Get Mystery Box with random crypto!

Walta

የቴሌግራም ቻናል አርማ walta_tv_eth — Walta W
የቴሌግራም ቻናል አርማ walta_tv_eth — Walta
የሰርጥ አድራሻ: @walta_tv_eth
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 8
የሰርጥ መግለጫ

This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.
For more updates please visit https://www.facebook.com/waltainfo
#ሼር #በማድረግ_አጋርነታችሁን_አሳዩን

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2022-09-04 20:46:20
በመንግስታዊ የስራ ኃላፊነት ዘርፍ ግርማ ዋቄ ተሸላሚ ሆኑ

ነሐሴ 29/2014 (ዋልታ) የዓመቱ የበጎ ሰው ሽልማት መንግስታዊ ኃላፊነትን በብቃት በመወጣት ግርማ ዋቄ ተሸላሚ ሆነዋል።

አቶ ግርማ በዓለም አቀፍ ደረጃ በአቪየሽን ዘርፍ ከ50 ዓመታት በላይ ያገለገሉ ሲሆን ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ስኬቶች በርካታ አስተዋፆ ማድረጋቸውን ተነግሯል።

አሁን ላይ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቦርድ ሰብሳቢ በመሆን እያገለገሉ ነው።

በንግድና ስራ ፈጠራ ዘርፍ ደግሞ ሰኢድ መሀመድ ተሸላሚ ሆነዋል።

በአንድ የልብስ ስፌት መኪና ወደ ዘርፉ የገቡት  አቶ ሰኢድ ስራቸውን ወደ ኢንዱስትሪ በማሳደግ የአምባሳደር ሙሉ ልብስ ድርጅት ባለቤት ለመሆን የበቁ ናቸው።

በትዕግስት ዘላለም

ለፈጣን መረጃዎች፦
ፌስቡክ https://bit.ly/3Ma7QTW
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
ዩቲዩብ https://www.youtube.com/c/WaltaTV/featured
ቲዊተር https://twitter.com/walta_info
አብራችሁን ስለሆናችሁ እናመሰግናለን!
2.1K views17:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-04 20:46:20
አሸባሪው የህወሓት ቡድን የከፈተብንን ጦርነት በጋራ ለመመከት ዝግጁ ነን - የደሴ ከተማ ነዋሪዎች

ነሐሴ 29/2014 (ዋልታ) ከመከላከያ ሠራዊትና ከሌሎች የጸጥታ አካላት ጎን በመሰለፍ አሸባሪው የህወሓት ቡድን ለሶስተኛ ጊዜ የከፈተውን ጦርነት ለመመከት ቁርጠኛ መሆናቸውን የደሴ ከተማ ነዋሪዎች አስታወቁ።

የደሴ ከተማ አስተዳደር ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ዛሬ ተወያይቷል።

ከውይይቱ ተሳታፊዎች መካከል አቶ አማረ እሸቱ አሸባሪው ህወሓት ኢትዮጵያን ለማፍረስ ለሶስተኛ ጊዜ ጦርነት መክፈቱን ጠቁመው፤ ከታሪካዊ ጠላቶቻችን ጋር በመሆን የከፈተውን ጦርነት ለመመከት ቁርጠኛ መሆናቸውን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያን ሰላም ለማስጠበቅና የህብረተሰቡን ደህንነት ለማረጋገጥ ዋጋ እየከፈሉ ከሚገኙት የመከላከያ ሠራዊትና ሌሎች የጸጥታ አካላት ጎን በመሰለፍ ጠላትን ለመፋለም ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።

''የሽብር ቡድኑበሚነዛው የሀሰት ወሬ ሳንደናገጥ ስንቅና ትጥቅም እናቀብላለን፣አካባቢያችንንም ከሰርጎ ገቦች በመጠበቅ ነፃነታችንን በደምና አጥንታችን ጭምር እናረጋግጣለን'' ብለዋል።

ሌላዋ የውይይቱ ተሳታፊ ወይዘሮ ሞሚና አደም አሸባሪው ህወሓት የመንግስትን የሠላም አማራጭ ወደ ጎን በመግፋት ሀገር ለማፍረስ የጀመረውን ጦርነት በጋራ እንደሚመክቱ ተናግረዋል።

የስንቅ ዝግጅት በማድረግ ደጀንነታቸውን በተግባር እያረጋገጡ መሆናቸውን አስረድተዋል።

ለፈጣን መረጃዎች:-
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth

አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን!
2.3K views17:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-04 16:52:34
የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ትልቅ ጨዋታ ያስተናግዳል ማንችስተር ዩናይትድ ከአርሰናል

