Get Mystery Box with random crypto!

The Ethiopian Economist View

የሰርጥ አድራሻ: @wasealpha
ምድቦች: ኢኮኖሚክስ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 19.90K
የሰርጥ መግለጫ

Wase.belay12@gmail.com(0913243956)

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 34

2022-09-16 19:38:29 የውጪ ባንኮች ወደ ሀገር ውስጥ በመግባታቸው የሀገር ውስጥ ባንኮች ደንበኞቻቸውን ያጣሉ?


ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የውጪ ባንኮች ወደ ሃገር ውስጥ እንዲገቡ መታሰቡን ተከትሎ ብዙ ሰዎች የሀገር ውስጥ ባንኮች ህልውና አሉታዊ ተጽኖ እንደሚደርስበት ያስባሉ! የሀገር ውስጥ ባንኮች ደንበኞቻቸውን ሊያጡ ስለሚችሉ ይጎዳሉ የሚል መከራከሪያ ያነሳሉ!


በመጪው ጊዚያት ውስን የሀገር ውስጥ ባንኮች ሊጎዱ ይችላሉ! ነገር ግን የሚጎዱት የውጪ ባንኮች ስለሚገቡ ወይም መሰረታዊ ደንበኞቻቸውን ስለሚያጡ ነው ብዬ አላስብም!


ለዚህ ውይይት እንዲረዳን የፋይናንስ ገበያውን ባህል እንመልከት! የቆጣቢው ህዝብ ብዛት፤ ሰዎች የሚቆጥቡበት/የባንክ ደብተር የሚከፍቱበት ምክንያት እና አማካይ ሰዎች በየባንክ አካውንታቸው እየቆጠቡ ያሉት የቁጠባ መጠን፤ ወዘተ፡፡


በተመሳሳይ የውጪ ባንኮች መሰረታዊ ትኩረት ቁጠባን በማሰባሰብ ለብድር ማቅረብ ሳይሆን ከተከማቸ ካፒታል ብድር በማቅረብ ከከፍተኛ የብድር ወለድ ትርፍ መሰብሰብ ነው፡፡ ስለዚህ የሀገር ውስጥ ባንኮች ሰፊ የቁጠባ ስርዓት ላይ መሳተፋቸውን ከቀጠሉ ለብድር ሊያቀርቡት የሚችሉት ካፒታል ተቀማጭ ገንዘብ ሳያጡ በገበያው ሊቆዩ ይችላሉ፡፡


#ለምሳሌ፡- የውጪ ባንኮች በሀገር ውስጥ የማህበራዊ ተሳትፏቸው ደካማ ነው! እንዲሁም ዋና መስሪያ ቤት ላይገነቡም ይችላሉ! ምን ማለት ነው በተዘዋዋሪ በተደረገላቸው ጥበቃ ወይም ማህበራዊ ሃላፊነታቸውን ለመወጣት በከፍተኛ ሁኔታ ወጪ በማውጣት የሚሳተፉ የሀገር ውስጥ ባንኮች በተወሰነ መልኩ ከተሳትፏቸው ሊቀንሱ ይችላሉ! ነገር ግን ከጠቅላላ ኢኮኖሚው ፋይዳ አንጻር የሚቻቻል ይሆናል ብዬ አስባለሁ፡፡


ልብ በሉ አሁንም የውጪ ባንክ ሳይገባም የባንክ ሴክተሩን ፉክክር መቋቋም ያቃታቸው የሀገር ወስጥ ባንኮች አሉ! በተመሳሳይ ከ5 ዓመት በኋላ (ለአዳዲስ ባንኮች እስከ 7 ዓመት) መሟላት የሚገባው የ5 ቢሊየን ብር ተቀማጭ ካፒታል ለሟሟላት ብዙ የሚቀራቸው ባንኮች ብዙ ናቸው፡፡


