Get Mystery Box with random crypto!

Walta

የቴሌግራም ቻናል አርማ walta_tv_eth — Walta W
የቴሌግራም ቻናል አርማ walta_tv_eth — Walta
የሰርጥ አድራሻ: @walta_tv_eth
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 8
የሰርጥ መግለጫ

This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.
For more updates please visit https://www.facebook.com/waltainfo
#ሼር #በማድረግ_አጋርነታችሁን_አሳዩን

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 8

2022-08-30 20:37:37
ኢትዮጵያን የብጥብጥ ማዕከል ለማድረግ ሲሰሩ በነበሩ 111 ህገወጥ የዲጂታል ሚዲያዎች ላይ ክስ ተመስርቷል- የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን

ነሐሴ 24/2014 (ዋልታ) በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ሀሰተኛ መረጃዎችን በማሰራጨት ኢትዮጵያን የብጥብጥ ማዕከል ለማድረግ ሲሰሩ በነበሩና በመገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን ህጋዊ እውቅና በሌላቸው 111 የዲጂታል ሚዲያዎች ላይ ክስ መመስረቱን የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡

በኮሚሽኑ የታክቲክ ወንጀሎች ምርመራ ምክትል ዋና መምሪያ ሃላፊ ረዳት ኮሚሽነር ብርሃኑ አበበ፤ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በተደራጁና የሽብር ወንጀሎች፣ በሙስና፣ በፋይናንስና ንግድ ነክ፣ በታክስና ጉሙሩክ ወንጀሎች ላይ ጥቆማዎችን መነሻ በማድረግ ምርመራዎች ተከናውነዋል ብለዋል።

በዚህም መሰረት 2 ሺህ 668 ጥቆማዎችን በመቀበል 1 ሺህ 438 መዝገቦችን መርምሮ ለፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ መላካቸውንም ገልጸዋል፡፡

ከዚህ ውስጥ ሀገሪቱን የብጥብጥ ማዕከል ለማድረግ ሲሰሩ በነበሩና ሀሰተኛ የማህበራዊ ሚዲያ ስያሜ በመጠቀም ሲንቀሳቀሱ በነበሩ አካላት ላይ ክስ መመስረቱን ተናግረዋል፡፡

እነኚህ አካላት ህዝብን ለአመጽ በማነሳሳት ድብቅ ዓላማቸውን ለማሳካት ሲንቀሳቀሱ እንደነበርም በምርመራ መረጋገጡን ነው ያብራሩት።

መረጃ ተጣርቶባቸው ክስ የተመሰረተባቸው 111 የሚሆኑት የዲጂታል ሚዲያዎች በመገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን ህጋዊ እውቅና እንደሌላቸው ተናግረዋል፡፡

በአሁኑ ጊዜም የእነኚህ ህገወጥ የዲጂታል ሚዲያ ባለቤቶች በህግ ቁጥጥር ስር ውለው ጉዳያቸው እየታየ መሆኑንም ጠቅሰዋል፡፡

ለፈጣን መረጃዎች:-
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth

አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን!
4.8K views17:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-15 20:16:16
“አዋቂ” የተሰኘው የማህበራዊ ሚዲያ ጊዜውን የዋጁ እና ወጣቶችን ወደበጎ ነገር የሚመሩ አቀራረቦችን ይዞ መጥቷል ሲሉ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል ገለጹ፡፡

የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከፈርስት ኮንሰልት ጋር በጋራ ለመሥራት ስምምነት የተፈራረመ ሲሆን ÷ በፈርስት ኮንሰልት የተተገበረው “ አዋቂ” የተሰኘው የማህበራዊ ሚዲያ በይፋ ተመርቋል፡፡

በሥነ ስርዓቱ ላይ የተገኙት የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል÷ ወጣቶች በተሰራላቸው ላይ መኖር ብቻ ሳይሆን የራሳቸውንም መሥራት ይጠበቅባቸዋል ብለዋል፡፡

ለዚህም “ አዋቂ” ወጣቶችን በወጣት ቋንቋ ማናገር የሚችሉ ፣ ጊዜውን የዋጁ አቀራረቦችና ወጣቶችን በአስተሳሰብ የሚለውጡ ዘመናዊ የመገናኛ ዘዴዎችን ይዞ የመጣ መሆኑን ነው የተናገሩት፡፡

የፈርስት ኮንሰልት ስራአስኪያጅ አቶ ነቢል ኬሎ በበኩላቸው ፥ “አዋቂ” ከ 17 ዓመት በፊት የተፈጠረ ሃሳብና ለወጣቶች ዕድል የሚፈጥር መሆኑን ተናግረዋል፡፡