ነሐሴ 29/2014 (ዋልታ) የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ትልቅ ጨዋታ ያስተናግዳል ማንችስተር ዩናይትድ ከአርሰናል።

የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ አመሻሽ 12:30 ኦልትራፎርድ ስታዲየም ላይ ይጀምራል።

አርሰናል ከ5 ጨዋታ 15 ነጥብ በመሰብሰብ ሊጉን እየመራ ሲሆን ተጋጣሚው ማንቸስተር ዩናይትድ ከ5 ጨዋታ 9 ነጥብ በመያዝ 8ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል።

በታሪክ በተቀናቃኝነት የሚታወቁት ሁለቱ ቡድኖች በሀገራችንም በርካታ ደጋፊዎች ያሏቸው ሲሆን ጨዋታቸው በጉጉት የሚጠበቅ ነው።

በዛሬው ጨዋታ በዩናይትድ በኩል ማርሺያል በአርሰናል በኩል ቶማስ ፖርቴ በጉዳት አይሰለፍም።

እስካሁን በሁሉም ውድድሮች 237 ግዜ እርስ በእርስ ተጫውተው ማንቸስተር ዩናይትድ 98 ግዜ ድል ሲቀናው አርሴናል 86 አሸንፎ በቀሪው አቻ ተለያይተዋል።

ዛሬስ አመሻሽ 12:30 የሚጀምረው ጨዋታ ምላሽ ይሰጣል።

ለፈጣን መረጃዎች:-
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth

አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን!
896 views13:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-04 16:52:34
ምክር ቤቱ አሸባሪው ሕወሓት ወደ ሰላማዊ አማራጭ እንዲመለስ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ጫና ሊያደርግ ይገባል አለ

ነሐሴ 29/2014 (ዋልታ) የሕወሓት የሽብር ቡድን ወደ ሰላማዊ አማራጭ እንዲመለስ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ጫና እንዲያደርግ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ጠየቀ።

አንዳንድ የውጪ ኃይሎች የሽብር ቡድኑን በመደገፍ በኢትዮጵያ የውስጥ ጉዳይ ከሚያደርጉት ጣልቃገብነት እጃቸውን በመሰብሰብ የሰላም መንገድን እንዲደግፉም ምክር ቤቱ ጥሪ አቅርቧል።

53 ፓርቲዎችን በአባልነት ያቀፈው የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ዳግም የተቀሰቀሰው ጦርነት ቆሞ ሰላማዊ አማራጮች እንዲቀጥሉ ሲል የአቋም መግለጫ አውጥቷል።

መንግስት ለወሰደው የተናጠል የተኩስ አቁም ውሳኔና ጦርነቱ ሰላማዊ እልባት እንዲሰጠው በአፍሪካ ሕብረት በኩል የተጀመረው ጥረት ትልቅ ተስፋ ተጥሎበት እንደነበር የጠቀሰው መግለጫው፣ሰላማዊ አማራጩ እያለ በወርሃ ነሃሴ በአሸባሪው ሕወሓት ኅይሎች በተከፈተው ጥቃት ሳቢያ ዳግም የተቀሰቀሰው ጦርነት ምክር ቤቱን ያሳዘነ ድርጊት መሆኑን ገልጿል።

ለፈጣን መረጃዎች:-
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth

አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን!
754 views13:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-04 16:52:34
በኪነ ጥበባት የፊልም ዳይሬክቲንግ ዘርፍ ዓለምፀሀይ በቀለ ተሸላሚ ሆነች

ነሐሴ 29/2014 (ዋልታ) በ10ኛው የዓመቱ የበጎ ሰው ሽልማት በኪነ ጥበባት የፊልም ዳይሬክቲንግ ዘርፍ ዓለምፀሀይ በቀለ ተሸላሚ ሆናለች።

ዓለምፀሀይ በቀለ በቴሌቭዥን ድራማዎች፣ ትያትርና ፊልሞች ላይ በዳይሬክቲንግ፣ አማካሪነት እና በሌሎችም ስራዎች ተሳትፋለች።

ቤቶች፣ገመና ፣ ማክቤል፣ የመሸበት ይቅርታ ፣ የአና ማስታወሻ ፣ አፋልጉኝ ፣ ቪዛው ከተሳተፈችባቸው ስራዎች መካከል ጥቂቶቹ ናቸው።