በርካታ ሃብቶቻቸውን ዋስትና በማስያዝ በቢሊየን እና በመቶ ሚሊየን ብድር ውስጥ ያሉ ደንበኞች እስከ 30 ዓመት የሚቆይ የእዳ ዋስትና ውስጥ በመሆናቸው በቀላሉ ከነባር የሀገር ውስጥ ባንኮች በመላቀቅ ከውጪ ባንኮች ዋስትና አስይዘው ብድር ለመውሰድ የሚያስችል አቅም ሊኖራቸው ስለማይችል የሀገር ውስጥ ባንኮች ከፍተኛ ተበዳሪ ደንበኞቻቸው እንደያዙ በገበያው ትርፋማነታቸውን ይዘው የሚቀጥሉ ይሆናል፡፡


የውጪ ባንኮች መግባት ከፍተኛ መጠን ያለው ብድር ለማቅረብ ድፍረት ወይም አሰራር ሊኖራቸው ስለማይችል ወደ ተለያዩ ታዳጊ ሀገራት ገበያ ሲገቡ ዝቅተኛ ብድሮች ላይ የመሳተፍ ልምድ ስላላቸው የሀገር ውስጥ ባንኮች ከፍተኛ የብድር ጥያቄዎችን በማስተናገድ በገበያው ሊፎካከሩ መቻላቸው አይቀርም፡፡


ባንኮች ያለባቸው አደጋ የውጪ ባንኮች ከመግባታቸው በፊትም ለረጅም ዓመታት ለባለሃብቶች/ድርጅቶች ያቀረቡትን ብድር ወለድ እንጂ ዋናውን በመሰብሰብ የተመዘገበ ትርፋቸው ዝቅተኛ በመሆኑ የመጪው ጊዜ ስጋታቸው ከውጪ ባንኮች ጋር ከመፎካከር በላይ እስካሁን ሲያቀርቡ የኖሩትን ዋናውን/Principal ብድር ማስመለስ ላይ ነው (ሁሉም ብድር በበቂ ዋስትና የቀረበ ነው ብሎ ማሰብ ጤነኛ አይደለም)፡፡


በባንኮች የቁጠባ ታሪክ ውስጥ ብዙ የባንክ ደብተር የሚከፍቱ ሰዎች እና በምክንያት ሳይሆን በሰዎች ጉትጎታ ብዙ አካውንት የሚከፍቱ ሰዎች በአካውንቶቻቸው የሚያንቀሳቅሱት ገንዘብ ከፍተኛ ባለመሆኑ አዳዲስ የውጪ ባንኮች በገቡበት ቅስፈት ብዙ ሰዎች ተጨማሪ አካውንት ከውጪ ባንኮች ቢያወጡ ከፍተኛ ቁጠባ ወደ ውጪ ባንኮች የሚዛወር እና ከፍተኛ ቁጠባ ከሃገር ውስጥ ባንኮች የሚወጣ ሊሆን ይችላል ብዬ አላስብም፡፡


#ለምሳሌ፡- የሰዎች ልምድ በመሆኑ የመጀመሪያ ወራቶች ላይ የውጪ ባንክ አካውንት የሚኖራቸው ሰዎች ቁጥር እንደወረት መጨመሩ አይቀርም! በተመሳሳይ የሳፋሪኮም 07 መነሻ ሲም ካርድ የሚያወጣ ሰው ቁጥር ቀላል ሊሆን አይችልም፡፡


መደበኛ የሀገር ውስጥ ባንኮች ገጠሩን ሲነኩ ስላልኖሩ እና የገጠሩ ክፍለ ኢኮኖሚ የፋይናንስ አቅርቦት እየተሸፈነ ያለው በመደበኛ የዋስትና ማስያዣ ባለመሆኑ አደጋ በመጋራት የብድር እና ቁጠባ ተቋማት ህልውና የውጪ ባንኮች በመግባታቸው ይበልጥ የሚፈተን ሊሆን ይችላል፡፡


