Get Mystery Box with random crypto!

Walta

የቴሌግራም ቻናል አርማ walta_tv_eth — Walta W
የቴሌግራም ቻናል አርማ walta_tv_eth — Walta
የሰርጥ አድራሻ: @walta_tv_eth
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 8
የሰርጥ መግለጫ

This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.
For more updates please visit https://www.facebook.com/waltainfo
#ሼር #በማድረግ_አጋርነታችሁን_አሳዩን

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-09-06 17:18:22
የጠ/ሚ ጽህፈት ቤት የበጎነት ቀንን ምክንያት በማድረግ የበዓል ስጦታ አበረከተ

ጳጉሜ 1/2014 (ዋልታ) የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የበጎነት ቀንን ምክንያት በማድረግ የበዓል ስጦታ አበረከተ፡፡

ስጦታው የተበረከተላቸው ጽህፈት ቤቱ ለሚያሳድጋቸው 35 ልጆችና ዝቅተኛ ደመወዝ ላላቸው 119 የፅህፈት ቤቱ ሰራተኞች እንደሆነ ተገልጿል፡፡

የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ኃላፊ እና የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር ተፈሪ ፍቅሬ የበጎነት ቀንን በማስመልከት የተበረከተው ስጦታ ለአዲስ ዓመት እንኳን አደረሳችሁ ለማለት እንደሆነ ገልፀዋል፡፡

በጎነት ከአመለካከት የሚነሳ በመሆኑ ሁሉም ባህሉ ሊያደርገው እንደሚገባና ቀኑን ጠብቆ ሳይሆን የዘውትር ተግባራችን መሆን ይገባዋልም ብለዋል፡፡
ለፈጣን መረጃዎች:-
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth

አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን!
2.8K views14:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-06 17:18:22
በመከላከያ ሠራዊቱ የደረሰብን ምት መቋቋም አልቻልንም - ምርኮኞች

ጳጉሜ 1/2014 (ዋልታ) "በኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የደረሰብን ምት ፈፅሞ የምንቋቋመው አልሆነም ሲሉ በሰቆጣ ግምባር እጃቸውን የሠጡ የአሸባሪው ህወሓት ታጣቂዎች ገለጹ፡፡

ምርኮኞቹ አያይዘውም ብዙዎች ከአጠገባችን ተደምስሰውብናል፣ አመራሮቻችንም ሞተዋል የተረፉትም ሸሽተዋል በማለት ተናግረዋል፡፡

ጉዕዲ ገ/ኪዳን በሠቆጣ ግምባር እጃቸውን ለመከለከያ ሠራዊት ከሰጡ የአሸባሪው ህወሓት ታጣቂዎች መካከል አንዷ ስትሆን አማራን መደምሰስ አለብን የሚል ተልዕኮ እንደተሰጣቸውም ተናግራለች።

በትግራይ ክልል ውስጥ ከፍተኛ አፈና እና የመብት ጥሰት በአሸባሪ ቡድኑ ታጣቂዎች እየተደረገ መሆኑን የገለጸችው ጉዕዲ ምንም እንኳን የጦርነት ፍላጎት ባይኖራትም በቤተሰቦቿ ላይ የሚደርሰውን ወከባ እና እንግልት ላለማየት አሸባሪውን ቡድን መቀላቀሏን ገልፃለች።

ሌላኛው ምርኮኛ ኤልያስ ገብረፃዲቅ የሦስት ወንድ እና የአንድ ሴት ልጅ አባት ሲሆን ከሚሰራበት ቦታ በሽብር ቡድኑ ታጣቂዎች ተገዶ ወደ ማሰልጠኛ እንደተወሰደ መናገሩን የመከላከያ ሰራዊት መረጃ አመልክቷል።

ለፈጣን መረጃዎች:-
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth

አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን!
2.3K views14:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-06 17:18:22
ሚኒስቴሮቹ የበጎ ፈቃደኝነት ቀን በጋራ እያከበሩ ነው

ጳጉሜ 1/2014 (ዋልታ) የጤና፣ የትምህርት እንዲሁም የስራና ክህሎት ሚኒስቴሮች የበጎ ፈቃደኝነት ቀንን በጋራ እያከበሩ ነው፡፡