እንዲሁም በጎ ያደረጉ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ዘርፍ ርብቃ ጌታቸው ሀይሌ የዓመቱ የበጎ ሰው ተሸላሚ ሆነዋል።

በኢትዮጵያ የትምህርት ጥራትን ለማምጣት የሚደረገውን ጥራት ለመደገፍ በርካታ ስራዎች መስራታቸው ተነግሯል።

ሀይሌሚናስ አካዳሚ አዳሪ ትምህርት ቤት በመክፈትም ከ9-12ኛ ክፍል ጥሩ ውጤት ያመጡ ተማሪዎችን ከመላ ሀገሪቱ በመቀበል በማስተማር ላይ ይገኛሉ።

በትምህርት ተቋማቸውም በእውቀት እና ስነ-ምግባር የታነፀ ትውልድ ለመገንባት እየሰሩ መሆናቸውም ተነግሯል።

ወ/ሮ ርብቃ በውጭ ሀገር የሚኖሩ በመሆኑ ተወካያቸው ሽልማቱን ተቀብለዋል።

ለፈጣን መረጃዎች:-
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth

አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን!
646 views13:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-04 16:52:34
አሸባሪው ሕውሓት የከፈተውን ጦርነት ለመመከት ድጋፋችንን እናጠናክራለን - የሀረሪ ክልል ወጣቶች

ነሐሴ 29/2014 (ዋልታ) አሸባሪው ሕውሓት የከፈተውን ጦርነት ለመመከት በሚከናወኑ ተግባራት ድጋፋቸውን እንደሚያጠናክሩ የሀረሪ ክልል ወጣቶች ተናገሩ።

የክልሉ ብልፅግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በክልሉ ከሚገኙ ወጣቶች ጋር ተወያይቷል።

በመድረኩ ላይ የተገኙ የክልሉ ወጣቶች መንግስት በተደጋጋሚ የሰላም አማራጮች በማቅረብ እና በሆደ ሰፊነት በመንቀሳቀስ ለሰላም ያሳየውን ቁርጠኝነት አድንቀዋል።

አሸባሪው ህውሃት የተሰጠውን የሰላም አማራጭ በመግፋት የከፈተውን ጦርነት ለመመከት በሚከናወኑ ተግባራት ከሀገር መከላከያ ሰራዊትና ሌሎች የፀጥታ አካላት ጎን በመቆም አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርጉ ገልፀዋል።

ወጣቱ በተለይም አንድነቱን ማጠናከር፣ የአካባቢውን ሰላም መጠበቅና ማህበራዊ ሚዲያን በአግባቡ መጠቀም አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመዋል።

በውይይት መድረኩ ላይ የተገኙት የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አብዱጀባር መሀመድ እንዳሉት አሸባሪው ሕወሓት በተደጋጋሚ ጊዜ የቀረበለትን የሰላም ጥሪ ወደ ጎን በመተው ለሦስተኛ ጊዜ በሀገሪቱ ላይ ጦርነት ከፍቷል።

በመሆኑም በአሁኑ ወቅት እየተካሄደ የሚገኘው ሀገርን የመታደግ ተግባር የትግራይ ህዝብን ጨምሮ መላው ኢትዮጵያውያንን ነፃ ለማውጣት መሆኑን ተናግረዋል።

ለፈጣን መረጃዎች:-
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth

አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን!
610 views13:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-04 16:52:34
በቅርስና ባህል ዘርፍ ሼክ መሀመድ አወል አምዛ ተሸላሚ ሆኑ

ነሐሴ 29/2014 (ዋልታ) የበጎ ሰው ሽልማት በቅርስና ባህል ዘርፍ ሼክ መሀመድ አወል አምዛ ተሸላሚ ሆነዋል።

ሼክ መሀመድ አወል ታሪክን በማኖርና በማቆየት እንዲሁም በሕዝበ ሙስሊሙ እንዲሁም የእምነቱ ተከታይ ባልሆኑ ጥበብ አፍቃሪ ሕዝብ ውስጥ የሚቀሩ የመንዙማ ስራዎቻቸው ከፍተኛ አስተዋፆ ማድረጋቸው ተገልጿል።

በትዕግስት ዘላለም

ለፈጣን መረጃዎች፦
ፌስቡክ https://bit.ly/3Ma7QTW
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
ዩቲዩብ https://www.youtube.com/c/WaltaTV/featured
ቲዊተር https://twitter.com/walta_info
አብራችሁን ስለሆናችሁ እናመሰግናለን!
585 views13:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-04 16:52:34
የበጎ ሰው ሽልማት በበጎ አድራጎት ዘርፍ ክብራ ከበደ ተሸላሚ ሆነዋል