የማህበራዊ ሚዲያ ሥራው የግሉን ዘርፍ ወደሥራ የሚያመጣ በተለይ ወጣቶችን ለሥራ እንዲነሳሱ የተፈጠረ ጅምር በመሆኑ የወጣቶችን ክህሎት በማዳበር በኩል በጎ ሃሳቦቻቸውን የሚያጎለብት በመሆኑ ሁሉም ሊተባበር እንደሚገባ ተጠቁሟል፡፡

የ“አዋቂ “ ማህበራዊ ሚዲያዎች ወጣቶችን ማነቃቃት ብቻ ሳይሆን ሥራ እንዲያገኙና ሥራ እንዲፈጥሩ እየተሰራ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን ፥ በ 9 ወር ውስጥ ከ230 ሺህ በላይ ተከታዮችን ማፍራት እንደቻለ በሥነሥርዓቱ ላይ ተገልጿል፡፡

በአንድ ዓመት ውስጥም ከ500 ሺህ በላይ ወጣቶች እንዲከተሉትና ተሰጥኦን መሠረት ያደረጉ በጎ አስተሳሰቦችን በማስረጽ ወጣቶችን ለሥራ ንቁ ለማድረግ እንደሚሰራ መገለጹን ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ ያመክታል፡፡
ለፈጣን መረጃዎች:-
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
2.0K views17:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-15 20:16:16
ተጨማሪ 104 የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ካምፓሶችና ቅርንጫፎች ላይ እርምጃ ተወሰደ

ሐምሌ 8/2014 (ዋልታ) በተለያዩ የክልል ከተሞች በሚገኙ ግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ካምፓሶችና ቅርንጫፎች ላይ የእርምት እርምጃ መውሰዱን የኢፌዴሪ ትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን አስታወቀ፡፡

ተቋማቱ የእርምት እርምጃ የተወሰደባቸው የእውቅና ፈቃድ ባልተሰጠባቸው ካምፓሶች፣ ቅርንጫፎች እና የትምህርት መስኮች ተማሪ ተቀብለው ሲያስተምሩ፣ የእውቅና ፈቃድ እድሳት ባልተሰጠባቸው የትምህርት መስኮች መዝገበው ሲያስተምሩ በመገኘታቸው ነው ተብሏል፡፡

ከዚህ ባለፈም ተቋማቱ ባልተፈቀደበት የትምህርት አሰጣጥ ክፍለ ጊዜ ማለትም በሳምንቱ የመጨረሻ ሁለት ቀናት ቅዳሜና እሁድ እና በማታ ክፍለ ጊዜ በማስተማራቸው፣ ፈቃድ ባገኙበት ካምፓስ ላይ አለመገኘት እንዲሁም በእውቅና ፈቃድ እና በእውቅና ፈቃድ እድሳት ወቅት ተሟልተው የነበሩ ግብዓቶችን አጓድለው መገኘታቸው ተመላክቷል፡፡

ተቋማቱ የፈጠሩትን ስህተት ተከትሎም የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ ከመስጠት ጀምሮ በፕሮግራም፣ በካምፓስና በተቋማት ደረጃ የእውቅና ፈቃዳቸው ተሰርዞ ሙሉ ለሙሉ የተዘጉ እንዳሉም ባለሥልጣኑ አስታውቋል።

በ2014 ዓ.ም ብቻ በአዲስ አበባ 106፣ በክልል ከተሞች በ1ኛ ዙር 95 እና በ2 ዙር 104 ፤ በድምሩ በሀገር አቀፍ ደረጃ የመመሪያ ጥሰት በተገኘባቸው 305 የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ ካምፓሶች እና ቅርንጫፎች ላይ የእርምት እርምጃ በመውሰድ ለሕዝብ ይፋ መደረጉ ተጠቁሟል፡፡

ለፈጣን መረጃዎች:-
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth

አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን!
1.6K views17:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-15 20:16:16
በቀጣይ ዓመት በ70 የትምህርት ፕሮግራሞች የመውጫ ፈተና እንደሚሰጥ ተገለጸ

ሐምሌ 8/2014 (ዋልታ) የትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ የአስተዳደርና መሠረተ ልማት መሪ ሥራ አስፈጻሚ ሰለሞን አብረሃ (ዶ/ር) ከቀጣይ ዓመት ጀምሮ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተመራቂ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና በ70 ፕሮግራሞች መሰጠት እንደሚጀምር ገልጸዋል።

