Get Mystery Box with random crypto!

AddisWalta - AW

የቴሌግራም ቻናል አርማ waltatveth — AddisWalta - AW A
የቴሌግራም ቻናል አርማ waltatveth — AddisWalta - AW
የሰርጥ አድራሻ: @waltatveth
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 45.24K
የሰርጥ መግለጫ

This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.
For more updates please visit https://shorturl.at/ehosX https://www.youtube.com/c/WaltaTV/featured

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 12

2023-04-27 14:27:20
ሰላም የእንደዋልታ ቤተሰቦች በየአካባቢያችሁ የምታዩዋቸውን የህግ ጥሰቶች እና ማናቸውንም እሴቶቻችንን ይንዳሉ ተብለው የሚታሰቡ ድርጊቶችን ማለትም በየአካባቢው መፀዳዳት ፤ ቆሻሻ መጣል ፤ በተከለከሉ ቦታዎች መኪና ማቆም ፤ የህፃናት ጉልበት መበዝበዝ ፤ ህገወጥ ግብይቶችና የመሳሰሉትን ተገቢ ያልሆኑ ተግባራትን በፎቶግራፍ ወይም በቪዲዮ ከስር ባለው የቴሌግራም ገፃችን ይላኩልን፡፡ እኛም መልሰን ወደ እርስዎ እናቀርባለን::
https://t.me/endewalta
212 views11:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-27 12:04:45
የቀን 6፡00 ዜና ከ #ዋልታ_ቴቪ በቀጥታ ሚያዝያ 19/2015https://fb.watch/k9YTnuvATd/
1.4K views09:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-27 10:13:38
አርጀንቲና ከቻይና ለምታስገባቸው ምርቶች በዶላር ሳይሆን በዩዋን ልትከፍል ነው
ሚያዚያ 19/2015 (ዋልታ) አርጀንቲና ከቻይና ለምታስገባቸው ምርቶች በዶላር ሳይሆን በቻይና መገባበያ በዩዋን ልትከፍል መሆኑን የሀገሪቱ የኢኮኖሚ ሚኒስትር ሰርጂዮ ማሳ ገለጹ፡፡
ውሳኔውም እየቀነሰ የመጣውን የአርጀንቲናን የዶላር ክምችት ለማቃለል ያለመ መሆኑ ተነግሯል፡፡
አርጀንቲና በሚያዝያ ወር ብቻ ወደ 1 ቢሊየን ዶላር ግምት ያላቸው የቻይና ምርቶችን በዩዋን ለመክፈል ያቀደች ሲሆን በቀጣይ በየወሩ ወደ 790 ሚሊዮን ዶላር የሚጠጋ ግምት ያላቸው ምርቶችን በዩዋን እንደምትከፍልም ተጠቁሟል፡፡
ቻይና ከዶላር ውጭ የንግድ ልውውጥ ሥምምነት ከሩሲያ፣ ፓኪስታን፣ ብራዚል እና ሌሎች በርካታ ሀገራት ጋር ማድረጓ ይታወቃል፡፡
2.2K views07:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-27 09:58:36
በብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አደም ፋራህ የተመራ የክልል ርዕሳነ መስተዳደሮች ልዑክ ወደ መቀሌ ገቡ
ሚያዚያ 19/2015 (ዋልታ) በብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አደም ፋራህ የተመራ የክልል ርዕሳነ መስተዳደሮች ልዑክ ወደ መቀሌ ገብተዋል።
የሁሉም ክልል ርዕሰ መስተዳደሮቹ እና የአዲስ አበባና የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባዎች በመቀሌ አሉላ አባነጋ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር የስራ ኃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች እና የመቀሌ ከተማ ነዎሪዎች ደማቅ አቀባበል አድርገውላቸዋል።
የርዕሳነ መስተዳደሮቹ የመቀሌ ጉዞ ለትግራይ ክልል አጋርነታቸውን ለማሳየት እና በመልሶ ግንባታ ሂደት የድርሻውን ለማበርከት ዓላማ ያደረገ ነው።
የክልል ርዕሳነ መስተዳደሮች፣ የአዲስ አበባ እና የድሬዳዋ ከተማ ከንቲባዎች ወደ መቀሌ ሲያቀኑ ከሰላም ስምምነቱ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው ሲል የዘገበው ኢቢሲ ነው።
ከሰሞኑ በወዳጅነት አደባባይ በተካሄደው ‘ጦርነት ይብቃ፤ ሰላምን እናፅና’ በሚል መሪ ቃል በተካሄደ መርሐ ግብር ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች በመቀሌ ጉብኝት እንደሚያደርጉ መናገራቸው ይታወሳል።
2.1K views06:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-27 09:26:41
በብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አደም ፋራህ የተመራው የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮችና ባለስልጣናት የተካተቱበት ቡድን ወደ መቀሌ ተጓዘ
ሚያዚያ 19/2015 (ዋልታ) በብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አደም ፋራህ የተመራና የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮችና ሌሎች ባለስልጣናት የተካተቱበት ቡድን ወደ መቀሌ ተጓዘ።
በቡድኑ ውስጥ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ፣ የአፋር ክልል፣ የኦሮሚያ ክልል፣ የደቡብ ክልል፣ የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል፣ የጋምቤላ ክልል፣ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል፣ የሶማሌ ክልል፣ የሲዳማ ክልል ይገኙበታል።
በተጨማሪም የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ የድሬዳዋ ከተማ ከንቲባ ከድር ጁሀርና ሚኒስትሮች እና ሌሎች የሥራ ኃላፊዎች አብረው መጓዛቸውን የዘገባው ኢ.ፕ.ድ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ለሰሜኑ ጦርነት የሠላም ስምምነት አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት የዕውቅና መርሀ-ግብር ሲከናወን የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች ወደመቀሌ በማቅናት መቀራረቡን እንዲያጠናክሩ ተናግረው እንደነበር የሚታወስ ነው።
2.1K views06:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-27 09:06:20
እንደምን አደርሽ ኢትዮጵያ ከ #ዋልታ_ቴቪ ሚያዝያ 19/2015https://fb.watch/k9OoqarDdu/
2.1K views06:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-26 19:49:03

