Get Mystery Box with random crypto!

Walta

የቴሌግራም ቻናል አርማ walta_tv_eth — Walta W
የቴሌግራም ቻናል አርማ walta_tv_eth — Walta
የሰርጥ አድራሻ: @walta_tv_eth
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 8
የሰርጥ መግለጫ

This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.
For more updates please visit https://www.facebook.com/waltainfo
#ሼር #በማድረግ_አጋርነታችሁን_አሳዩን

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2022-09-04 16:52:33
አሸባሪው ሕወሓት በጭና ንፁሃን ወገኖችን የጨፈጨፈበት 1ኛ ዓመት መታሰቢያ እየተካሄደ ነው

ነሐሴ 29/2014 (ዋልታ) አሸባሪው ሕወሓት በሰሜን ጎንደር ዞን ጭና ንፁሃን ወገኖችን በግፍ የጨፈጨፈበት የ1ኛ ዓመት የመታሰቢያ ዝግጅት በጭና እየተካሄደ ነው።

በመታሰቢያ ዝግጅቱ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል ከፋለ (ዶ/ር)፣ የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል፣ ሌሎች የመንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችና የመከላከያ ሠራዊት ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል ሲል አሚኮ ዘግቧል፡፡

ለፈጣን መረጃዎች፦
ፌስቡክ https://bit.ly/3Ma7QTW
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
ዩቲዩብ https://www.youtube.com/c/WaltaTV/featured
ቲዊተር https://twitter.com/walta_info
አብራችሁን ስለሆናችሁ እናመሰግናለን!
606 views13:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-04 16:52:33
በክልሉ በተከናወኑ የሠላምና ጸጥታ ሥራዎች ላይ ምክክር እየተካሄደ ነው

ነሐሴ 29/2014 (ዋልታ) በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በተከናወኑ የሠላምና ጸጥታ ሥራዎች ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ እየተካሄደ ነው።

የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰንን ጨምሮ የክልል የሁሉም ዞኖች፣ ከተማ አስተዳደር፣ የፌዴራልና የክልል የጸጥታ ከፍተኛ አዛዦች በተገኙበት ነው ምክክሩ እየተካሄደ የሚገኘው።

በክልሉ ባለፉት ወራት በሶስቱም ዞኖች፣ በማኦና ኮሞ ልዩ ወረዳ፣ በአሶሳ ከተማ አስተዳደር የተከናወኑ የሠላምና የጸጥታ ሥራዎች ቀርበው እንደሚገመገሙ ተጠቁሟል

ከክልሉ ኮሙዩኒኬሽን ያገኘነው መረጃ እንዳመላከተው በቀጣይ የክልሉን ሠላምና ጸጥታ የበለጠ ለማጠናከር የሚያስችሉ የቀጣይ አቅጣጫዎች በመድረኩ እንደሚቀመጡ ይጠበቃል፡፡

ለፈጣን መረጃዎች፦
ፌስቡክ https://bit.ly/3Ma7QTW
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
ዩቲዩብ https://www.youtube.com/c/WaltaTV/featured
ቲዊተር https://twitter.com/walta_info
አብራችሁን ስለሆናችሁ እናመሰግናለን!
765 views13:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-04 10:26:32
የሕወሓትን የመከፋፈል ሴራ ለማክሸፍ እንደሚሰሩ የዞን አመራሮች ገለጹ

ነሐሴ 29/2014 (ዋልታ) የአሸባሪውን ሕወሓት የመከፋፈል ድብቅ ሴራ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ በመቅበር ለሕዝቦች የጋራ ተጠቃሚነት ትኩረት ሰጥተው እንደሚሰሩ የምዕራብ ጉጂ ዞን እና የጌዴኦ ዞን ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ገለጹ፡፡