ሥራ አስፈፃሚው ይህን የተናገሩት የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ የ2014 ዓ.ም በጀት ዓመት የእቅድ አፈጻጸም ሪፖርት እና የ2015 ዓ.ም በጀት ዓመት እቅድ በቀረበበት ወቅት ነው፡፡

በጦርነቱ የወደሙ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን መልሶ በማቋቋም ወደ ሥራ ማስገባት መቻሉ በ2014 በጀት ዓመት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ርብርብ እና ጠንካራ ትብብር የታየበት መሆኑ ተገልጿል።

በትግራይ ክልል ዩኒቨርሲቲዎች ይማሩ የነበሩ እና በጦርነቱ ምክንያት የወጡ ተማሪዎችን በሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ምደባ በመስጠት ትምህርታቸውን የማስቀጠል ሥራ ውጤታማ እንደነበርም ተጠቅሷል፡፡

የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ዓለም አቀፋዊ አጋርነት እየጎለበተ መምጣቱ ለቀጣይ ዓመት የእቅድ አፈጻጸም ስኬት በምቹ ሁኔታነት ተገምግሟል፡፡

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የኦድት ግኝቶችን ለመቀነስ በከፍተኛ ትኩረት እየተሠራ መሆኑ ተገልጾ የሚመለከታቸው የመንግሥት አካላትም የግዥ ሥርዓት መመሪያዎችን ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተጨባጭ ሁኔታና ባህሪያት በተለይም ከተማሪዎች አገልግሎትና ምርምር ሥራዎች አንጻር መልሰው ቢቃኙት ጥሩ እንደሚሆን አስተያየት ተሰጥቷል፡፡

በቀጣይ ዓመት በ70 የትምህርት ፕሮግራሞች ለሚሰጠው የመውጫ ምዘና ከወዲሁ ዝግጅት እንደሚደረግ የሚኒስቴሩ መረጃ አመላክቷል፡፡

ለፈጣን መረጃዎች:-
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
1.4K views17:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-15 20:16:16
ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ የኦሮሚያ ክልል ለአገራዊ ምክክሩ ስኬት አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል አሉ

ሐምሌ 8/2014 (ዋልታ) የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ለአገራዊ ምክክሩ መሳካት አስፈላጊው ድጋፍ እንደሚያደርግ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ አረጋገጡ፡፡

ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ ከአገራዊ የምክክር ኮሚሽኑ አባላት ጋር ዛሬ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል፡፡

ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ ኢትዮጵያ በተለያዩ ፈተናዎች ብትፈተንም ችግሮቹን ወደ ዕድል እየለወጠች እንደምትገኝ አስረድተዋል፡፡

በቀጣይም የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን በሕዝቦቿ አንድነት እና ትብብር በመቅረፍ አመርቂ ውጤት እንደምታስመዘግብም ያላቸውን እምነት ገልጸዋል፡፡

አገራዊ ምክክሩ በግልጽነት እና በፍትሃዊነት ያለምንም የፖለቲካ ጫና ሕዝቦችን በማሳተፍ መካሄድ እንዳለበትም ነው የጠቆሙት፡፡

የኦሮሞ ሕዝብ ሰላም እና ልማት ወዳድ እንደመሆኑ መጠን ለአገራዊ ምክክሩ ስኬት ከኮሚሽኑ ጎን እንደሚቆም አረጋግጠዋል፡፡

አገራዊ የምክክር ኮሚሽን ዋና ሰብሳቢ መስፍን አርአያ (ፕ/ር) በበኩላቸው አገራዊ ምክክሩ በአገራዊ ጉዳዮች የሕዝቦችን አስተያየት መሰረት በማድረግ ነፃ፣ አካታች እና ታአማኒ በሆነ መልኩ እንደሚካሄድ ተናግረዋል፡፡

በአፋን ኦሮሞ የተተረጎመውን የአገራዊ ምክክር ኮሚሽን አዋጅም ለርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ ማስረከባቸውን የክልሉን ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ ጠቅሶ ኤፍቢሲ ዘግቧል፡፡
ለፈጣን መረጃዎች:-
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth

አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን!
1.3K views17:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-15 20:16:16
ኢትዮጵያ ድርቅን ለመቋቋም ከጎረቤት ሀገራት ጋር ተቀናጅታ እየሠራች መሆኗ ተገለጸ