3.6K views16:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-26 19:21:58

3.5K views16:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-26 19:10:14
የአውሮፓ ህብረት ምክር ቤት ከኢትዮጵያ ጋር ያለውን ግንኙነት ለማደስ እና ሀገሪቱን ለማገዝ መወሰኑን ኢትዮጵያ በበጎ እደምታየው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ

ሚያዚያ 18/2015 (ዋልታ) የአውሮፓ ህብረት ምክር ቤት ኢትዮጵያ በፕሪቶሪያ የተፈረመውን የሰላም ስምምነት ተግባራዊ በማድረግ ረገድ ትልቅ እምርታ ማስመዝገቧን እ.ኤ.አ ሚያዚያ 24 ቀን 2023 መግለጫ ማውጣቱን ጠቅሶ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

ኢትዮጵያ ከህብረቱ ጋር ያላትን ግንኙነት ለማጠናከር ብዙ ጥረት ስታደርግ መቆየቷን እና ይህ የህብረቱ ውሳኔም ወደላቀ ደረጃ ከፍ እንደሚያደርገው ሚኒስቴሩ ጠቅሷል፡፡

ህብረቱ መደበኛውን የባለብዙ- አመላካች አመታዊ ፕሮግራምን እንደገና ለማንቀሳቀስ መወሰኑ፣ አለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ የማረጋጋት ጥረት እንዲደግፉ ማበረታታቱን እና አበዳሪ ተቋማትም የእዳ አከፋፈል ሽግሽግ እንዲያደርጉ ጥሪ ማድረጉን ኢትዮጵያ በበጎ እንደምትቀበለው አስታውቋል፡፡

ኢትዮጵያ ሰላሟን በማጠናከር፣ በጦርነቱ የተጎዳውን የህብረተሰብ ክፍል መልሶ በተማቋቋም፣ ኢኮኖሚያዊ ማሻሻያዎችን እና የአየር ንብረት ለውጥን ሊቋቋም የሚችል እድገትን ለማሳካት ጥረት በምታደርግበት ወቅት ወዳጅ አገሮች ግንኙነታቸውን እያጠናከሩ መሆናቸውንም መግለጫው ያመለክታል፡፡

የአውሮፓ ህብርት ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ፣ በቀይ ባህር እና አካባቢው ቁልፍ ስትራቴጂካዊ አጋር መሆኗን እና አገሪቱ ወደ ዘላቂ ሰላም የምታደርገውን ጉዞ ለመደገፍ ዝግጁ መሆኑን ከትናንት በስቲያ ባወጣው መግለጫ አመላክቷል።
3.1K views16:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-26 19:04:47
ዋልታ ምሽት ከ #ዋልታ_ቴቪ በቀጥታ ሚያዝያ 18/2015
https://fb.watch/k91hKfHzW9/
2.8K views16:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