ሚኒስቴሮቹ በጋራ የሚያዘጋጁት የሙሉ ቀን መርኃ ግብር በሚኒሊክ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ እና የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት በተለያዩ ዝግጅቶች ተጀምሯል።

የትምህርት ተቋማትን ፅዱና ውብ በማድረግ እንደዚሁም የተተከሉ ችግኞችን በማረም፣ በመኮትኮት እና በመንከባከብ ነው መርኃ ግብሩ እየተካሄደ ያለው።

በመርኃ ግብሩ ላይ የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ፣ የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር)  እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

መርኃ ግብሩ ለ2015 የትምህርት ዘመን የትምህርት ተቋማት ለተማሪዎች ምቹ፣ ፅዱ፣ ውብና ማራኪ እንዲሁም ሳቢ እንዲሆኑ እና ለመማር ማስተማሩ ሂደት ጉልህ ሚና እንዲኖራቸው ለማድረግ የሚያስችል እንደሆነ መገለፁን የትምህርት ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።

ለፈጣን መረጃዎች:-
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth

አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን!
2.3K views14:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-06 11:43:58
ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ ለአቅመ ደካሞች የተገነቡ ቤቶችን አስረከቡ

ጳጉሜ 1/2014 (ዋልታ) የበጎ ፈቃድ ቀንን በማስመልከት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አቧሬ አካባቢ ለአቅመ ደካሞችና በአነስተኛ ገቢ ለሚተዳደሩ የአቧሬ አካባቢ ነዋሪዎች የተሠሩላቸውን ቤቶች አስረክበዋል።

ይህ ርክክብ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የተጀመረው የዓመታዊ የቤት እድሳት አንድ አካል መሆኑን ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

ለፈጣን መረጃዎች:-
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth

አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን!
3.4K views08:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-06 11:43:57
"እምባ ማበስና የኑሮ ጫና ማቃለል የመንግስታችን ቀዳሚ ኃላፊነት ነው" - ከንቲባ አዳነች አቤቤ አቤቤ

ጳጉሜ 1/2014 (ዋልታ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ ሦስት በመከላከያ ኮንስትራክሽን አማካኝነትና በሄይንከን ኢትዮጵያ የተገነቡ ቤቶችን መርቀው ለአቅመ ደካማ ወገኖች የቀልፍ ርክክብ አድርገዋል፡፡

ከንቲባዋ በሰው ተኮር ዕቅዳችንን ማዕከል በማድረግ በ2014 ዓ.ም በአጠቃላይ ስምንት ሺሕ ቤቶችን ድጋፍ ለሚሹ አቅመ ደካማ ወገኖች አስረክበናል ብለዋል፡፡

ባለፉት ጊዚያት በዓመት የነበረው ከፍተኛ ቤት የመገንባት አሃዝ ሶስት ሺሕ ነበር ያሉት ከንቲባ አዳነች ከበጎ ፈቃደኞችና ከአገር ወዳድ አካላት ጋር ከተቀናጀን ብዙ መሥራት እንደምንችል የተማርንበትም ምዕራፍ ነው ብለዋል፡፡

በዛሬው ዕለት 952 ቤቶችን ከበጎ ፈቃደኛች ጋር በቅንጅት ግንባታቸውን አጠናቀን ሙሉ በሙሉ ርክክብ እንፈጽማለን ብለው ማህበራዊ ኃላፊነታቸውን በአግባቡ የሚወጡ ዜጎች በሚፈለገው ልክ ከደገፉን ብዙ በመሥራት በጉብዝናቸው ወራት ለሀገር እጅግ የደከሙ አቅመ ደካማ ወገኖቻችን መደገፍ እንችላለን ሲሉ አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል::

እምባ ማበስና የኑሮ ጫና ማቃለል የመንግስታችን ቀዳሚ ኃላፊነት ነው ያሉት ከንቲባዋ በዘላቂነት ተመሣሣይ ችግር ያለባቸውን ወገኖች ለመርዳት ከተማ አስተዳደሩ ከበጎ ፈቃደኞችን ጋር ይሰራል ማለታቸውን የከንቲባ ጽ/ቤት መረጃ ያመለክታል፡፡

