Get Mystery Box with random crypto!

Walta

የቴሌግራም ቻናል አርማ walta_tv_eth — Walta W
የቴሌግራም ቻናል አርማ walta_tv_eth — Walta
የሰርጥ አድራሻ: @walta_tv_eth
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 8
የሰርጥ መግለጫ

This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.
For more updates please visit https://www.facebook.com/waltainfo
#ሼር #በማድረግ_አጋርነታችሁን_አሳዩን

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-09-05 15:09:56
ኢትዮ ቴሌኮም ለአካል ጉዳተኞችና አረጋዊያን ማኅበራት ድጋፍ አደረገ

ነሐሴ 30/2014 (ዋልታ) በኢትዮ ቴሌኮም የምዕራብ ሪጅን ለቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አካል ጉዳተኞች እና አረጋዊያን ማኅበራት የገንዘብ ድጋፍ አደረገ።

የሪጅኑ ኦፕሬሽን ዳይሬክተር ጥላሁን እጅጉ እንዳሉት አብሮነት በመልካም ተግባር በሚል መሪ ቃል ኢትዮ ቴሌኮም ድጋፍ አድርጓል።

በዚህም የድርጅቱ ምዕራብ ሪጅን ለአካል ጉዳተኞች እና አረጋዊያን ማኅበራት የ150 ሺሕ ብር ድጋፍ አድርጓል ብለዋል።

ተቋሙ የተሰጠውን ተልዕኮ ከማስፈጸም ባሻገር ለተቸገሩ ወገኖች የሚያደርገውን በጎ ተግባር አጠናክሮ ይቀጥላል ማለታቸውን የኢዜአ ዘገባ አመላክቷል፡፡

ድጋፉን ያበረከቱት የአሶሳ ዞን መስተዳድር ተወካይ ኡስማን መሃመድ ኢትዮ ቴሌኮም ኅብረተሰቡን በማቀራረብ የልማት ስራዎችን ከማፋጠን ባለፈ የዜግነት ግዴታውን እየተወጣ ይገኛል ብለዋል።
ለፈጣን መረጃዎች:-
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth

አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን!
4.0K views12:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-05 15:09:56
የኬንያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት የዊሊያም ሩቶን አሸናፊነት አጸና

ነሐሴ 30/2014 (ዋልታ) የኬንያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት በሀገሪቱ በተካሄደው ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ላይ የቀረበውን ክስ ውድቅ በማድረግ የዊሊያም ሩቶን በፕሬዝዳንትነት መመረጥ አጸደቀ።

ተሸንፈው የነበሩት እና ጉዳዩን ወደ ፍርድ ቤት የወሰዱት ራይላ ኢዲንጋ ያቀረቡትን ክስ የሀገሪቱ ፍርድ ቤት ውድቅ ማድረጉን ቢቢሲ ዘግቧል።

ምርጫውን ተከትሎ ተፎካካሪ ዕጩ የነበሩት ራይላ ኦዲንጋ በምርጫው ሂደት ላይ ማጭበርበር መከሰቱን በመግለጽ ያቀረቡትን ክስ ተከትሎ ነው ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ውሳኔውን ያሳለፈው።

ሰባት አባላት ያሉት የኬንያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት የቀረበለትን ክስ ሲመለከት ቆይቶ ዊሊያም ሳሞይ ሩቶ አምስተኛው የአገሪቱ ፕሬዝዳንት ሆነው የተመረጡበት ሂደትን ተቀብሎታል።

ተቀናቃኙ ራይላ ኦዲንጋ እና አጋሮቻቸው በምርጫው ሂደት የውጤት መለወጥን ጨምሮ ከፍተኛ የማጭበርበር ድረጊቶች ተፈጽመዋል በማለት ነው ለአገሪቱ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ክስ ያቀረቡት።

ከፍተኛ ፉክክር በተካሄደበት ምርጫ 50 ነጥብ 5 በመቶ የመራጮችን ድምጽ አግኝተው በጠባብ የድምጽ ብልጫ ነበር ዊሊያም ሩቶ ማሸነፋቸው የታወጀው።

ለፈጣን መረጃዎች:-
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth

አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን!
3.5K views12:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-05 15:09:56
በአዲስ አበባ በተለያዩ ክፍለ ከተሞች ለመከላከያ ሰራዊት የስንቅ ዝግጅት እየተደረገ ነው

ነሐሴ 30/2014 (ዋልታ) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳዳር በተለያዩ ክፍለ ከተሞች ለመከላከያ ሰራዊት የስንቅ ዝግጅት መርኃ ግብር እየተከናወነ ነው፡፡