የጉጂ እና የጌዴኦን የሕዝብ ለሕዝብ ትሥሥርን ለማጎልበት በማሰብ በምዕራብ ጉጂ ዞን የገላና ወረዳ ብልጽግና ጽህፈት ቤት ከአባላቱ በሰበሰበው ገንዘብ በጌዴኦ ዞን ኮቾሬ ወረዳ አንጨቢ ቀበሌ በድንበር ተሻጋሪ የበጎ ሥራ ፈቃድ አገልግሎት የአቅመ ደካማ ቤቶችን ማደስና መስራት ጅምሯል፡፡

መርኃ ግብሩ በኦሮሞ ጉጂ እና በጌዴኦ ሕዝቦች መካከል እውነተኛ ሠላም እንዲፈጠርና የቀደመው ቁርሾ በሁለቱም ወገኖች እንዲረሳ የተዘጋጀ መሆኑን ከገላና ወረዳ ኮሙዩኒኬሸን ያገኘነው መረጃ አመላክቷል፡፡

ለፈጣን መረጃዎች፦
ፌስቡክ https://bit.ly/3Ma7QTW
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
ዩቲዩብ https://www.youtube.com/c/WaltaTV/featured
ቲዊተር https://twitter.com/walta_info
አብራችሁን ስለሆናችሁ እናመሰግናለን!
2.8K views07:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-04 10:26:32
"የተከፈተብንን ጦርነት በጀግንነት እየመከትን የግብርና ሥራችን ተጠናክሮ ይቀጥላል!" - አማራ ክልል

ነሐሴ 29/2014 (ዋልታ) አሸባሪው ህወሓት ይህን ወቅት ለጦርነት የሚመርጠው የሀገሪቱ የኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት የሆነው የግብርና ዘርፉን ሆን ብሎ ለማዳከም ጭምር መሆኑን የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ ገለጸ።

አርሶ አደሩን ከግብርና ሥራው አስተጓጉሎ ሕዝብን ለማስራብ እና ኅልውናውን ለማጥፋት፤ ኢትዮጵያን ደግሞ እንደ ሀገር በኢኮኖሚ ደካማ አድርጎ ራሷን መከላከል እንዳትችል በማድረግ ሀገሪቱን ለማፍረስ አስቦ የፈፀመው ጥቃት ነው ብሏል።

አክሎም፣ ይህን የጥፋት ተልዕኮ ለመመከት ጥምር ጦሩ በጀግንነት እየመከተ ይገኛል መላው ሕዝቡም ደጀንነቱን እያሳየ መሆኑን ገልጿል።

"ሌላኛው የህልውና የፍልሚያ ግንባር የግብርና ልማት በመኾኑ፤ በዚሁ ግንባር የተሰለፋችሁ አመራሮች፣ ባለሙያዎችና መላው አርሶ አደሮች በእልህና በቁጭት ያለንን አቅም ሁሉ ተጠቅመን በሰብል ጥበቃ በተለይ አረም ማረምና ተባይ አሰሳ ማድረግ፤ የተተከሉ ችግኞች መንከባከብ፤ በቀሪ እርጥበት ለሚዘሩ ሰብሎች ትኩረት መስጠት፤ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ኮምፖስት ዝግጅት አጠናክሮ መቀጠል፤ ለቀጣይ ዓመት መስኖ ልማት ቅድመ ዝግጅት ማድረግና ሌሎች ስራዎች ላይም ከፍተኛ ርብርብ ማድረግ አለብን" ሲል ቢሮው አሳስቧል።

ምንጊዜም ቢሆን ፈተና ውስጥ ብንሆን፤  ችግር ቢያጋጥመን፤ ጦርነት ቢታወጅብን በጀግንነት እየተፋለምን ፤በፅናት እየመከትን ከግብርና ሥራችን ለአፍታም ቢሆን አይናችንን አንነቅልም ሲል ቢሮው በማህበራዊ ትስስር ገጹ አስታውቋል።

ለፈጣን መረጃዎች:-
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth

አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን!
2.4K views07:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-03 15:10:23
ለውጭ ተላላኪ ባንዳዎች ኢትዮጵያን አሳልፈን አንሰጥም -  የዳማ ወረዳ ነዋሪዎች