የበለጠ እያሰፋን እንድንሰራ የእስካሁኑ የአቅመ ደካማ ወጎኖች ቤት ግንባታ ምሳሌ ሆኖናል ያሉት ከንቲባዋ የምናርፈው በሁሉም ረገድ ሁለንተናዊ ብልጽግናችንን ስናረጋግጥ ብቻ ነው ብለዋል፡፡
ለፈጣን መረጃዎች:-
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
2.9K views08:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-06 11:43:57
ገንዘባችንን፣ ዕውቀታችንንና ጉልበታችንን እጅግ ለሚያስፈልጋቸው ወገኖች ከማዋል በላይ ሀገርን የመውደድ መገለጫ የለም - ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ

ጳጉሜ 1/2014 (ዋልታ) ገንዘባችንን፣ ዕውቀታችንንና ጉልበታችንን እጅግ ለሚያስፈልጋቸው ወገኖች ከማዋል በላይ ሀገርን የመውደድ መገለጫ የለም ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ዓለም ጸንታ የቆመችው ለሌሎች በሚደረግ መልካም ነገር መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡

ከለውጡ ወዲህ ከተከተልናቸው መርሖች አንዱ በማኅበራዊ ኃላፊነት ማኅበራዊ ችግሮችን መፍታት ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ማዕድ ማጋራት፣ የድኾችን ቤት መሥራት፣ ትምህርት ቤቶችንና የጤና ተቋማትን መገንባት፣ የችግረኛ ገበሬዎችን እርሻ ማረስ፣ አካባቢን አረንጓዴ ማድረግ ባህል እንዲሆኑ ሠርተናል ብለዋል።

ሚልዮኖችም የዚህ ተሳታፊ ሆነዋል፤ ከሕጻናት እስከ አረጋዊያን ባህላቸው አድርገውታል ሲሉም አክለዋል።

በዚህ ዓመት በተደረጉት እነዚህ ማኅበራዊ አገልግሎቶች የተሳተፋችሁትን ሁሉ በራሴና በመንግሥት ስም አመሰግናችኋለሁ ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ አገልግሎቱን ያገኙት ወገኖች እንደሚመርቁንና እንደሚጸልዩልን አምናለሁም ብለዋል።

ኢትዮጵያችን በእነዚህ ወገኖች ምርቃትና ጸሎት ፈተናዎቿን አሸንፋ እንደምትጓዝ እርግጠኛ ነኝ ሲሉም አመልክተዋል።

ለፈጣን መረጃዎች:-
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth

አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን!
2.6K views08:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-06 11:43:57
በዛሬው የበጎ ፈቃድ ቀን በየካቲት 12 ሆስፒታል የደም ልገሳ መርኃ ግብር እንደሚካሄድ ተገለጸ

ጳጉሜ 1/2014 (ዋልታ) በዛሬው የበጎ ፈቃድ ቀን በየካቲት 12 ሆስፒታል የደም ልገሳ መርኃ ግብር መዘጋጀቱን የኢትዮጵያ ደምና ቲሹ ባንክ አስታወቀ።

ዕለቱን በማስመልከት በየካቲት 12 ሆስፒታል በዋናነት ከተዘጋጀው መርኃ ግብር በተጨማሪ በአዲስ አበባ ከተማ የተለያዩ አደባባዮች ማህበረሰቡ በነቂስ ወጥቶ የደም ልገሳ ተግባር እንዲያከናውን ዝግጅት መጠናቀቁን የባንኩ ምክትል ዳይሬክተር ሃብታሙ ታዬ ገልፀዋል።

በአገር አቀፍ ደረጃ የበጎ ፈቃድ ቀንን በማስመልከት ይተገበራሉ ተብለው ሰፊ ዝግጀት ከተደረገባቸው ተግባራት መካከል የደም ልገሳ መርኃ ግብር አንዱ መሆኑን የጠቆሙት ኃላፊው በሁሉም አካባቢዎች የሚገኙ የደም ባንኮች እና የጤና ቢሮዎች ለስራው መሳካት ዝግጅት መጨረሳቸውን ገልጸዋል።

