Get Mystery Box with random crypto!

Walta

የቴሌግራም ቻናል አርማ walta_tv_eth — Walta W
የቴሌግራም ቻናል አርማ walta_tv_eth — Walta
የሰርጥ አድራሻ: @walta_tv_eth
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 8
የሰርጥ መግለጫ

This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.
For more updates please visit https://www.facebook.com/waltainfo
#ሼር #በማድረግ_አጋርነታችሁን_አሳዩን

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 7

2022-08-31 21:12:05
የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በነበረበት እንደሚቆይ ተገለጸ

ነሐሴ 25/2014 (ዋልታ) የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ከነሐሴ 26 ቀን 2014 ዓ.ም እስከ መስከረም 30 ቀን 2015 ዓ.ም በነበረበት እንደሚቆይ የንግድ እና ቀጣናዊ ትሥሥር ሚኒስቴር አስታወቀ።

ከነሐሴ 26 ቀን 2014 ዓ.ም እስከ መስከረም 30 ቀን 2015 ዓ.ም ተግባራዊ የሚደረገው የነዳጅ ምርቶች ዋጋ የአውሮፕላን ነዳጅን ጨምሮ በነሐሴ ወር 2014 ዓ.ም እየተሸጠበት ባለው ዋጋ ያለምንም ለውጥ እንዲቀጥል የተወሰነ መሆኑን የሚኒስቴሩ መረጃ አመላክቷል።

ከሰኔ 29 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ እየተደረገ ያለው የታለመት የነዳጅ ድጎማ አሠራር በተመሳሳይ በመስከረም ወር 2015 ዓ.ም እንደሚቀጥልም ገልጿል።

ለፈጣን መረጃዎች:-
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth

አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን!
3.7K views18:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 21:12:04
ቢሮው የ8ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ከዛሬ ጀምሮ በኢንተርኔት ላይ ማየት እንደሚቻል አስታወቀ

ነሐሴ 25/2014 (ዋልታ) የኦሮሚያ ትምህርት ቢሮ የ8ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ከዛሬ ጀምሮ በኢንተርኔት ላይ ማየት እንደሚቻል አስታወቀ።

ቢሮው የ8ኛ ክፍል ፈተና ውጤት መውጣቱን አስመልክቶ በሰጠው መግለጫ በክልሉ 451 ሺሕ 21 ተማሪዎች ለፈተና የተመዘገቡ ሲሆን 98 ነጥብ 3 በመቶ የሚሆኑት ፈተና መውሰዳቸውን ገልጿል።

በዚህም የ9ኛ ክፍል የማለፊያ ውጤት ለወንዶች 50 በመቶ እና ለሴቶች 47 በመቶ ነው ብሏል።

በአርብቶ አደሩ አካባቢ የ9ኛ ክፍል ማለፊያ ውጤት በመቶኛ ለወንዶች 47% ለሴቶች 44% ሲሆን ለልዩ ፍላጎት ተማሪዎች ደግሞ ለወንዶች 44% እና ለሴቶች 41% መሆኑም ተገልጿል።

ማለፊያው ውጤት በአገሪቱ ተጨባጭ ሁኔታ እና በትምህርት ጥራት ላይ ተመስርቶ መወሰኑን የኦሮሚያ ትምህርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ ግርማ ባይሳ ገልጸዋል::

ሴት ተማሪዎች የተሻለ የፈተና ውጤት በማምጣት ለውጥ አምጥተዋልም ነው ያሉት።

ተማሪዎች ውጤታቸውን በኢንተርኔት ላይ ‘https://oromia.ministry.et/#/home ላይ መመልከት ይችላሉም ነው የተባለው።
ለፈጣን መረጃዎች:-
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth

አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን!
3.4K views18:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 16:58:13
ህወሓት ሕጻናትን በጦርነት እያሰለፈ የሚያከናውነውን ጭካኔ የተሞላበት ተግባር ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ እያወገዘው አለመሆኑ ተገለጸ

ነሐሴ 25/2014 (ዋልታ) አሸባሪው ህወሓት ሕጻናትን አስገድዶ በጦርነት በማሰለፍ የሚያከናውነውን ጭካኔ የተሞላበት ተግባር ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ በተገቢው መልኩ እያወገዘው አለመሆኑ ተገለጸ፡፡