በዚህም በየካ፣ ጉለሌ እና ለሚ ኩራ ክፍለ ከተሞች በሁሉም ወረዳ የሚገኙ ነዋሪዎች ለአገር መከላከያ ሰራዊት ደጀን መሆናቸውን በተግባር ለማሳየት የስንቅ ዝግጅት እያደረጉ መሆኑ ተገልጿል፡፡

በስንቅ ዝግጅት መርኃ ግብሩ የክፍለ ከተሞቹ ከፍተኛ ሥራ ኃላፊዎች ተዘዋውረው በመመልከት ማበረታታቸውን ከከንቲባ ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

ለፈጣን መረጃዎች:-
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth

አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን!
3.1K views12:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-05 15:09:56
የተፋሰሱ አባል አገራት በፍትሀዊ አጠቃቀም ላይ ትብብራቸውን እንዲያጠናክሩ ም/ጠ/ሚ ደመቀ ጥሪ አቀረቡ

ነሐሴ 30/2014 (ዋልታ) የናይል ተፋሰስ አባል አገራት በፍትሀዊ እና ምክንያታዊ አጠቃቀም ላይ ትብብራቸውን እንዲያጠናክሩ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ጥሪ አቀረቡ፡፡

የናይል ተፋሰስ የላይኛው አባል አገራት የመጀመሪያው ከፍተኛ የትብብር ኮንፈረንስ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ኮንፈረንሱን በይፋ በከፈቱበት ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት የተፋሰሱ አባል አገራት በፍትሀዊ እና ምክንያታዊ አጠቃቀም ላይ ትብብራቸውን እንዲያጠናክሩ ጥሪ አቅርበዋል።

የናይል ወንዝን በፍትሀዊነት ለመጠቀም ምሁራን፣ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች እና ጋዜጠኞች በሙያቸው የበኩላቸውን አበርክቶ እንዲወጡ ጠይቀዋል።

የናይል ወንዝ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ እያደረሰበት በመሆኑ ሁሉም አባል አገራት የወንዙን ደኅንነት ለመጠበቅ የበኩላቸውን ሚና ሊወጡ ይገባልም ብለዋል።

ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት መጀመሩ ጠቀሜታው ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ቀጣናዊ ጭምር ነው ብለዋል።
በኮንፈረንሱ ላይ የላይኛው ተፋሰስ አባል አገራት ተመራማሪዎች፣ የቀድሞ ሚኒስትሮች፣ ጋዜጠኞች እና ተፅዕኖ ፈጣሪዎችም መታደማቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽ/ቤት መረጃ ያመላክታል።

ለፈጣን መረጃዎች:-
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth

አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን!
3.0K views12:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-05 11:25:04
በአሜሪካ ለተፈናቀሉ ወገኖች የሚውል ከ100 ሺሕ ዶላር በላይ ተሰበሰበ

ነሐሴ 30/2014 (ዋልታ) በአሜሪካ ዋሺንግተን ዲሲ ለተፈናቀሉ ወገኖች የሚውል የገቢ ማሰባሰቢያ መርኃ ግብር ከ100 ሺሕ ዶላር በላይ ተሰበሰበ።

በዓለም አቀፍ የኢትዮጵያ ዳያስፖራ የተግባር ቡድን “ሁሉም እጆች ለኢትዮጵያ” በሚል መሪ ሀሳብ በግጭትና በተፈጥሮ አደጋዎች ምክንያት ለተፈናቀሉ ዜጎች የሚውል የገቢ ማሰባሰቢያ መርኃ ግብር በዋሺንግተን ዲሲ በሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ተካሂዷል።

በመርኃ ግብሩ ለጨረታ ቀርቦ በ10 ሺሕ ዶላር የተሸጠውን የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የስዕል ሥራ ጨምሮ በአጠቃላይ ከ100 ሺሕ ዶላር በላይ ገቢ ተሰበስቧል።

በአሜሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስለሺ በቀለ ዳያስፖራው በተለያዩ መስኮች ለኢትዮጵያ የሚያደርገው ድጋፍን ማሳደግ እንደሚገባ ገልጸዋል።

መርኃ ግብሩን ላዘጋጁትና ተሳትፎ ላደረጉ አካላት ምስጋና ያቀረቡት አምባሳደር ስለሺ በተለይም የኢትዮጵያን እውነት ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ በማስገንዘብ፣ በዕውቀትና በቴክኖሎጂ ሽግግር፣ በተቋማት ግንባታ፣ በዲጂታልና በህዝብ ለህዝብ ዲፕሎማሲ የዳያስፖራው ተሳትፎ ማደግ እንዳለበት አመላክቷል።