ነገር ግን የገጠሩ ማህበረሰብ ንቃተ ህሊና እና ለአዳዲስ አሰራሮች የሚኖራቸው ተሳትፎ ፈጣን ባለመሆኑ ከተለመደው የብድር እና ቁጠባ የደንበኝነት መዝገቦቻቸው ወደ አዳዲሶቹ የውጪ ባንኮች ደንበኛ ለመሆን ፈጣን ምላሽ ይሰጣሉ ለማለት እንደሚያስቸግር ይሰማኛል፡፡


#ለምሳሌ፡- አዳዲስ የግብርና አሰራር (ምርጥ ዘር፤ መስኖ/ውሃ ማቆር፤ ኩታ ገጠም፤ የመኖ ዝርያ፤ ወዘተ) ለማስተዋወቅ በጣም ከፍተኛ ተግዳሮት የሚኖረው ከተለመደው የወጡ ልምዶችን ቶሎ ያለመቀበል ባህሪ በብዛት ስላል ነው)፡፡


የውጪ ባንኮች ባይመጡም ወደፊት ሁሉም የሀገር ውስጥ ባንኮች የተለመደውን ትርፋቸውን ይዘው ሊቀጥሉ አይችሉም! ውስን ባንኮች አሁንም በተሻሉ ባንኮች እየተዋጡ ነው፡፡ የስራ ማስኬጃ ወጪያቸውን እስከሸፈኑ ድረስ እንዳልወደቁ የሚያስቡ እንዲሁም ለባለአክሲዮን የትርፍ ክፍፍል መስጠት ተቸግረው/ዝቅተኛ መጠን የትርፍ ክፍፍል በተደጋጋሚ እያቀረቡ ያሉ ባንኮችን ታዘቡ፡፡


#ለምሳሌ፡- አንድ ባንክ በበቂ ሁኔታ ከፍተኛ ደሞዝ ለሃላፊዎቹ፤ ለሰራተኞቹ እና አበል ለቦርዶቹ እስከከፈለ እና የስራ ማስኬጃ ወጪውን እስከሸፈነ ድረስ አክሲዬን የገዙ ደንበኞች ምንም ትርፍ አላገኙም በሚል የሚጨነቅበት ደረጃ ምን ያህል ነው? በተመሳሳይ የባንከ ባለአክሲዮኖች  ባንካችን የትርፍ ክፍፍል እየሰጠን አይደለም ስለዚህ ይቅርብን ቢሉ! ለሶስተኛ ወገን ከስረው ካላስተላለፉ በቀር አሰራሩ ቀላል ነው?


የውጪ ባንኮች ቢገቡም ባይገቡም ወደ ፊት የካፒታል ገበያው ሲከፈት አሁን ካለው በተሻለ የነባር/ውጤታማ ባንኮች አክሲሆን ለገበያ በሰፊው ሊዘዋወር ስለሚችል ባለአክሲዮኖቻቸውን እያጡ የሚመጡ ባንኮች እንዲሁም አዳዲስ ባንኮች ለመክፈት ለገበያ ለሚቀርብ አክሲዬን ለመግዛት ፍላጎቶቻቸው የሚቀንስ ትርፍ ላይ ትኩረት የሚያደርጉ ሰዎች ቁጥር እየጨመረ ስለሚመጣ አሁን ላይ ደካማ ባንኮች እስከ ጥምረት የደረሰ ስትራቴጂ ማሰብ መጀመር አለባቸው (ጠቅላላ ጉባዬ ላይ ባለአክሲዬኖች ይህንን የመፍትሄ ሃሳብ ቢያነሱ ስህተት ነው?)፡፡


በተቃራኒው የውጪ ባንኮች መግባትን እንደ እድል በመቁጠር በቴክኖሎጂ፤ በዘርፉ በሰለጠነ የሰው ሃይል፤ በቀልጣፋ አሰራር፤ በደህንነት አመራር፤ በጥምረት ብድር የማቅረብ አሰራር፤ ወዘተ ላይ ማሻሻያዎችን በማድረግ በጋራ ለማደግ ቀዳዳዎችን መፍጠር የሚችሉ የሀገር ውስጥ ባንኮች ለውጡን በብዙ ሊጠቀሙበት ይችላሉ፡፡
6.7K viewsWasyhun Belay, 16:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-15 19:32:40 መንግስት በየተቋማቱ #የመጨረሻዎቹን መሪዎች ማስቀመጥ አለበት!