ሐምሌ 8/2014 (ዋልታ) ኢትዮጵያ ድርቅን ለመቋቋም ከጎረቤት ሀገራት ጋር በቅንጅት እየሠራች መሆኗን የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ ገለጹ፡፡

የፓርቲው ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ የተባበሩት መንግሥታት ዋና ፀሐፊ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ሃና ቴተህ ጋር ተወያይተዋል፡፡

በውይይታቸውም በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የመከሩ ሲሆን በአፍሪካ ቀንድ በአየር ንብረት መዛባት ምክንያት ያጋጠመውን ድርቅ ለመቋቋም ኢትዮጵያ በሀገር ውስጥ እየተገበረች ያለውን የአረንጓዴ ዐሻራ መርኃ ግብር የማስፋፋት ዕቅድ አውጥታ ከጎረቤት ሀገራት ጋር በቅንጅት እየሠራች መሆኑን አመልክተዋል፡፡

የተባበሩት መንግሥታት ለዚህ የኢትዮጵያ ዕቅድ ድጋፍ እንዲያደርግም ልዩ መልዕክተኛዋን ጠይቀዋል፡፡

በትግራይ ክልል የተፈጠረውን ግጭት በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት በብልጽግና ፓርቲ የሚመራው መንግሥት ዝግጁ መሆኑን ጠቁመው በመንግሥት በኩል እስካሁን የተደረጉ ጥረቶችን እና የሰላም አማራጩ እውን እንዲሆን የተወሰዱ እርምጃዎችን ገልጸዋል፡፡
ለፈጣን መረጃዎች:-
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth

አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን!
1.3K views17:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-15 20:16:16
በመዲናዋ ለ24 ዘመናዊ ሆስፒታሎች ግንባታ የሚውል መሬት መሰጠቱ ተገለጸ

ሐምሌ 8/2014 (ዋልታ) አዲስ አበባን የጤና ቱሪዝም ተደራሽ ለማድረግ ለ24 ዘመናዊ ሆስፒታሎች ግንባታ የሚውል መሬት መስጠቱን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ፡፡

የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በጤና ዘርፍ የተሠሩትን ሥራዎች ለአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት አቅርበዋል፡፡

በሪፖርታቸውም የእናቶች እና የሕጻናት ሞትን ለመቀነስ በወሊድ ጊዜ በባለሙያ የታገዘ የወሊድ አገልግሎት ለ152 ሺሕ 990 እናቶች በባለሙያ የታገዘ የወሊድ አገልግሎት መሰጡትን ጠቅሰው የድህረ ወሊድ ክትትል ለማድረግ ለ156 ሺሕ 94 የአገልግሎቱ ተጠቃሚ በማድረግ የእናቶችን ሞት መቀነስ መቻሉን ገልጸዋል፡፡

የማኅበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን ሽፋንም 81 ነጥብ 3 በመቶ ማሳካት መቻሉን ከንቲባዋ አብራርተዋል።

ከፍለው መታከም ለማይችሉ ወገኖች 83 ሚሊየን ብር ወጪ በማድረግ 28 ሺሕ 882 የቤተሰብ አባላት የህክምና አገልግሎት እንዲያገኙ መደረጉንም አንስተዋል፡፡

የመድኃኒትና የህክምና መሳሪያዎች መናር ጋር በተያያዘ ከከተማ አስተዳደሩ በጀት 181 ነጥብ6 ሚሊየን ብር ድጎማ መደረጉንም ነው ገለጹት፡፡

የኩላሊት ህክምና የተደራሽነትና የአቅርቦት ችግርን ለመቅረፍ ከአጋር ድርጅት ጋር በመሆን 30 አዳዲስ የኩላሊት እጥበት ማሽኖችን በማስገባት በዳግማዊ ምኒልክ ሆስፒታል ሥራ መጀመሩን ጠቁመው ይህም የከተማውን የኩላሊት እጥበት አቅም በአምስት እጥፍ ማሳደግ መቻሉን ተናግረዋል።

ለፈጣን መረጃዎች:-
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth

አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን!
1.3K views17:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-15 20:16:16
ከ9 ሺሕ በላይ የሽጉጥ ጥይት ከእነ ተጠርጣሪዎቹ ተያዘ

ሐምሌ 8/2014 (ዋልታ) የአዲስ አበባ ፖሊስ እና የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት በጋራ በመቀናጀት ባደረጉት ክትትል ከ9 ሺሕ በላይ የሽጉጥ ጥይት ከእነ ተጠርጣሪዎቹ መያዛቸውን አስታወቁ፡፡