ዕለቱን ምክንያት በማድረግ ከጤና ሚኒስቴር፣ ትምህርት ሚኒስቴር እንዲሁም ስራና ክህሎት ሚኒስቴር የተውጣጡ አካላት በዕለቱ የሚካሄዱ የበጎ ፍቃድ አገልግሎት መርኃ ግብሮችን በዋናነት እንደሚያስተባብሩም ኃላፊው ተናግረዋል።

የበጎ ቀን ሲባል ትልቁ በጎነት የደም ልገሳ ነው የሚሉት ኃላፊው በደም እጥረት ምክንያት ህይወታቸውን ሊያጡ የሚችሉ ሰዎችን በበጎ ፈቃድ ደም በመለገስ መታደግ እንደሚቻል ገልፀዋል።

በክረምቱ በአዲስ አበባ ከተማ የተለያዩ ቦታዎች ድንኳኖችን በመትከል በጎ ፈቃደኞች ደም እንዲለግሱ በተከናወነው ስራ ከ3 ሺሕ በላይ ዩኒት ደም በክምችት ደረጃ መኖሩንም ኃላፊው ገልፀዋል።

ይሁንና አሁን ባለው ተጨባጭ የሃገራችን ሁኔታ የሚያስፈልገው የደም ከምችት ከፍተኛ እጥረት የሚታይበት መሆኑን ተናግረዋል።

ለፈጣን መረጃዎች:-
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
3.0K views08:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-05 20:21:51
አሸባሪው ህወሓት በጦርነት ምንም አይነት ተሳትፎ የሌላቸው ህጻናት፣ አረጋዊያንና ሴቶች ላይ አሰቃቂ ጥቃት ፈጽሟል - ተጎጂዎች

አሸባሪው ህወሓት በጦርነት ምንም አይነት ተሳትፎ የሌላቸው ህጻናት፣ አረጋዊያንና ሴቶች ላይ አሰቃቂ ጥቃት ፈጽሟል ሲሉ በዋግኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር በቡድኑ ጥቃት ሰለባ የሆኑ ተጎጂዎች ገለጹ።

ቡድኑ በለኮሰው ጦርነት የመከላከል አቅም የሌላቸውን ንጹሃንን የማይምር አረመኔ እንደሆነም አመልክተው ድርጊቱን በመገንዘብ የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ሊያወግዘው እንደሚገባ ተናግረዋል።

በዋግኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡ የቡድኑ ጥቃት ሰለባዎች እንዳሉት የአሸባሪው ህወሓት ታጣቂዎች በከፈቱት ጦርነት አስከፊ ጉዳት አድርሰዋል።

ታጣቂዎቹ በከባድ መሳሪያ ታግዘው በንጹሃን ላይ ጉዳት እንደሚያደርሱም ተናግረው በጥቃቱ ህይወታቸውን ያጡ ህጻናትና አረጋውያን እንዳሉ ተናግረዋል።

ከአንድ ቤተሰብ ሰባት ሰዎች እንደተገደሉና በሬ፣ ላምና በጎችም በጥቃቱ ሰለባ መሆናቸውን እንዳስተዋሉም ገልጸዋል።

ንጹሐንን ከመጨፍጨፍ ወደኋላ የማይለልውን አሸባሪ ቡድን ሁሉም ኢትዮጵያዊ ሊዋጋው እንደሚገባ አስገንዝበው ''የህወሓት የሽብር ቡድን ለንፁሃን ዜጎች ግድ የሌለውና ሃላፊነት የማይሰማው ነው” ብለዋል።

የብሄረሰብ አስተዳደሩ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ ኃላፊ ከፍያለው ደባሽ ቡድኑ በከፈተው ጦርነት ምክንያት በርካታ ንፁሃን ዜጎች ላይ የህይወትና የአካል ጉዳት ማድረሱን ገልጸዋል።

የሽብር ቡድኑ ለንፁሃን ዜጎች የማያስብ እንደሆነ በዋግኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር በንፁሃን ዜጎች ላይ የፈጸመው ጥቃት በቂ ማሳያ ነው ብለዋል።

ቡድኑ በተፈናቃይ ጊዜያዊ መጠለያ ጣቢያዎች በሚገኙ ወገኖች ላይም አረመኔያዊ ተግባር ፈፅሟል ብለዋል።
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
4.1K views17:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-05 20:21:50
የመውጫ ፈተና ለግልና ለመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች የጋራ መመዘኛ መሆኑ ተገለጸ