ነሐሴ 29/2014 (ዋልታ) በ10ኛው የዓመቱ የበጎ ሰው ሽልማት በበጎ አድራጎት ዘርፍ ለሀገራቸውና ለሕዝባቸው ባደረጉት አስተዋፆ ክብራ ከበደ ተሸላሚ ሆነዋል።

ወ/ሮ ክብር በተለይ በፓርኪንሰን ህመም በተያዙበት ወቅት ለህመሙ የተሰጠው አነስተኛ ትኩረት ይቆጫቸው ነበር።

የፓርኪንሰን ታማሚዎች ታዲያ ህክምና ሳያገኙ በቤት እንደሚቀሩ የተገነዘቡት ወ/ሮ ክብር የፓርኪንሰን ታማሚዎች ተገቢውን ህክምና እንዲያገኙ ድጋፍ የሚያደርግ በጎ አድራጎት ማኅበር በማቋቋም በርካቶችን እረድተዋል። ይህም በበጎ አድራጎት ዘርፍ ተሸላሚ አድርጓቸዋል።

በትዕግስት ዘላለም

ለፈጣን መረጃዎች፦
ፌስቡክ https://bit.ly/3Ma7QTW
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
ዩቲዩብ https://www.youtube.com/c/WaltaTV/featured
ቲዊተር https://twitter.com/walta_info
አብራችሁን ስለሆናችሁ እናመሰግናለን!
588 views13:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-04 16:52:34
ዶ/ር ውብሸት ዠቅያለ የዓመቱ የበጎ ሰው ሽልማት በመምህርነት ዘርፍ ተሸላሚ ሆኑ

ነሐሴ 29/2014 (ዋልታ) በ10ኛው የዓመቱ የበጎ ሰው ሽልማት በመምህርነት ዘርፍ ከቀረቡ ሶስት እጩዎች መካከል ዶ/ር ውብሸት ዠቅያለ ተሸላሚ ሆነዋል።

በትዕግስት ዘላለም

ለፈጣን መረጃዎች፦
ፌስቡክ https://bit.ly/3Ma7QTW
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
ዩቲዩብ https://www.youtube.com/c/WaltaTV/featured
ቲዊተር https://twitter.com/walta_info
አብራችሁን ስለሆናችሁ እናመሰግናለን!
590 views13:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-04 16:52:34
የዓመቱ የበጎ ሰው ሽልማት ሥነ-ሥርዓት እየተካሄደ ነው

ነሐሴ 29/2014 (ዋልታ) 10ኛው የዓመቱ የበጎ ሰው ሽልማት ሥነ-ሥርዓት እየተካሄደ ነው።

ለመጨረሻ የዳኞች ውሳኔ 27 እጩዎች 1 ልዩ ተሸላሚ መለየታቸው የሚታወቅ ሲሆን ተሸላሚዎችን በእውቀታቸው እና በሞያቸው መሰረት የረዥም ጊዜ ልምድ ባላቸው ዳኞች ይመረጣሉ ተብሏል።

ኪነ-ጥበብ፣ መምህርነት፣ መንግሥታዊ የሥራ ኃላፊነት፣ ሚዲያ፣ ንግድና ሥራ ፈጠራ፣ በጎ አድራጎት፣ ዲያስፖራ፣ ቅርስና ባህል እንዲሁም ሳይንስ በሽልማት መርኃ ግብሩ የተካተቱ ዘርፎች ናቸው።

የበጎ ሰው ሽልማት ቦርድ አባል ነፃነት ተስፋዬ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አስተላልፈው ባለፉት 9 ዓመታት መርኃ ግብሮች 187 ሰዎችና ድርጅቶች እውቅና ማግኘታቸውን ገልጸዋል፡፡

አክለውም የዘንድሮው መርኃ ግብር ቁጥሩን ወደ 225 ከፍ እንደሚያደርገው ተናግረዋል።

በመርኃ ግብሩ የኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴን ጨምሮ፣ አርቲስቶች፣ አትሌቶች እንዲሁም በርካታ እንግዶች ተገኝተዋል።

በትዕግስት ዘላለም

ለፈጣን መረጃዎች፦
ፌስቡክ https://bit.ly/3Ma7QTW
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
ዩቲዩብ https://www.youtube.com/c/WaltaTV/featured
ቲዊተር https://twitter.com/walta_info
አብራችሁን ስለሆናችሁ እናመሰግናለን!
602 views13:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