የፖለቲካ ተንታኙ አንድሪው ኮሪብኮ ለኢዜአ እንደገለጹት አሸባሪው ህወሓት ሕጻናትን አስገድዶ በጦርነት በማሰለፍ ለሰው ማዕበል የጦርነት ስልት እየተጠቀመባቸው ቢሆንም ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ለጉዳዩ የሚጠበቅበትን ምላሽ እየሰጠ አይደለም፡፡

ሥነ ምግባር ያለው ወታደር ሕጻናትን ተኩሶ እንደማይገድል ገልጸው የሽብር ቡድኑ ማፊያዎች ይህን ከግንዛቤ በማስገባት ሕጻናትን በጦርነት በማሰለፍ ለሽብር ተግባራቸው እውን መሆን እየሠሩ ነው ብለዋል፡፡

ቡድኑ ሕጻናትን በጦርነት የሚያሰልፈው በወታደሩ ዘንድ “ራስን በመከላከልና ሕጻናትን ተኩሶ አለመግደል” በሚለው የሞራል እሳቤ ላይ ውዥንብር ለመፍጠርና ዓለማውን ለማሳካት መሆኑንም ነው የጠቀሱት፡፡

ኢትዮጵያ ለመልማት የምታደርገውን ጥረትና በዓለም አቀፉ መድረክ ያላትን ሚዛናዊ አካሄድ የማይፈልጉ የውጭ አካላት ጦርነቱ እንዲባባስ እየሠሩ መሆናቸውንም ተናግረዋል፡፡

የፌዴራል መንግሥት ችግሩ በሰላም እንዲፈታ ረዥም ርቀት ቢጓዝም የሽብር ቡድኑ ግን ጥቃትን በመፈጸም ችግሮች እንዲባባሱ ማድረግ ሆኗል ነው ያሉት፡፡

ለፈጣን መረጃዎች:-
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth

አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን!
4.1K views13:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 16:58:13
ደቡብ ሱዳን ለኢትዮጵያ ያላትን ድጋፍ አረጋገጠች

ነሐሴ 25/2014 (ዋልታ) የደቡብ ሱዳን ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ሀገራቸው ለኢትዮጵያ ያላትን ጠንካራ ድጋፍ በድጋሚ አረጋግጠዋል፡፡

የመከላከያ ሚኒስትር አብርሃም በላይ (ዶ/ር) ከደቡብ ሱዳን ምክትል ፕሬዝዳንት ታባን ዴንግ እንዲሁም ከሀገሪቷ ፕሬዝዳንት ሳልቫኪር የደኅንነት ጉዳዮች አማካሪ ቱት ጋትሉዋክ ጋር መክረዋል፡፡

በዚህም ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎቹ ሀገራቸው በማንኛውም ሁኔታ ውስጥ ከኢትዮጵያ ጋር ለመቆም የማይናወጥ አቋም እንዳላት መግለጻቸውን በጁባ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ አመላክቷል፡፡

ሁለቱ ወገኖች በቀጣናው የሠላም እና ደኅንነት ጉዳዮች ላይ የመከሩ ሲሆን ኢትዮጵያ እና ደቡብ ሱዳን በትብብር መሥራት አስፈላጊ እንደሆነም ተነስቷል፡፡

ለፈጣን መረጃዎች:-
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth

አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን!
3.5K views13:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 16:58:13
ለፀጥታ ኃይሎች የምናደርገው ሁለንተናዊ ድጋፍ ተጠናክሮ ይቀጥላል- የወልዲያ ከተማ ነዋሪዎች

ነሐሴ 25/2014 (ዋልታ) ''የሕወሓት የሽብር ቡድንን በጀግንነት እየተፋለሙ ለሚገኙ የመከላከያና ሌሎች የፀጥታ ኃይሎች የምናደርገው ሁለንተናዊ ድጋፍ ተጠናክሮ ይቀጥላል’’ ሲሉ የወልዲያ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ።

በከተማው የንግድና ሌሎች ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች እየተከናወኑ እንደሆነ ተገልጿል።

የከተማው ነዋሪዎች ''ወራሪ ቡድኑን ባጠረ ጊዜ ድል መምታት የምንችለው ከሰራዊቱ ጎን በመሰለፍ ነው'' ያሉ ሲሆን ለመከላከያ ሰራዊቱና ሌሎች ፀጥታ ኃይሎች ጉልበት ለመስጠትም የእለት ደራሽ ምግቦችን በተደራጀ አግባብ እያዘጋጁ መሆኑን ተናግረዋል።

