሀገራት የውጪ ምንዛሬ ክምችት በብሄራዊ ባንኮቻቸው በኩል በሀገር ውስጥ አልያም በሌሎች ሀገራት ባንኮች ውስጥ እንደሚያደርጉ ይታወቃል፡፡ የውጪ ንግዶች ግብይት  በአብዛኛው የሚደረገው በዶላር በመሆኑ ሀገራት ከፍተኛ ዶላር ከውጪ ምንዛሬ ግኝቶቻቸው ላይ ያስቀምጣሉ እሱ Foreign-Exchange Reserves ይባላል (የሌሎች ጠንካራ ምንዛሬ ያለባቸው ሀገራትን ገንዘብንም ሊያስቀምጡ ይችላሉ)፡፡

ሀገራት የውጪ ምንዛሬ ከውጪ ንግድ (Export)፤ ከብድር፤ ከእርዳታ፤ ከውጪ ከጥተኛ ኢንቨስትመንት (FDI)፤ ሌሎች ሀገራት ካሉ ዜጎጃቸው (Remittances)፤ ከቱሪዝም፤ ወዘተ ሊያገኙ ይችላሉ፡፡

የሚያከማቹትን የውጪ ምንዛሬ ከውጪ ሀገራት የሚፈልጓቸውን ቁሳቁሶች እና አገልግሎት ለመሸመት ሊጠቀሙበት ይችላሉ (ክምችቱ በዶላር አልያም በዓለም አቀፍ ቦንድ ሊሆን ይችላል)፡፡ ገንዘቡ ዓለም አቀፍ የንግድ እንቅስቃሴ ጤነኛ ባልሆነባቸው ጊዚያት እንደ ዋስትን ያገለግላል፤ የሀገር ውስጥ ገንዘቦችን የመግዛት አቅም ለመቆጣጠር ያግዛል…..

#ለምሳሌ፡- በቂ የውጪ ምንዛሬ ያከማቸ ብሄራዊ ባንክ የገንዘቡን የመግዛት አቅም እንዳይወርድ ሊጠቀምበት ይችላል፡፡ እንዴት? በቂ የውጪ ምንዛሬ በሌለበት ገበያ ሰዎች ወደ ጥቁር ገበያ የሚኖራቸው ፍላጎት ስለሚያድግ በጥቁር ገበያ የአንድ ዶላር የምንዛሬ መጠን እንዲጨምር ያደርጋል ምክንያቱም ብሄራዊ ባንክ የሰዎችን የውጪ ምንዛሬ ጥያቄ በቀላሉ መመለስ ስለማይችል ነው፡፡

በዓለም አቀፍ ገበያ ጤነኛ የሚባለው መደበኛ የመሸጥ እና የመሸመት ሂደት ሲስተጓጎል ሀገራት ከውጪ ምንዛሬ ክምችታቸው እያወጡ ማክሮ ኢኮኖሚውን ከዋጋ ንረት እና ከምርት እጥረት ይታደጋሉ፡፡

#ለምሳሌ፡- አንድ ሀገር በዓመት ውስጥ 10 ቢሊየን ዶላር የውጪ ምንዛሬ ከተለያዩ ምንጮች አግኝታ በተመሳሳይ ለተለያዩ ዓመታዊ ወጪዎቿ (ተገቢውን የውጪ እዳ መክፈልን ጨምሮ) በሙሉ 8 ቢሊየን ዶላር ወጪ ብታደርግ 2 ቢሊየን ዶላር ለመጠባበቂያ በሚል ብታስቀምጥ 2 ቢሊየን ዶላር ተቀማጭ ወይም በግምት ለ3 ወር የሚቆይ የሸመታ አቅም ያለው ክምችት አላት እንደማለት ነው፡፡

#ለምሳሌ፡- ቻይና እና ጃፓን ወደ ውጪ በመላክ የሚያገኙት ገቢ ከውጪ ከሚሸምቱት ጋር ሲነጻጸር ከፍተኛ በመሆኑ ከፍተኛ የውጪ ምንዛሬ ክምችት አላቸው፡፡

የተወሰኑ ያደጉ እና በማደግ ላይ ያሉ ሀገራት የውጪ ምንዛሬ ክምችታቸው የምን ያህል ጊዜ የሸመታ አቅማቸውን እንደሚሸፍን ለማየት ያህል አሜሪካ ለ3 ቀን፤ ጀርመን ለ9 ቀን፤ ፈረንሳይ ለ27 ቀን፤ ኬንያ ከአራት ወር በላይ፤ ህንድ ለ8 ወር፤ ጃፓን እና ቻይና ከአንድ አመት በላይ፤ ሲዊዘርላንድ ከ2 ዓመት በላይ፤ ኢትዮጲያ ለ21 ቀን፤ ወዘተ ነው፡፡