ነሐሴ 28/2014 (ዋልታ) ለውጭ ተላላኪ ባንዳዎች ኢትዮጵያን አሳልፈን አንሰጥም ሲሉ በጉጂ ዞን የዳማ ወረዳ ነዋሪዎች ገለጹ።

በዞኑ የተለያዩ ወረዳዎች አሸባሪዎቹን የትሕነግና ሸኔ ቡድኖች የሚያወግዝ ሰልፍ እየተካሄደ ይገኛል።

ሰልፉ እየተካሄደባቸው ከሚገኝባቸው ወረዳዎች አንዷ ዳማ ስትሆን ሀገራችን ኢትዮጵያን ለውጭ ተላላኪ ቡድኖች አሳልፈን አንሰጥም ሲሉ በሰልፉ የተሳተፉ የወረዳዋ ነዋሪዎች ተናግረዋል።

አሸባሪ ቡድኖቹ ትሕነግና ሸኔ ሰዋዊ መንፈስ የሌላቸውና ለጥፋት ብቻ የተፈጠሩ መሆናቸውን የሚያነሱት የወረዳ አስተዳዳሪ ታሪካየው ተስፋዬ እነዚህን ቡድኖች ከስር በመንቀል ማጥፋት እንደሚገባ ገልጸዋል።

አሸባሪዎችን ድል አድርጎ የሀገርን ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ ህይወቱን እስከ መስጠት እየተዋጋ የሚገኘውን የመከላከያ ሰራዊታችንን መደገፍና ማበረታታት ያስፈልጋልም ብለዋል።

እንደ ዳማ ወረዳም በአንድ ቀን ብቻ የምግብ እህልን ጨምሮ 43 በሬዎችንና ከ63 በላይ በጎችን ለመከላከያ ሰራዊት ከማህበረሰቡ መሰብሰብ መቻሉንም ተናግረዋል።

ድጋፉ በዚህ አያበቃም የሚሉት አስተዳዳሪው ደም መስጠትን ጨምሮ ለመከላከያ ሰራዊታችን አስፈላጊ የሆኑ ቁሶችን በሙሉ እንደሚያደርጉም ለዋልታ ቴሌቪዥን ገልፀዋል።

እኛ በሰላም እንድንኖርና እንድንቀሳቀስ መከላከያ ሰራዊታችን በዱር በገደሉ እየተዋደቀ ነው የሚሉት የዳማ ወረዳ ነዋሪዎች ሁሌም ከሰራዊታችን ጎን ነን ብለዋል።

ታምራት ደለሊ (ከጉጂ ዞን ዳማ ወረዳ)

ለፈጣን መረጃዎች:-
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth

አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን!
3.3K views12:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-03 15:10:22
የሚኒስትሮች ምክር ቤት የባንክ ዘርፍን ለውጭ ኢንቨስተሮች ክፍት ለማድረግ በቀረበ ረቂቅ ፖሊሲ ላይ ውሳኔ አሳለፈ

ነሐሴ 28/2014 (ዋልታ) የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 13ኛ መደበኛ ስብሰባ የባንክ ዘርፍን ለውጭ ኢንቨስተሮች ክፍት ለማድረግ በቀረበ ረቂቅ ፖሊሲ ላይ ተወያይቶ ውሳኔ ማሳለፉን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት መረጃ አመላክቷል፡፡

ለፈጣን መረጃዎች:-
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth

አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን!
2.8K views12:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-03 15:10:22
10 ሺሕ ሐሰተኛ ብር ይዞ የተገኘ ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ

ነሐሴ 28/2014 (ዋልታ) በጎዳና ላይ የንግድ ተግባር ሲያከናውን የነበረ ግለሰብ 10 ሺሕ ሐሰተኛ ብር ይዞ በመገኘቱ በቁጥጥር ሥር ውሎ ምርመራ እየተጣራበት እንደሚገኝ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ።

ተጠርጣሪው በቁጥጥር ስር የዋለው በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 9 ልዩ ቦታው መገናኛ ተርሚናል አካባቢ ነው።