ቢሮ ተቀምጠው ባለጉዳይ የሚያስተናግዱ የመንግስት ሰራተኞች እና ሃላፊዎች በሀገሪቷ ኢኮኖሚ ምርት እና ምርታማነት ላይ ተዘዋዋሪ ተጽኖ እንዳላቸው ሊረዱ ይገባል፡፡


#ለምሳሌ፡- ተቋማቶች የኢንቨስትመንት ፍቃድ ወይም የንግድ ፍቃድ ሂደቶች ላይ ፈጣን ምላሽ በመስጠታቸው በፍጥነት ስራ እንዲጀመር እና ምርት እንዲጨምር እንዲሁም የመንግስት ገቢ እንዲያድግ ማድረግ ይችላሉ፡፡


የተሾሙበትን ተቋም ራዕይ፤ ተልዕኮ እና ተግባር በመረዳት በእውቀት እና በድፍረት ሃላፊነት ወስደው የሚወስኑ የሚያሰሩ እና የሚሰሩ ሃላፊዎች ያሉበትን ያህል በየተቋሙ #አይሆንም፤ #አይቻልም እና #አይፈቀድም የሚል መልስ በግላቸው የሚሰጡ #ይሆናል የሚል መልስ ለመስጠት የመጨረሻ ሰው አለመሆናቸው የሚያሳዩ ብዙዎች ናቸው፡፡


#ለምሳሌ፡- በተቋማት የሆነ ጥያቄ እና አቤቱታ ይዞ ለሄደ ሰው ሃላፊዎች/ሰራተኞች ማንንም ሳያማክሩ #እንደማይቻል ሊናገሩ ይችላሉ! ስለዚህ የተቋሙ የመጨረሻ ሰው ማነው? ብላችሁ ስትሄዱ እሱም ለመወሰን እንዳልቻለ በኮሚቴ ወይም ከበላይ አካሎች ጋር አውርቼበት ምላሽ እሰጣለሁ ይላል፡፡


ማንንም ማማከር፤ ኮሚቴ ማዋቀር እና ከበላዮቹ ጋር ማውራት ሳያስፈልገው #አይሆንም! ያለ ሰው ይሆናል ወይም የማይሆነው በዚህ ምክንያት ነው ለማለት እንደመጨረሻ ሰው ሚና መውሰድ መከራ ነው፡፡


ለአንድ ጉዳይ ለዓመታት በተቋም የሚመላለሱ ሰዎች የመጨረሻ የሚባለውን ሰው ማግኘት ባለመቻላቸው ይቸገራሉ! ወረዳ መልስ አጥተው ክፍለ ከተማ የሄዱ፡ ክፍለ ከተማ መልስ አጥተው ከተማ የሄዱ፡ ሰዎችን ብትጠይቁ በየተቋሙ የመጨረሻ መሆን የነበረባቸው የተቋም ሃላፊዎች አግኝተዋቸዋል! ነገር ግን በውሳኔ እና ሃላፊነት በመውሰድ ረገድ የመጨረሻው ሰው መሆን ባለመቻላቸው የስራ ጫና/ተጠቃሚነት አንድ ቦታ እና ጥቂት ሰዎች ላይ እንዲጠራቀም ያደርጋል፡፡


በብዙ ተቋማት ለተለያዩ ጉዳዮች የመሄድ ልምድ አለኝ! በአብዛኛው ተቋማት ተቋማዊ አሰራር የመገንባት ልምምድ ብዙ ነው የሚቀረው፡፡ አንድ ሃገር ከድህነት ለመውጣት የመጀመሪያ የምትመከረው ተቋማዊ አሰራሮችን (Institutionalization) ለመገንባት እንድትሞክር ነው፡፡