የጦር መሳሪያ ዝውውሩን ለመቆጣጠር እየተሰራ ያለው ሥራ ተጠናክሮ መቀጠሉን ከአዲስ አበባ ፖሊስ ያገኘነው መረጃ አመላክቷል፡፡

መነሻውን ባሕርዳር ከተማ ያደረገ የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 3-98555 አ/አ ኤፍ.ኤስ.አር ተሽከርካሪ ላይ ከጫት ጋር በማድረግ በማዳበሪያ ተጭኖ ወደ አዲስ አበባ የገባ ጥይት በጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ልዩ ቦታው አጂፕ ቶታል አካባቢ ሐምሌ 7 ቀን 2014 ዓ.ም ከጠዋቱ 2 ሰዓት እጅ ከፍንጅ እንደተያዘ ፖሊስ አስታውቋል፡፡

ጥይቱን ሲያዘዋውሩ የተገኙ አራት ተጠርጣሪዎች እና ለህገ-ወጥ ተግባር የተገለገሉበት አንድ ተሽከርካሪ በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራው መቀጠሉም ተገልጿል፡፡

ለፈጣን መረጃዎች:-
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth

አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን!
1.5K views17:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-15 16:38:52
በመጪው የትምህርት ዘመን ከመመሪያው ውጭ ወርሃዊ የክፍያ ጭማሪ ማድረግ በሕግ ያስጠይቃል

ሐምሌ 8/2014 (ዋልታ) ትምህርት ቤቶች በ2015 የትምህርት ዘመን ከመመሪያው ውጭ ወርሃዊ የክፍያ ጭማሪ ማድረግና ሌሎች የአገልግሎት ክፍያ እንዳይጠይቁ የአዲስ አበባ የትምህርትና ሥልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለሥልጣን አሳሰበ።

የባለሥልጣኑ ምክትል ሥራ አስኪያጅ ፍቅርተ አበራ እንደገለጹት ከመመሪያው ውጭ የክፍያ ጭማሪ በሚያደርጉ የግል ትምህርት ቤቶች ላይ እርምጃ ይወሰዳል።

መመሪያው በ2014 ዓ.ም ጭማሪ ያደረጉ የግል ትምህርት ቤቶች በ2015 የትምህርት ዘመን ምንም አይነት ጭማሪ እዳያደርጉ ያዛል።

ነገር ግን መመሪያውን በመጣስ አንዳንድ የግል ትምህርት ቤቶች አስቀድመው በደብዳቤና በተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎች ጭማሪ እንደሚያደርጉ ለወላጆች መልዕክት እያስተላለፉ መሆኑ ተደርሶበታል ብለዋል።

መመሪያውን በሚጥሱ ትምህርት ቤቶች ላይ ፈቃድ የመሰረዝና በሕግ የማስጠየቅ እርምጃዎች እንደሚወስድ ከወዲሁ አሳስበዋል።
ለፈጣን መረጃዎች:-
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth

አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን!
2.4K views13:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-15 16:38:52
ተማሪ ቢንያም የሕክምና ትምህርቱን እንዲቀጥል ተወሰነ

ሐምሌ 8/2014 (ዋልታ) ተማሪ ቢንያም ኢሳያስ የሕክምና ትምህርቱን እንዲቀጥል ተወስኗል።

የተማሪ ቢንያም ኢሳያስን ትምህርት በተመለከተ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ እና የሕክምና ትምህርት ቤት ለተማሪው የትምህርት ሂደት ይረዳሉ ያሏቸውን አማራጮች ማቅረባቸው ይታወሳል።

ሆኖም ተማሪ ቢንያም ብቸኛ ፍላጎቱ የሕክምና ትምህርትን መማር እንደሆነ ገልጿል።

በዚሁም መሠረት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና የጤና ሳይንስ ኮሌጅ አካዳሚክ ኮሚሽን በጋራ ባካሄዱት ስብሰባ ተማሪ ቢንያም ኢሳያስ የሕክምና ትምህርቱን እንዲቀጥል ተወስኗል።

እስካሁን የተቋረጡ ትምህርቶችንም በማካካስ ትምህርቱን ካቆመበት እንዲቀጥል ይደረጋል መባሉን ከዩኒቨርሲቲው የጤና ሳይንስ ኮሌጅ ያገኘነው መረጃ አመላክቷል፡፡
ለፈጣን መረጃዎች:-
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth
ቴሌግራም https://t.me/WALTA_TV_Eth

አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን!
2.0K views13:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