ፖሊስ እንደገለፀው ግለሰቡ በአካባቢው ላይ የጎዳና ላይ ንግድ የሚሰራ ሲሆን ኅብረተሰቡ በጥርጣሬ የተመለከተውን ጉዳይ ለፖሊስ ጥቆማ በመስጠቱ በወንጀል መከላከል ሥራ ላይ በነበሩ የፖሊስ አባላት ሊያዝ ችሏል።

በግለሰቡ ላይ በተደረገ ፍተሻም በባለ ሁለት መቶ የብር ኖት 10 ሺሕ ሐሰተኛ ብር ይዞ ተገኝቷል።

በበዓላት ወቅት የሚኖረውን ግብይት እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም ሐሰተኛ ገንዘብ ለማዘዋወር የሚደረጉ እንቅስቃሴዎችን ለመግታት ፖሊስ የቁጥጥር እና ክትትል ስራ እያከናወነ መሆኑን ገልጿል።

ነጋዴውም ሆነ ሸማቹ የኅብረተሰብ ክፍል ይህን የክትትል ሥራ በመደገፍ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እያደረገ አጠራጣሪ ጉዳዮች ሲገጥሙት ለፀጥታ አካላት ጥቆማ እንዲሰጥ ፖሊስ ጥሪውን አቅርቧል።

ለፈጣን መረጃዎች:-
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth

አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን!
2.6K views12:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-03 15:10:22
ምርጫ ቦርድ የፖለቲካ ፓርቲዎች በአካባቢ ምርጫ ላይ በንቃት እንዲሳተፉ  ጠየቀ

ነሐሴ 28/2014 (ዋልታ) የፖለቲካ ፓርቲዎች በአካባቢ ምርጫ ላይ በንቃት እንዲሳተፉ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጠይቋል።

ምርጫ ቦርድ ለአምስተኛ ጊዜ በሚካሄደው የአካባቢ ምርጫ የሕግ ማዕቀፍ እና አፈጻጸም ላይ ያስደረገውን ጥናት አስመልክቶ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ምክክር አካሂዷል።

ጥናቱ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፌዴራሊዝም እና የአስተዳደር ጥናት ማዕከል የተደረገ ሲሆን የአካባቢ ምርጫ አስፈላጊነት ተመላክቶበታል።

በኢትዮጵያ የአካባቢ ምርጫን ለማካሄድ ያለው የሕግ ማዕቀፍ በጥናቱ የተመላከተ ሲሆን ክልሎች ሕገ-መንግሥቱን መሠረት በማድረግ በተለያዩ ጊዜ ምርጫ ማካሄዳቸው በጥናቱ ተነሥቷል።

በኢትዮጵያ ቀደም ሲል 4 የአካባቢ ምርጫዎች የተካሄዱ ሲሆን የመጨረሻው ከተካሄደ ከ9 ዓመት በላይ እንዳስቆጠረ ተገልጿል።

5ኛውን የአካባቢ ምርጫ ከክልሎች ጋር በመነጋገር በ2015 ዓ.ም እንደሚደረግም የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ብርቱካን ሚዴቅሳ መናገራቸውን ኢብኮ ዘግቧል።

የአካባቢ ምርጫ የብሔረሰብ፣ የዞን፣ የወረዳ እና የቀበሌ ምክር ቤቶች አባላት ምርጫ የሚካሄድበት እንደሆነ በምርጫ ህጉ ተቀምጧል።

ለፈጣን መረጃዎች:-
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth

አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን!
2.4K views12:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-03 15:10:22
የዳውሮ ብሔር ዘመን መለወጫ "ቶክ ቤኣ" በዓል እየተከበረ ነው

ነሐሴ 28/2014 (ዋልታ) የዳውሮ ብሔር ዘመን መለወጫ "ቶክ ቤኣ" በዓል በዞን ደረጃ እየተከበረ ነው።

የዳውሮ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ምትኩ መኩሪያ (ዶ/ር) በአከባበሩ ወቅት ባደረጉት ንግግር "ቶክ ቤኣ" በዓል በዓለም የማይዳሰሱ ቅርሶች ውስጥ እንዲመዘገብ ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ ጠይቀዋል።