ለአንድ ተቋም የሚያሰራ አዋጅ፤ ደንብ እና መመሪያ ከተዘጋጀ እሱን ተከትሎ የማስፈጸም እና የመፈጸም ሃላፊነት በየተቋሙ ያሉ ሃላፊዎች እና ሰራተኞች ድርሻ ነው፡፡ አንዳንዶች "ተገልጋይ መመሪያውን አያውቀውም" በሚል መነሻ አብዛኛውን የሚቻል ጉዳይ ቅንነት በማጣታቸው፤ ለሙስና እና በአቅም ማነስ ምክንያት "መመሪያው አይፈቅድም" በሚል ጥቅል መልስ ለረጅም ጊዜ ድህነት ቅነሳ ስርዓት ላይ የሚተኙ አሉ፡፡


#ለምሳሌ፡- በተቋማቸው ላይ ሃላፊ ሆነው እንደተወካይ ወይም ከላይ ላለው መዋቅር መልክተኛ ይመስል ተራ
ጉዳይ ሲቀርብላቸው ቆይ ከላይ ጉዳዩን ማብራሪያ ልጠይቅበት የሚሉ ብዙ ናቸው፡፡


አንዳንዶች አይሆንም ለሚል መልስ የተቀመጡ ይመስል ንግግራቸውን አይሆንም ከሚል ነው የሚጀምሩት #ለምሳሌ፡- ባለሙያ መልስ መስጠት ካልቻለ ቡድን መሪ፤ ቡድን መሪ መልስ ካልሰጠ ዳይሬክተር፤ ዳይሬክተር መልስ መስጠት ከተቸገረ የመጨረሻው በስልጣን ተዋረድ ሃላፊው ጋር ቀርቦለት መመለስ እንደማይችል በተለያየ ምክንያት ካሳየ በለውጥ ጥናቶች ስራን እና ሃላፊነትን ወደታች ማውረድ የሚለው የ Decentralization መርህ ዋጋ አጥቷል ማለት ነው፡፡


አንዳንድ ሰዎች በየተቋሙ "ሃላፊውን አሳዩኝ" ይላሉ ነገር ግን ሃላፊውም በተለያዩ ምክንቶች ለብቻው ምላሽ መስጠት እንደማይችል ያሳያል (ተገልጋዮች የየተቋማቱ ሃላፊዎች የመጨረሻ ሰዎች እንደሆኑ ያምናሉ፡ የየተቋማቱ ሃላፊዎች የመጨረሻዎቹ ሰዎች እንደሆኑ ቢያምኑም በተግባር ግን የመጨረሻ አይደሉም)፡፡


#ለምሳሌ፡- ከተማ ያሉ ሃላፊዎች ክፍለ ከተሞች መጨረስ የነበረባቸውን አለመጨረሳቸውን ይታዘባሉ! ክፍለ ከተሞች ወረዳ በራሱ አቅም መወሰን አለመቻሉን ይታዘባሉ! የሚገርመው ወረዳ ያሉ ተገልጋዮች ክፍለ ከተማ ቢሄዱ የተሻለ ምላሽ እንደሚያገኙ ይሰማቸዋል! ከተማ ቢሄዱ ደግሞ የተሻለ እንዲሁም ፈጣን ምላሽ እንደሚያገኙ ያምናሉ፡፡


ይህ ሁሉ የሚያሳየው በየተቋሙ ጉዳዮቻችንን የምንነግራቸው ሃላፊዎች የመጨረሻዎቹ ሰዎች መሆናቸውን እንዴት ማረጋገጥ እንችላለን? በተመሳሳይ መንግስት በየተዋረድ ያስቀመጣቸው የስራ ሃላፊዎች በተቋማቸው የመጨረሻዎቹ ሰዎች ለመሆን በእውቀት እና በነጻነት ብቁ መሆናቸውን ማረጋገጥ አለበት፡፡