ተደራጅተው ስንቅ ለሰራዊቱ ግንባር ድረስ ሄደው ለማቅረብ ዝግጅት እያደረጉ መሆኑን ገልጸው ከስንቅ ዝግጅት ባለፈ ግንባር በመግባት ጠላትን ለመዋጋት ዝግጁ መሆናቸውንም ገልጸዋል።

የሕወሓት የሽብር ቡድንን በጀግንነት እየተፋለሙ ለሚገኙ የፀጥታ ኃይሎች ደጀን መሆን እንደሚገባ የገለጹት የወልዲያ ከተማ ነዋሪዎች ይህ ድጋፍና እገዛም ሰራዊቱ ጦርነቱን በድል እስኪያጠናቅቅ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

አሸባሪው የሕወሓት ቡድን ሃሰተኛ ወሬን በስፋት በመጠቀም ኅብረተሰቡን ለማደናገር ይሰራል ያሉት ነዋሪቹ ለዚህም ኅብረተሰቡ የሽብር ቡድኑን የሃሰት ወሬ በመረዳት አካባቢውን ነቅቶ ሊጠብቅና ለሰራዊቱ ደጀንነቱን ሊያጠናክር እንደሚገባ ጠቁመዋል።

በወልዲያ ከተማ በአሁኑ ወቅት የጉሊት ገበያን ጨምሮ፣ ሌሎች ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች እንደቀጠሉ መሆናቸውን ኢዜአ ከስፍራው ዘግቧል።

ለፈጣን መረጃዎች:-
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth

አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን!
3.5K views13:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 12:47:09
የሕወሐት ዕብሪት ለሰላም የተዘረጉ እጆች እንዲታጠፉ እያስገደደ ነው - መንግሥት

ነሐሴ 25/2014 (ዋልታ) የሕወሐት ዕብሪት ለሰላም የተዘረጉ እጆች እንዲታጠፉ እያስገደደ ነው ሲል የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ገለጸ፡፡

የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ያወጣው ወቅታዊ መግለጫ ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል፡-

የሕወሐት ዕብሪት ለሰላም የተዘረጉ እጆች እንዲታጠፉ እያስገደደ ነው!

መንግሥት ለሰላም አማራጭ ዕድል ለመስጠት ሲል የሕዝብ ማዕበል አስነሥቶ ሕጻናትን፣ ወጣቶችንና አረጋውያንን ለመማገድ የመጣውን የሕወሐት ታጣቂ፣ በምሥራቅ አማራ በኩል በጀግንነት ሲከላከል ቆይቷል።

ሕወሐት በምሥራቅ አማራ በኩል በቆቦና አካባቢው የከፈተው ወረራ በጀግናው የመከላከያ ሠራዊትና በደጀኑ ሕዝብ ጠንካራ የመከላከል ብቃት የተነሣ ባሰበው ልክ አልሄደለትም።

በዚህም ምክንያት ለሰላም የተሰጠውን ሁለንተናዊ አማራጭ አሽቀንጥሮ ጥሎ ወረራውን ወደ ሌሎች አካባቢዎች እያስፋፋ ይገኛል።

ያለ ጦርነት መኖር የማይችለው ሕወሐት በዋግ፣ በወልቃይት አቅጣጫና በሱዳን ድንበር አካባቢ ወረራ ከፍቷል። ይሄንን የሕወሐት ወረራ ጀግናው የመከላከያ ሠራዊት በተሟላ ዝግጅትና በጽኑ ቁመና እየተከላከለ ይገኛል።

የኢትዮጵያ መንግሥት በተለያዩ አቅጣጫዎች የተከፈቱበትን ጥቃቶች በጽናት እየተከላከለ፣ አሁንም ለሰላም አማራጮች የዘረጋቸውን እጆች ዛሬም ድረስ አላጠፈም።

