2022-09-02 20:18:24
ምክር ቤቱ አሸባሪው ሕወሓት ሀገርን ለማፍረስ እያደረገ ያለውን ወረራ አወገዘ
ነሐሴ 27/2014 (ዋልታ) የደቡብ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት አሸባሪው ሕወሓት ሀገርን ለማፍረስ እያደረገ ያለውን ወረራ አውግዟል፡፡
የደቡብ ብሄሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በተለያዩ ጉዳዮች ላይ በመምከር ውሳኔ አሳልፏል።
የደቡብ ብሄሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል መስተዳድር ምክር ቤት ዛሬ ባካሔደው 247ኛ መደበኛ ስብሰባው በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በስፋት መክሯል።
በዚህም ምክር ቤቱ የደቡብ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል መንግሥት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የምሥረታ እና ነባሩን ክልል በአዲስ ክልል የማደራጀት ተግባር ማስፈፀሚያ ፕሮጀክት ጽ/ቤት ማቋቋሚያና የአሰራር ሥርዓት መወሰኛ ደንብ ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አስተላልፏል፡፡
ከሰሜኑ ጦርነት ጋር በተያያዘ መንግስት ለሰላም ያለውን ፅኑ አቋም በተኩስ አቁም ማሳየቱን እና አርሶ አደሩ ከነበረበት የጦርነት ስጋት ወጥቶ ወደ ግብርና ስራው እንዲያተኩር ለማድረግ መንግስት የተኩስ አቁም ማድረጉ በምክር ቤቱ ገልጿል፡፡
ሆኖም ግን አሸባሪው ህወሓት መንግስት ለሰላም ያሳየውን ቁርጠኝነት ወደ ጎን በመተው በህዝብ ላይ ግልጽ ወረራ መፈፀሙን ምክር ቤቱ ጠቅሷል።
መንግስት የዜጎችን ህይወት ለመታደግ ብሎም በሀገሪቱ ላይ የተቃጣውን ጥቃት ለመመከት ተገዶ የገባበትን ጦርነት መስተዳድር ምክር ቤቱ የሚደግፍ ሲሆን ሂደቱንም በቅርበት እንደሚከታተል አጽንኦት መስጠቱን ከክልሉ ኮሙኒኬሽ ቢሮ የተገኘ መረጃ ያመለክታል።
ለፈጣን መረጃዎች:-
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን!
3.3K views17:18