በርግጥ አይሆንም መልስ ነው! ነገር ግን ጉዳዩን በአግባቡ ሳይረዱ ለአይሆንም መልስ መዘጋጀት ባለጉዳዮች ረጅም ጥበቃ በማድረግ ጊዚያቸውን እና መተማመናቸውን እንዲያጡ በማድረግ ድህነት ቅነሳን ያስተጓጉላል፡፡


#ማስታወሻ፦ አንዳንዶች ርዕስ ብቻ ያነባሉ፤ አንዳንዶች ምሳሌውን ብቻ ያነባሉ፤ ሌሎች ገረፍ አርገው በማንበብ ጀጅ ያረጋሉ፤ አንዳንዶች የላቀ ተጨማሪ ምልከታ ይሰጡኛል። እኔ የምመክረው የፅሁፉን Context በመረዳት Rational የሆነ ውይይት ብናካሂድ ነው።
5.2K viewsWasyhun Belay, 16:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-14 20:19:31 ዋጋ ንረት ከፍተኛ ሲሆን የገንዘብ የመግዛት አቅም ስለሚዳከም ሰዎች ገንዘባቸውን ምን ላይ ቢያውሉት ከቁጥጥራቸው ወጪ የሆነውን የዋጋ ንረት ችግር መቋቋም ይችላሉ?


ገንዘብ በዋለበት ቦታ ዋጋውን የመወሰን አቅም አለው! ስለዚህ ሁኔታ የሰራሁትን ትንተና

ተመልከቱ!



ገንዘብ በቤት ሲቀመጥ፤ በባንክ ሲቀመጥ፤ አክሲዮን/ቦንድ ሲገዛበት፤ ወርቅ ሲገዛበት፤ የውጪ ምንዛሬ ሲገዛበት እና ንግድ ሲጀመርበት ሊኖረው የሚችለውን ልዩነት ተመልከቱ!
5.5K viewsWasyhun Belay, 17:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-13 19:33:53
#መረጃ

"ለግል መገልገያ እንዲውሉ ወደ ሀገር የሚገቡ/የሚወጡ ዕቃዎች ሁኔታን የሚወስነው በሥራ ላይ ያለው መመሪያ (መመሪያ ቁጥር 51/2010) ለሕገ ወጥ ንግድ በር የከፈተ እና አገልግሎት አሰጣጡ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ያሳደረ በመሆኑ ዓለምአቀፍ አሠራሮችን በተከተለ አኳኋን መመሪያውን አሻሽል ማውጣት በማስፈለጉ" በሚል ምክንያት ለግል መገልገያ እንዲውሉ ወደ አገር የሚገቡ ወይም ከአገር የሚወጡ ዕቃዎችን ለመወሰን መመሪያ ቁጥር 923/2014 ከነሀሴ 12/2014 ጀምሮ ተፈፃሚ እንዲሆን በገንዘብ ሚኒስቴር የተሻሻለው መመሪያ ይፋ ወጥቷል፡፡

በቀደመው መመሪያ በርካታ የቁሳቁስ አይነቶች ወደ ሀገር ውስጥ ከቀረጥ ነጻ ለማስገባት የሚፈቅደው መመሪያ በተሻሻለው አዲሱ መመሪያ መጠኑን ወደሚከተለው ሰንጠረዥ አሳጥሯል፡፡ ሙሉ መመሪያውን ማንበብ ለምትፈልጉ ከታች አስቀምጫለሁ!
6.4K viewsWasyhun Belay, 16:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-12 18:54:56 አዲስ አበባ ውስጥ #ባስ በመጠበቅ ከሚጠፋው ጊዜ በላይ #ባስ_ውስጥ ሆኖ በመንገድ መዘጋጋት የሚጠፋው ጊዜ እየበለጠ ነው!