ነሐሴ 30/2014 (ዋልታ) የመውጫ ፈተና ለግልና ለመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች የጋራ መመዘኛ መሆኑን የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ፋንታ ማንደፍሮ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡

ከግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር በመውጫ ፈተና ዙሪያ ውይይት ተደርጓል፡፡

የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ በዚህ ወቅት እንደገለጹት የመውጫ ፈተናን ውጤት መሰረት በማድረግ የግልና የመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እርስ በርሳቸው እንደሚወዳደሩ ሚኒስትር ደኤታው አመልክተዋል፡፡

በመሆኑም ጥሩ ውጤት ሊገኝ የሚችለው ጥሩ ሂደት ሲኖር በመሆኑ ተቋማቱ ተማሪዎች ለውጤት እንዲበቁ ከወዲሁ ዝግጅት ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል፡፡

የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ ኤባ ሚጀና (ዶ/ር) በበኩላቸው በመውጫ ፈተና ዝግጅትና አስተዳደሩ ላይ የሚመለከታቸው ሁሉም ባለድርሻዎች እንደሚሳተፉበትና በትምህርት ሚኒስቴር አስተባባሪነት በማእከል እንደሚዘጋጅ ገልጸዋል፡፡

ተማሪዎች ለምረቃ መብቃትና የትምህርት ማስረጃዎቻቸውንም መውሰድ የሚችሉት የመውጫ ፈተናውን ካለፉ በኋለ መሆኑን ጠቁመው በፈተናው ያላለፉ ተማሪዎችም ተገቢውን ዝግጅት በማድረግ ደግመው መፈተን የሚችሉበት አሰራር እንደሚኖር  አስታውቀዋል፡፡

የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በመውጫ ፈተና ዙሪያ ለሚያደርጉት ዝግጅትም የትምህርት ሚኒስቴር አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚው አረጋግጠዋል፡፡

ለፈጣን መረጃዎች:-
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth

አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን!
3.3K views17:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-05 20:21:50
አሸባሪው ህወሓት በአንድ ቤት ውስጥ የነበሩ 10 ንጹሀን ዜጎችን በግፍ መግደሉ ተገለጸ

ነሐሴ 30/2014 (ዋልታ) የአሸባሪ ህወሓት ቡድን በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ሰቆጣ ወረዳ ልዩ ስሙ ወለህ በሚባል አካባቢ 10 ንጹሃን ዜጎችን በግፍ መጨፍጨፉን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።

ወ/ሮ ለምለም አዳነ የወለህ ማርያም ቀበሌ ነዋሪ ሲሆኑ ልጆቻቸውን ለማሳደግ፣ ለማስተማርና ለቁም ነገር ለማድረስ ደፋ ቀና እያሉ በነበሩበት ስዓት በጭካኔ የተሞላው እና ለንጹሃን የማይራራው የሽብር ቡደኑ ከነ ልጆቻቸው በጭካኔ ገድሏቸዋል ነው የተባለው።

ከተገደሉት ንጹሃን ዜጎች መካከል ሰባቱ ወ/ሮ ለምለም አዳነ እና 6 ልጆቻቸው ሲሆኑ ሌሎቹ 3ቱ ደግሞ ተፈናቃዮች መሆናቸው ታውቋል።

የሰላም ድርድሩን ወደ ጎን በማለት ድጋሚ ነፍጥ ያነሳው የሽብር ቡድኑ ህወሓት ሰላማዊ የሆኑና ራሳቸውን መከላከል የማይችሉ ሴት እና ሕፃናትን በከባድ መሳሪያ ጨፍጭፎ መግደሉን አሚኮ ዘግቧል።

ይህ የአሸባሪ ቡድኑ የጭካኔ ድርጊት፣ ከሰላም ይልቅ ለጦርነት እጁን የዘረጋ፣ የሀገሪቱ ዜጎች በሰላም እንዳይኖሩ የወጠነ ጨፍጫፊ ቡድን መሆኑን ያሳያል።

ለፈጣን መረጃዎች:-
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth

አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን!
3.4K views17:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