ለሰላም የተዘረጋው እጅ በሕወሐት ዕብሪታዊ ወረራ ምክንያት እንዳይታጠፍ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ የሚቻለውን እንዲያደርግ የኢትዮጵያ መንግሥት አሁንም ያሳስባል። ወገናችን የሆነው የትግራይ ሕዝብም ይሄንን የዕብሪት ወረራ በማውገዝ ሕወሐት ከሚያስከትልበት መከራ ራሱን ነጻ እንዲያወጣ ጥሪ እናቀርባለን።

የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

t.me/WALTA_TV_Eth
4.2K views09:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 12:47:09
“የሃይማኖት መገናኛ ብዙኃን ለአብሮነት እሴቶች መጠናከር” በሚል ምክክር እየተካሄደ ነው

ነሐሴ 25/2014 (ዋልታ) የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን ከኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጋር “የሃይማኖት መገናኛ ብዙኃን ለአብሮነት እሴቶች መጠናከር” በሚል ምክክር እያካሄደ ነው።

በመድረኩ በሰላም ግንባታ ዙሪያ የሃይማኖት ተቋማት ሚና፣ የትውልድ ቀረጻና የጋራ ዕሴቶችን ስለማስቀጠል በሚል ውይይት እየተደረገ ነው።

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር መሃመድ እድሪስ እንደገለጹት ሃይማኖት ኢትዮጵያ ውስጥ የነበረውን አዎንታዊ ሚና ታሳቢ በማድረግ እንዲሁም ትውልድ ቀረጻና ሀገር ግንባታ ላይ የሚሰሩትን ሥራ ለማጠናከር የሃይማኖት መገናኛ ብዙኃን ፈቃድ ተሰጥቷል።

በኢትዮጵያ 46 የሃይማኖት መገናኛ ብዙኃን እንዳለ የሚታወቅ ሲሆን ዛሬ 23ቱ ፈቃድ እንደሚሰጣቸውና ቀሪዎቹ በሂደት ላይ መሆናቸው ተመላክቷል።

በኢትዮጵያ 97 ነጥብ 3 በመቶ የሚሆነው አማኝ ባለባት ሃገር ግጭት፣ ጦርነትና መፈናቀል የታየው ትውልዱ ላይ ባለመሰራቱ በመሆኑ የሃይማነት ሥነ ምግባር ላይ መስራት እንዳለባቸው ተገልጿል።

ለፈጣን መረጃዎች:-
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth

አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን!
3.5K views09:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 12:47:09
አሻባሪው ህወሓት የጥፋት ጉዞ ለሠላማችን ዘብ በመቆም እንገታዋለን - የሀረሪ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት

ነሐሴ 25/2014 (ዋልታ) አሻባሪው ህወሓት ለሠላም የተዘረጋውን የኢትዮጵያ እጅ ነክሶ የጀመረውን የጥፋት ጉዞ ለሠላማችን ዘብ በመቆም እንገታዋለን ሲሉ የሀረሪ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አብዱጀባር መሀመድ ተናገሩ፡፡

የሀረሪ ክልል ብልጽግና ፓርቲ አመራሮች በወቅታዊ ሀገራዊና ክልላዊ ጉዳዮች ላይ ውይይት ተካሄደ።

የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አብዱጀባር መሀመድ እንዳሉት አሸባሪው ህወሓት በተደጋጋሚ ጊዜ የቀረበለትን የሰላም ጥሪ ወደ ጎን በመተው ለሦስተኛ ጊዜ በሀገራችን ላይ ጦርነት ከፍቷል።

መንግሥት የሠላም አማራጭ የተከተለው የትግራይን ሕዝብ ዘላቂ ጥቅም በማሰብ እንደሆነ ጠቁመው፣ ቡድኑ ግን ለሶስተኛ ጊዜ ወረራ መፈጸሙን ተናግረዋል።

አሻባሪው ህወሃት ለሠላም የተዘረጋውን የኢትዮጵያ እጅ ነክሶ የጀመረውን የጥፋት ጉዞ ለሠላማችን ዘብ በመቆም እንገታዋለን ብለዋል።

የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ለማስከበር አስፈላጊውን መሥዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁ ነን ማለታቸውን ከክልሉ መንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያሳያል፡፡

መላው የክልሉ ሕዝብ ባለፋት ጊዜያት በአገር ህልውና ላይ ከውስጥና ከውጭ የተቃጣብንን አደጋ ለመመልከት በተደረገው ጥረት ምልአተ ህዝቡን በማነቃነቅ ግንባር ቀደም የድጋፍ ተሳትፊ በማድረግ ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከት እንደተቻለም ገልጸዋል።