በገቢ ማሰባሰቢያ መርኃ ግብሩ ላይ በተባበሩት መንግሥታት የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛ አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ፣ ጋዜጠኛ ሄርሜላ አረጋዊ፣ የዳያስፖራ ማኅበረሰብ አባላትና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች መገኘታቸውን የኢዜአ ዘገባ ያመለክታል።

ለፈጣን መረጃዎች:-
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth

አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን!
842 views08:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-05 11:25:04
አዲስ ወግ “ፈተና፣ ድል፣ ተስፋ” በሚል ርዕስ እየተካሄደ ነው

ነሐሴ 30/2014 (ዋልታ) የ2014 የመጨረሻው #አዲስ ወግ ውይይት “ፈተና፣ ድል፣ ተስፋ” በሚል ርዕስ እየተካሄደ ይገኛል፡፡

ውይይቱ የ2014 ዓ.ምን በመቃኘት እየተካሄደ እንደሚገኝ ነው የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት መረጃ ያመላከተው፡፡

በመድረኩ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ብሔራዊ ደኅንነት አማካሪ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን፣ የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ እንዲሁም የፕላን እና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተሳታፊዎች ናቸው።

አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን በዚህ ወቅት እንደገለጹት ከተሠሩ የለውጥ እርምጃዎች የተነሳ የጸጥታ ተቋማት የሀገርን ሰላም ለማስከበርና ሉዓላዊነትን ለማስጠበቅ እንዲሁም የዜጎችን ደኅንነት ለማስጠበቅ በሚያስችል አቋም ላይ ይገኛሉ ብለዋል።
ለፈጣን መረጃዎች:-
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth

አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን!
764 views08:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-04 20:46:20
በጎነት ለተወሰነ ሰው፣ ዘር፣ ሃይማኖት የተሰጠ አይደለም- ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ

ነሐሴ 29/2014 (ዋልታ) በ10ኛው የበጎ ሰው ሽልማት መርኃ ግብር ላይ ተገኝተው የመዝጊያ ንግግር ያደረጉት የኢፌድሪ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በጎነት ለሆነ አካል ብቻ የተሰጠ ተግባር አይደለም ሲሉ ተናገሩ።

በጎ ሰው የሚሰራውን ስራ በንፁህነት፣ በትጋት እና በታማኝነት የሚሰራ ማለት ነውም ብለዋል።

የበጎ ሰው ተሸላሚዎች ለሀገራቸውና ለሕዝባቸው የሚችሉትን ያደረጉና ብዙ የፈፀሙ ናቸውና ይገባቸዋል ነው ያሉት ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ።

የሚሰሩ ሰዎችን እውቅና የመስጠትና የማመስገን ልምዳችን ዝቅተኛ ነው ያሉት ፕሬዝዳንቷ ምስጋና እና እውቅና መስጠትን ሁላችንም ልናደርገው የሚገባ ነው ብለዋል።

መርኃ ግብሩም እውቅና የመስጠትን ልምድ የሚያበረታታ በመሆኑም አዘጋጆቹን አመስግነዋል።

"በጎ ሰዎችን በመሸለምና ዕውቅና በመስጠት ሌሎች በጎ ሰዎች እናፍራ" በሚል መሪ ቃል የተካሄደው 10ኛው የበጎ ሰው ሽልማት ተጠናቋል።

በትዕግስት ዘላለም

ለፈጣን መረጃዎች፦
ፌስቡክ https://bit.ly/3Ma7QTW
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
ዩቲዩብ https://www.youtube.com/c/WaltaTV/featured
ቲዊተር https://twitter.com/walta_info
አብራችሁን ስለሆናችሁ እናመሰግናለን!
3.1K views17:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-04 20:46:20
ኮማንደር አትሌት ደራርቱ ቱሉ የ10ኛው የበጎ ሰው ልዩ ተሸላሚ ሆነች

ነሐሴ 29/2014 (ዋልታ) ኮማንደር አትሌት ደራርቱ ቱሉ ለሀገሯ ባበረከተችው አስተዋፆ የ10ኛው የበጎ ሰው ልዩ ተሸላሚ ሆናለች።