ይህንን መረጃ ጉግል በመግባት መመልከት ይቻላል፡- In the latest reports, US Foreign Exchange Reserves equaled 0.1 Months of Import in Aug 2022, In the latest reports, Germany Foreign Exchange Reserves equaled 0.3 Months of Import in Jul 2022, Kenya Foreign Exchange Reserves equaled 4.9 Months of Import in Jun 2022, Switzerland Foreign Exchange Reserves equaled 31.5 Months of Import in Aug 2022, In the latest reports, France Foreign Exchange Reserves equaled 0.9 Months of Import in Jul 2022.

በቂ የውጪ ምንዛሬ በብሄራዊ ባንኮቻቸው ማከማቸት የቻሉ ሀገራት ከዓለም አቀፍ ተቋማት ተጨማሪ ብድር ለመቀበል የሚኖራቸው መተማመኛ ደረጃ የተሻለ ነው ሊሉ ይችላሉ፤ ዓለም አቀፍ እና ሀገር አቀፍ የተለያዩ አደጋዎች በሚፈጠሩ ጊዜ እና መደበኛ እንቅስቃሴዎች ሲስተጓጎሉ እንደ ዋስትና ሆኖ ያገለግላል (የ2008 የፋይናንስ ቀውስ ወቅት፤ በኮቪድ ወቅት፤ አሁን ደግሞ በራሽያ እና ዩክሬን ጦርነት ወቅት፤ ወዘተ ወቅት ሀገራት ችግሮችን አልፈውባቸዋል)……

የውጪ ባለሃብቶች ወደ ሃገር ውስጥ ገብተው ኢንቨስት ለማድረግ የሃገሪቷን የውጪ ምንዛሬ ክምችት እንደ መተማመኛ ይቆጥራሉ! ስለዚህ ከፍተኛ የውጪ ምንዛሬ ክምችት አለ ማለት የሰሩበትን በቀላሉ መቀበል መቻላቸውን በመተማመን በዛች ሀገር ኢንቨስት ለማድረግ ሊወስኑ ይችላሉ፡፡ የውጪ ምንዛሬ ክምችት የሌላት ሀገር በዓለም አቀፍ አበዳሪ ሀገራት እዳ የመክፈል አቅሟ ደካማ ነው ስለሚባል ከፍተኛ የብድር ወለድ እንዲሰላባት ሊያደርግ ይችላል፡፡

የውጪ ምንዛሬ ክምችት መጠን እድምታው ለሁሉም ሀገራት ተማሳሳይ አይደለም ምክንያቱም ኢትዮጲያ እና ጀርመን ለዓለም አቀፍ ተቋማት የብድር ጥያቄ ቢያቀርቡ ተመሳሳይ መስፈርት፤ የውጪ ባለሃብቶች ኢትዮጲያ እና ጀርመን ሀገር ኢንቨስት ለማድረግ ተመሳሳይ መስፈርት ሊኖራቸው አይችልም፡፡

#ለምሳሌ፡- በተለይ የየሃገራቱ የውጪ ምንዛሬ ክምችት መጠንን በተመለከተ ተመሳሳይ መስፈርት ባለሃብቶች ሊኖራቸው አይችልም! ምን ማለት ነው አንድ ህንዳዊ ባለሃብት ጀርመን ሀገር ኢንቨስት በማድረጉ ገንዘቡን በውጪ ምንዛሬ የማግኘት እድሉ ኢትዮጲያ ውስጥ ኢንቨስት የማድረግን ያህል በብዙ መለኪያ አያሰጋውም ለማለት ነው፡፡

ሀገራት ለአደጋ ጊዜ ከሚኖራቸው ክምችች በላይ በፍጥነት ኢኮኖሚያዊ አቅሞቻቸውን ለማጠናከር የንግድ ሚዛን ክፍተታቸው ዝቅተኛም ሆኖ የውጪ ምንዛሬ ክምችታቸው ዝቅተኛ ሊሆን ይችላል፡፡ ምን ማለት ነው? ፈረንሳይ የውጪ ምንዛሬ ክምችቷ ከኬንያ በታች የሚያቆያት መሆኑ ሀገራቱ ያላቸውን የውጪ ምንዛሬ ለመጠቀም የወሰኑበትን ደረጃ እንጂ ያላቸውን ኢኮኖሚያዊ ጥንካሬ እና ድክመትን አመላካች ነው ማለት እንዳልሆነ ያሳያል፡፡