የትራንስፖርት ሁኔታ የሰዎች መጓጓዝ ማለት ብቻ ሳይሆን የገንዘብ እና ኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ፍጥነትን ይወስናል። ሰዎች በመንገድ መጨናነቅ መንገድ ላይ ዋሉ ማለት ከምርት ስርዓት ተቀነሱ ማለት ነው።


#ለምሳሌ፦ በአንድ ከተማ ውስጥ የመንገድ እንቅስቃሴን ለማስተካከል የትራንስፖርት አማራጮችን መጨመር፤  የመንገድ አማራጮችን ማስፋት ወይም የመንገድ እና የትራንስፖርት አጠቃቀም እና ስምሪትን ማስተካከል በተናጥል ወይም በአንድ ላይ ሊተገበሩ ይችላሉ።


ሁሉም አማራጮች ተገቢ ቢሆኑም በጣም የሚያዋጣውን መምረጥ ደግሞ ግድ ነው (Mitigate opportunity Cost)!


#ለምሳሌ፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር 110 አዳዲስ የአንበሳ አውቶቢሶችን 16.5 ሚሊዮን ዶላር በላይ ወጪ በማድረግ  ሥራ አስጀመረ እንዲሁም በሚቀጥሉት ሦስት ወራት 250 አዳዲስ አውቶቢሶች ወደ አገልግሎት የሚገቡ መሆናቸውን ገልጸዋል (ወጪው የአስተዳደሩ በጀት እና የዓለም ባንክ  ድጋፍ ነው)።


በርግጥ ከአገልግሎት እየወጡ ያሉ በርካታ አሮጌ ባሶች ያሉበት ከተማ በመሆኑ አዳዲስ ባሶች ግዢ መደረጉ መጥፎ አይደለም! ለጉዳዩ ትኩረት ለመስጠት እና ለመወያየት ያህል የሚከተለው ጥያቄ ቢነሳ....


#ጥያቄው! ለአዲስ አበባ ከተማ ለትራንስፖርት ሁኔታው ተቀዳሚ መፍትሄው ተጨማሪ 360 ባስ ነው? ወይስ የተለዋጭ መንገድ ማስፋፋት እና የመንገድ አጠቃቀም ስርዓት ማበጀት? የሚለው ነው።


360ዎቹ ባሶች የመንገድ መስፋፋት ሳይኖር እና የመንገድ እና የትራንስፖርት አጠቃቀም እና ስምሪት ላይ ሳይሰራ ወደ ስምሪት ሲገቡ ተጨማሪ Opportunity Cost አለመፍጠራቸውን ማረጋገጥ ተገቢ ነው።


የበጀት እና የውጪ ምንዛሬ እጥረት ባለበት ኢኮኖሚ ውስጥ ወሳኙ ነጥብ የሚከናወኑ ስራዎች የሚኖራቸው ፋይዳ በጣም አሳማኝ እና ተቀዳሚ (Significant) መሆናቸውን ማረጋገጥ ነው።
7.0K viewsWasyhun Belay, 15:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-12 17:38:10 በኑሮ ውድነት ወቅት ወጪያችንን እንዴት ማስተካከል እንደምንችል ያቀረብኩላችሁን

ተመልከቱ!
6.2K viewsWasyhun Belay, 14:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-10 21:46:42
2015 የስኬታችን ዓመት ይሁን!
መልካም አዲስ ዓመት!
6.2K viewsWasyhun Belay, 18:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-10 17:19:07 የአዲስ ዓመት እቅድ!

የሚለካ እና ያልተጋነነ እቅድ እንዴት ማቀድ ይቻላል? 2014 የነበራችሁበትን ደረጃ ካላወቃችሁ በ2015 ስለ መሻሻላችሁ ማረጋገጥ እንዴት ትችላላችሁ? ይህንን በተመለከተ የተዘጋጀውን ቪዲዮ ይመልከቱ!




6.0K viewsWasyhun Belay, 14:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-09 19:43:26 ለአዲስ ዓመት ስታቅዱ! #የሚለካ እና #ያልተጋነነ አድርጉት!