ሰርተን መለወጥ የምንችለው ሀገር ሰላም ስትሆን መሆኑን የገለጹት ኃላፊው አሸባሪው ህወሓት የሀገርን አንድነት ለመናድ የሚያደርገውን ሙከራ ለመመከት የክልሉ መንግሥትና ሕዝብ አስፈላጊውን ድጋፍ የሚያደርግ መሆኑን ገልጸዋል።

ለፈጣን መረጃዎች:-
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
3.2K views09:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 12:47:09
የቻይና ወታደሮች ሩሲያ ገቡ

ነሐሴ 25/2014 (ዋልታ) የቻይና ጦር በሩሲያ ግዛት ውስጥ በሚካሄደው ወታደራዊ ልምምድ ላይ ለመሳተፍ ሞስኮ መድረሱ ተነግሯል።

የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር በለቀቀው የቪዲዮ ምስል ላይ የቻይና ጦር ለግዙፉ ወታደራዊ ልምምድ ዝግጅት ሩሲያ መድረሱ ታይቷል።

ቮስቶክ 2022 የሚል መጠሪያ የተሰጠው ወታደራዊ ልምምድ ለ7 ቀናት በሩቅ ምስራቅ ሩሲያ እና በጃፓን ባሕር ላይ እንደሚካሄድ ተገልጿል።

በዚህ ወታደራዊ ልምምድ ላይ አዘጋጇ ሩሲያን ጨምሮ ቻይና፣ ቤላሩስ፣ ታጃኪስታን፣ ህንድ፣ ሞንጎሊያ እና ሌሎችን ሀገራት ይሳተፋሉ ተብሏል።

ከሀገራቱ የተውጣጡ 50 ሺሕ ወታደሮች በልምምዱ ላይ የሚሳተፉ ሲሆን ከ5 ሺሕ በላይ የተለያዩ አይነት የጦር መሳሪያዎች ጥቅም ላይ ይውላሉ መባሉን አል ዐይን ዘግቧል፡፡

ከጦር መሳሪያዎቹ መካከልም 140 የጦር አውሮፕላኖች እና 60 የጦር መርከቦች እንደሚገኙበትም የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር መግለጫ አመላክቷል።
ለፈጣን መረጃዎች:-
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth

አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን!
3.1K views09:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 12:47:09
የኢትዮጵያ አየር መንገድ 5 ቢሊየን ዶላር ገቢ ማግኘቱን አስታወቀ

ነሐሴ 25/2014 (ዋልታ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ በተጠናቀቀው 2014 በጀት ዓመት 5 ቢሊየን የአሜሪ ዶላር ገቢ ማግኘቱን አስታወቀ፡፡

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ በስሩ የሚገኙ ተቋማትን የ2014 በጀት ዓመት አፈጻጸም እና የ2015 ቀጣይ አቅጣጫዎችን ገምግሟል፡፡

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈፃሚ መስፍን ጣሰው አየር መንገዱ ባለፈው በጀት ዓመት በዓለም አቀፍ ደረጃ የተከሰተውን የኢኮኖሚ ቀውስ ተቋቁሞ 5 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር ገቢ ማግኘቱን ተናግረዋል፡፡

ኩባንያው በበጀት ዓመቱ 6 ሚሊየን 900 ሺሕ በላይ ዓለም አቀፍ መንገደኞችን ያጓጓዘ ሲሆን 7 ሺሕ 700 ቶን የጭነት አገልግሎት መስጠቱም ተመላክቷል፡፡

የተገኘው ገቢ ከ2013 በጀት ዓመት ጋር ሲነጻጸርም 79 በመቶ ጭማሪ ማሳየቱን ነው ዋና ሥራ አስፈጻሚው የገለጹት፡፡

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ማሞ ምህረቱ በአፍሪካ ቀዳሚ የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን፣ የነዳጅ ዋጋ ጭማሪን እና ሌሎች ተግዳሮቶችን ተቋቁሞ ያስመዘገበው ውጤት የሚያበረታታ እንደሆነ መግለፃቸውን ኤፍቢሲ ዘግቧል፡፡
ለፈጣን መረጃዎች:-
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth

አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን!
3.7K views09:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