በዓሉ ከዳውሮ ብሔር ማንነት መገለጫ ከሆኑ የባህል እሴቶች አንዱ እንደሆነ የገለጹት ዋና አስተዳዳሪው መጠበቅና መልማት ይገባልም ብለዋል።

የዳውሮ ዞን ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ ኃላፊ ዳዕሞ ደስታ በበኩላቸው "ቶክ ቤኣ" ከሀገሪቱ ብዝሀ ባህሎች አንዱ መሆኑን ገልፀው በዓሉ ለሀገርቱ የቱሪዝም ዕድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ተናግረዋል።

በበዓሉ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍል ተወካዮች፣ የባህል አምባሳደሮች፣ አርቲስቶች፣ የዘርፉ ምሁራን፣ የሁሉም ወረዳና ከተማ አስተዳደር አስተዳደር የባህል ልዑካኖች፣ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎችና ለሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች መገኘታቸውን የዞኑ ኮሙዩኒኬሽን የላከልን መረጃ አመላክቷል።

ለፈጣን መረጃዎች:-
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth

አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን!
2.3K views12:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-03 15:10:22
ኢትዮጵያ አሁንም ሰላምን ትመርጣለች - አምባሳደር ስለሺ በቀለ

ነሐሴ 28/2014 (ዋልታ) አሸባሪው ህወሓት በአስር ሺሕዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን በማሰለፍ ጦርነቱን ቢጀምረውም ኢትዮጵያ አሁንም ለሰላም እጇን ዘርግታለች ሲሉ  በአሜሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደር  ስለሺ በቀለ ገለጹ።

አምባሳደር ስለሺ በቀለ (ዶ/ር) በወቅታዊ ጉዳዮች ዙርያ ከሲ ኤንኤን ጋር ባደረጉት ቆይታ አሸባሪው ህወሓት  ለሰላም ምንም አይነት ፍላጎት ካለማሳየቱም በላይ ጦርነቱ እንዲጀመር ስለሚፈልግ ትንኮሳውን ጀምሯል ብለዋል።

ኢትዮጵያ ወደ ግጭቱ የገባችው አሸባሪው ህወሓት የሰው ማእበል በማሰለፍ በአማራና በአፋር ክልሎች ላይ ጉዳት ማድረስ በመጀመሩ ነው ብለዋል።

ካለፈው መጋቢት ጀምሮ የኢትዮጵያ መንግስት ሰብአዊነትን በማስቀደም ተናጥላዊ የተኩስ አቁም ማወጁን ያስታወሱት አምባሳደሩ አዋጁን ተከትሎም ኢትዮጵያ ከሽብር ቡድኑ ጋር ለሚደረገው የሰላም አማራጭ ተሳታፊዎች ማዘጋጀቷን አንስተዋል።

በትግራይ ክልል ለሚገኙ ተረጅዎች እንዲደርስ በሚልም በኢትዮጵያ በኩል በርካታ ተግባራት ሲከናወኑ እንደነበር ገልጸው መንግስት የምግብና የመድሃኒት እንዲሁም የእርዳታ ስርጭቱን ለማፋጠን የሚያግዙ የነዳጅና የስልክ  አቅርቦት እንዲኖር ማስቻሉን ተናግረዋል።

የአለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር በአፋርና በአማራ ክልል ስለወደሙ መሰረተ ልማቶች ከበቂ በላይ ማስረጃዎች እያላቸው ዝምታን ስለመምረጣቸው ያሰመሩበት አምባሳደሩ የኢትዮጵያ መንግስት በህዝብ ተሳትፎ የተመረጠ በመሆኑ በሁሉም የሃገሪቱ ጫፍ ላሉ ኢትዮጵያውያን ኃላፊነት እንዳለበት ይታወቃል ብለዋል።
ለፈጣን መረጃዎች:-
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth

አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን!
2.7K views12:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