በ2014 ዓ.ም የነበራችሁን ኑሮ ላለመድገም ወጥራችሁ ለመስራት፤ ድፍረት የተሞላባቸው የለውጥ ውሳኔዎችን ለማድረግ (ሱስ መቀነስ፤ ስራ መቀየር፤ የስራ መነሻ ብድር መውሰድ፤ ጓደኞች መለወጥ፤ ወዘተ ሊሆን ይችላል)፤ ማህበራዊ ግንኙነታችሁን ለማሳደግ (ከነበራችሁ ውሎ ከፍ ማለት፤ ከሰዎች ጋር ያላችሁን የግንኙነት ዋጋዎችን/ምክንያታዊነት መለየት፤ ለአዳዲስ የቢዝነስ ሃሳቦች ጆሮ መስጠት፤ ወዘተ ሊሆን ይችላል) እና ገቢያችሁን እጥፍ ለማድረግ (የመጨረሻ የጉልበት፤ የማህበራዊ እና የእውቀት አቅማችሁን መጠቀም፤ ትንንሽ ብሮችን ማክበር፤ ገንዘብ እስካስገኘ ምንም መስራት፤ ወጪን ምክንያታዊ ማድረግ፤ ወደ ገቢ መቅረብ፤ የቢዝነስ መረጃ መሰብሰብ፤ ወዘተ ሊሆን ይችላል)፡፡


ስለዚህ ወስኑ! ጻፉት! እና ዓመቱን ጀምሩ! ከነበራችሁበት ጥቂትም ቢሆን ከፍ ለማለት ካቀዳችሁ #የሚለካ አድርጉት! ለተለምዶ ሲባል የውሸት አታቅዱ (ማቀድ ጥሩ ልምድ ነው! ለተነሳሽነት ምክንያት መሆን ይችላል!)።


እኔ ውስብስብ እና የማይለካ እቅድ ኖሮኝ አያውቅም! ከላይ የጻፍኩት በየዓመቱ ማስታወሻዬ ላይ እጽፈው የነበረውን ነው፡፡ #ለምሳሌ፡- የዚህን ያህል ብር በዓመት ለማግኘት ብዮ አቅዳለሁ ለሱ አቅሜን አሟጥጬ መስራት ነው፡፡ የጻፍኩትን እቅድ በመጨረሻ ደምሬ ቀንሼ ውጤቱን የመለካት ልምድ አለኝ (ሁሉም ነገር ባይለካም ነገር ግን ከነበረበት መለወጡን አረጋግጣለሁ!)፡፡ 


ምን አልባት ከተሳካልኝ ስራ መቀየር፤ ምን አልባት ከተሳካልኝ ማግባት፤ ምን አልባት ከተሳካልኝ ልጅ መውለድ፤ ምን አልባት ከተሳካልኝ ቤት/መኪና መግዛት፤ ምን አልባት ከተሳካልኝ አዲስ ስራ መጀመር፤ ምን አልባት ከተሳካልኝ ውጪ ሃገር መሄድ፤ ወዘተ እቅድ መሆን አይችልም፡፡ እቅዱ በራሱ ለመሳካት የሌሎችን ሃይል የሚፈልግ ይመስላል፡፡


ምኞት ያላችሁን እና መፍጠር የምትችሉትን አቅም መነሻ በማድረግ ካልታቀደ ተስፋ እንድትቆርጡ ያደርጋል። ስለዚህ አሁን ባለኝ አቅም ምን ማድረግ እችላለሁ? እና የመጨረሻ በዙሪያዬ የሚኖርን የመጨረሻ አቅም አሰባስቤ ብጠቀም ምን ልሰራ እችላለሁ? የሚለውን በደንብ ለዩ!


#ለምሳሌ፡- አንድ ሰው እቅዴ በ2015 ዓ/ም የተሻለ ኑሮ ለመኖር የሚል በደፈናው ቢያቅድ ልክ ሊሆን አይችልም! የተሻለ ኑሮ፤ የተሻለ ስራ፤ የተሻለ ህይወት የሚል መለኪያ የለም፡፡ ካቀዳችሁ #የሚለካ እና #ያልተጋነነ አድርጉት!
6.4K viewsWasyhun Belay, 16:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