#ማስታወሻ፡- IMF በዘንድሮ ትንበያው የቀጣይ ዓመት የኢትዮጲያ የውጪ ምንዛሬ ክምችት የሸመታ አቅም አሁን ካለበት 21 ቀን ወደ 18 ቀን ዝቅ ሊል ይችላል ብሏል፡፡ በ2014 ኢትዮጲያ ከውጪ የሚያስፈልትን ቁሳቁሶች በተወሰነ መልኩም ለመሸመት ከ18 ቢሊየን ዶላር በላይ እንዳወጣች ይታወቃል ስለዚህ በ2022 በግርድፉ ከተሰላ 1.03 ቢሊየን ዶላር ገደማ የውጪ ምንዛሬ ክምችት በካዝናዋ አላት እንደማለት ነው፡፡
7.1K viewsWasyhun Belay, 16:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-20 21:39:47 የኢትዮጵያ የውጪ ምንዛሬ ክምችት ለ21 ቀን ሸመታ ብቻ የሚበቃ ነው! ምን ማለት ነው? ይህንን በተመለከተ ይህንን ትንታኔ እስከመጨረሻው ተመልከቱት።

5.8K viewsWasyhun Belay, 18:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-20 09:28:13
የሀገር ውስጥ አምራቾች ከውጪ ምርቶች ጋር ከመፎካከር በላይ የግብዓት እጥረት፤ የብድር አቅርቦት እጥረት፤ አነስተኛ ካፒታል፤ የማምረቻ ቦታ እጥረት፤ የመሰረተ ልማት እጥረት (በተለይ የሃይል እጥረት)፤ የሰላም እጦት እና የተንዛዛ አሰራር በመኖራቸው እየተፈተኑ በመሆኑ ስትራቴጂካል ድጋፍ በማድረግ የሀገር ውስጥ አምራቾች ከውጪ የሚገቡ ምርቶችን የመተካት አቅም እንዲኖራቸው ማድረግ ተገቢ ነው።
5.7K viewsWasyhun Belay, 06:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-19 11:08:40 የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ሕገ ወጥ የገንዘብ ዝውውርን ለሚጠቁሙ ወሮታ የሚከፈልበትን መመሪያ በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥቷል፡፡


በቅርቡ ብሄራዊ ባንክ 4 ህገወጥ ጉዳዮች ላይ ህብረተሰቡ ጥቆማ እንዲያደርግና ጥቆማ ለሚያደርጉ ዜጎችም #ወሮታ እንደሚከፍል ማስታወቁ ይታወሳል፡፡


በዚህም መሰረት፡-

1. ከተፈቀደ በላይ የሀገር ውስጥም ሆነ የውጭ ሀገር ገንዘብ ማከማቸት፤

2. ሀሰተኛ የገንዘብ ህትመት መፈፀም፤

3. የወርቅ ክምችት፤

4. ገንዘብ ህገወጥ በሆነ መንገድ ያለፈቃድ ማስተላለፍ በሚፈፅሙ ግለሰቦች ላይ ዜጎች ጥቆማ እንዲሰጡ እና ዜጎች ለሚሰጡት ጥቆማ ወሮታ እንደሚከፈላቸው ገልጾ ነበር።


- በባንክ ከተፈቀደው በላይ የገንዘብ መጠን ይዘው የሚገኙ ግለሰቦችን ለጠቆሙ ከተያዘው ገንዘብ 15 በመቶ፣

- የውጭ ሀገር ገንዘብ ዝውውር ለሚጠቁሙ 15 በመቶ፣

- ሕገወጥ ሐዋላን ለሚጠቁሙ 25 ሺህ ብር ወሮታ ይከፈላቸዋል።


ለግለሰቦች በቀን ከ100 ሺህ ብር በላይ መያዝ፣ ለተቋማትም በቀን ከ200 ሺህ ብር በላይ መያዝ የተከለከለ ነው።


ይህን መመሪያ የተላለፈን ግለሰብ ወይም ተቋም ለጠቆመ #ምስጢራዊነቱን በተጠበቀ መልኩ ወሮታው ተፈጻሚ እንደሚሆን ተገልጿል።


ጥፋተኛ ሆኖ የተገኘ ግለሰብ በከባድ የኢኮኖሚ ወንጀል እስከ 15 ዓመት ጽኑ እስራት እንደሚቀጣ ነው የተመላከተው።


ጠቋሚዎች በስልክ ቁጥር 0118133960፣ በኢ.ሜል አድራሻ tikoma@nbe.et፣ በፋክስ ቁጥር 0115514366 እንዲሁም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የፖ.ሣ.ቁጥር 5550 ላይ ጥቆማ መስጠት እንደሚቻል የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አስታውቋል።
5.7K viewsWasyhun Belay, 08:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