35 የወርቅ፣12 የብር፣15 የነሀስ ሜዳልያ ለሀገራኗ ለሕዝብ አበርክታለች።

ስፖርት የሰላም፣ የፍቅር፣ የአንድነትና የሀገር መገለጫ መሆኑን ማሳየትም የቻለች ነች።

እንዲሁም በሚዲያና ጋዜጠኝነት  ዘርፍ ሰለሞን ገብረስላሴ እንዲሁም በሳይንስ ዘርፍ ረዳ ተክለሃይማኖት ፕ/ር ተሸላሚ ሆነዋል።

በትዕግስት ዘላለም

ለፈጣን መረጃዎች፦
ፌስቡክ https://bit.ly/3Ma7QTW
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
ዩቲዩብ https://www.youtube.com/c/WaltaTV/featured
ቲዊተር https://twitter.com/walta_info
አብራችሁን ስለሆናችሁ እናመሰግናለን!
2.5K views17:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-04 20:46:20
መቆዶኒያ በጎፋ ዞን ለሚያስገነባው ህንፃ የመሰረት ድንጋይ አስቀመጠ

ነሐሴ 29/2014 (ዋልታ) መቆዶኒያ የበጎ አድራጎት ማህበር ከ80 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ በጎፋ ዞን ሳውላ ከተማ ለሚያስገነባው ህንፃ የመሰረት ድንጋይ አስቀምጧል።

በመቆዶኒያ የበጎ አድራጎት ማህበር የክልል ጉዳዮች ዳይሬክተር ማህተሜ በቃሉ ማህበሩ በአዲስ አበባ ማዕከል ከ7 ሺህ 500 በላይ ለሚሆኑ አረጋዊያንና የአዕምሮ ህሙማን አስፈለጊውን የምግብና ሌሎች ድጋፎችን እያደረገ መሆኑን አንስተው ሰብዓዊ ድጋፉን በመላው ኢትዮጵያ ተደራሽ ለማድረግ አቅዶ በስድስት ከተሞች ተጨማሪ ቅርንጫፎችን በመክፈት አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን ገልፀዋል።

የመቆዶኒያ ዋናው ማዕከል ምክትል ስራ አስኪያጅ ማሞ ታደሰ በበኩላቸው አረጋዊያንን ማገልገል ህዝብን ከምናገለግለው በላይ እንደሆነ በመረዳት ማገልገል እንደሚገባ አንስተው ግንባታው በአጭር ጊዜ ውስጥ እንደሚጠናቀቅ ተናግረዋል።

የሳዉላ ከተማ ከንቲባ ሙሉቀን ጉጃ የከተማ አስተዳደሩ ከ80 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ለሚገነባው የማህበሩ ህንጻ 300 ካሬ ሜትር ቦታ ያዘጋጀ መሆኑን ተናግረዉ ይህ ግንባታ ተጠናቅቆ አገልግሎት እስከሚሰጥ ድረስ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርጉ ቃል ገብተዋል፡፡

የጎፋ ዞን ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ ተመስገን ጌታቸው በበኩላቸው የሚሰራው ህንፃ ነገ እንደራሳችን መኖሪያ የሚታይ መሆኑን አስረድተው ሁሉም ሰው የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣም አሳስበዋል።

ግንባታው ሲጠናቀቅ አንድ ሺህ አረጋዊያንን ተጠቃሚ እንደሚያደርግም ደሬቴድ ነው የዘገበው።

ለፈጣን መረጃዎች:-
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth

አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን!
2.2K views17:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-04 20:46:20
ሕዝበ ሙስሊሙ ለሀገር ሰላም እያደረገ ያለውን አስተዋጽኦ አጠናክሮ እንዲቀጥል ምክር ቤቱ አሳሰበ

ነሐሴ 29/2014 (ዋልታ) ህዝበ ሙስሊሙ ለሀገር ሰላምና ለህዝቦች አንድነት እያደረገ ያለውን አስተዋጽኦ ከሌሎች ወገኖቹ ጋር በመሆን አጠናክሮ እንዲቀጥል የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ሼክ ሀጂ ኢብራሀም ቱፋ አሳሰቡ።

የምክር ቤቱ ፕሬዚዳንትና የምክር ቤቱ አባላት ከሲዳማ ክልል የእስልምና እምነት ተከታዮች ጋር የትውውቅ መርኃ ግብር ዛሬ በሐዋሳ አካሂደዋል።

ሼክ ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ በሥነ ሥርዓቱ ላይ እንዳሉት ሀገር ካለባት የሰላም እጦት እንድትላቀቅ መላው የእስልምና እምነት ተከታይ ከሌሎች ወገኖቹ ጋር በመተባበር መስራት አለበት።
ለፈጣን መረጃዎች:-
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth

አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን!
2.1K views17:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