Get Mystery Box with random crypto!

የዛሬ መረጃ ®

የቴሌግራም ቻናል አርማ todaynewsethiopia — የዛሬ መረጃ ®
የቴሌግራም ቻናል አርማ todaynewsethiopia — የዛሬ መረጃ ®
የሰርጥ አድራሻ: @todaynewsethiopia
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 42.26K
የሰርጥ መግለጫ

#መረጃ_አይናቅም ‼️
ትኩስ ና አዳዲስ የሀገር ውስጥ ና የአለም ዜናዎችን በፍጥነት ሰብስበን ወደናንተ እናደርሳለን Today News Ethiopia።
መረጃዎች ለወዳጅ ዘመድዎ ሼር በማድረግ አብሮነታችሁ ያሳዩ
#ለእውነት ና #ለትክክለኛ #መረጃ ብቻ እንሰራለን።

Ratings & Reviews

3.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

2

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 10

2023-03-15 21:40:59
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ ከአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ቢሊንከን ጋር ተወያዩ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ዛሬ ረፋድ ላይ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከንን ተቀብለው አነጋግረዋል።

ውይይታቸውም በተለያዩ የሀገር ውስጥ፣ ቀጣናዊ እና የሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ሲሆን፥ በኢትዮጵያ እና በዩናይትድ ስቴትስ መካከል ያለውን ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ ተስማምተዋል።

ኢትዮጵያ በሰላም ስምምነቱ ላይ እያስመዘገበች ያለችው ስኬት ተቀባይነት አግኝቷል። በኢኮኖሚው፣ በልማት ጥረቶች፣ በተለይም በግብርና እና በቀጣናዊ መረጋጋት ላይ ያሉ ጉዳዮችም ትኩረት መሰጠቱን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ገልጸዋል።
5.5K views18:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-14 20:21:47
አስገድዶ መድፈር ወንጀል የፈፀመው ተከሳሽ በእስራት ተቀጣ።

ተከሳሽ አንተነህ ተዘራ የተባለው ግለሰብ ታህሳስ 8/2015ዓም ከምሽቱ 3 00ሰአት ላይ በሐረር ከተማ አቦከር ወረዳ ልዩ ስፍራው ወርዋሪ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የ19አመት ወጣት የሆነችውን አስገድዶ በመድፈሩ በእስራት መቀጣቱን የሴቶችና ህፃናት መርማሪ የሆኑት ሣጅን አዚዛ አህመድ ገልፀዋል ።

መርማሪዋ እንደገለፁት ተከሳሹ የ19አመት እድሜ ያላትን ወጣት የሚስቱን ጓደኛ ሚስቴ የምሰራበት ቦታ ልትጠይቀኝ መታለችና ነይ አንቺም እኛጋር ታድሪያለሽ በማለት አታሎ በመውሰድ ሀይል በመጠቀም የግብረስጋ ግንኙነት የፈፀመባት በመሆኑ በፈፀመው አስገድዶ መድፈር ወንጀል ተከሶ በሐረሪ ክልል ከፍተኛ ፍርድቤት የካቲት 28/2015ዓም በዋለው ችሎት ተከሳሽ አንተነህ ተዘራ በ 5አመት ከ 6ወር እስራት እንዲቀጣ ተወስኖበታል ሲሉ የህፃናትና ሴቶች ወንጀል መርማሪ የሆኑት ሳጅን አዚዛ አህመድ ገልፀዋል።
365 views17:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-14 08:41:03 የዘንድሮው የሐጅ ጉዞ ምዝገባ በ11 የምዝገባ ጣቢያ እንደሚካሄድ ተገለጸ

የዘንድሮው የሐጅ ጉዞ ምዝገባ በ11 የምዝገባ ጣቢያ እንደሚካሄድ የኢትዮጵያ የእስልምና ጠቅላይ ምክር ቤት አስታወቀ፡፡የዘንድሮው የሐጅ ጉዞ የሑጃጆችን እንግልት ለመቀነስ የምዝገባ ጣቢያዎች ሑጃጁ በአቅራቢያው በሚገኘው የምዝገባ ጣቢያዎች እንደሚከናወን ነው የተገለጸው፡፡

ላለፉት 10 ዓመታት የሑጃጆች ቁጥር መረጃ ሰነድ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።በዚህም መሠረት 11 የምዝገባ ጣቢያዎች የሚከፈቱ ሲሆን÷ እንደ ሁኔታው የምዝገባ ጣቢያዎቹ ቁጥር ሊጨምር እንደሚችል ተመላክቷል፡፡

ከቀናት በኋላ የሚጀመረው የዘንድሮው የሐጅ ጉዞ ምዝገባ ለመመዝገብ ተመዝጋቢው በአካል መገኘት ይኖርበታልም ተብሏል፡፡በዚሁ መሰረት ÷ የአገልግሎት ጊዜው ለመጠናቀቅ ከስምንት ወራት በላይ ጊዜ የቀረው የጉዞ ሰነድ (ፖስፖርት)፣ አንድ ጉርድ ፎቶ ግራፍ፣ የኮቪድ19 ክትባት ማስረጃ ማቅረባቸው ሲረጋገጥ የአገልግሎት ክፍያ በባንክ እንዲከፍሉ ይደረጋል ነው የተባለው፡፡

በቡድን (በጀምዓ) መጓዝ የሚፈልጉ ሑጃጆች 50 ሰዎች በአንድ ቡድን ሆነው ተደራጅተው መመዝገብ እንደሚችሉም ተገልጿል።ለትውልደ ኢትዮጵያውያን ሑጃጆች ምዝገባ በጠቅላይ ምክር ቤቱ የምዝገባ ጣቢያ ብቻ ይከናወናል መባሉን ከኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

http://t.me/TodayNewsEthiopia
2.5K views05:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-10 22:55:29 የዓረብ ሊግ የሕዳሴ ግድብን በተመለከተ ያወጣውን መግለጫ ኢትዮጵያ እንደማትቀበል ገለፀች

የዓረብ ሊግ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ እና የውሃ ሙሌትን በተመለከተ በትናንትናው ዕለት ያወጣውን የአቋም መግለጫ ኢትዮጵያ እንደማትቀበል ገልጻለች፡፡

ሊጉ በትናንትናው ዕለት ለግብጽ አቋም የወገነ መግለጫ ማውጣቱ የሚታወቅ ሲሆን ፥ ጉዳዩን አስመልክቶ የኢትዮጵያ መንግስት መግለጫ ሰጥቷል፡፡

በመግለጫውም የሕዳሴ ግድብ የግንባታ ሥራና የውሃ ሙሌትን የማስተዳደር ስራ ለሚመለከታቸው የተፋሰሱ የአፍሪካ ሀገራት ሊተው እንደሚገባ አንስቷል።
2.3K views19:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-10 17:10:20
በኢትዮጵያ በተወሰኑ የማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች ላይ የተደረገው ክልከላ እንዲነሳ አምነስቲ ጠየቀ

ኢትዮጵያ ውስጥ የቴሌግራም፣ ፌስቡክ ፣ ዩትዩብ መሰል የማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች እስካሁን ምክንያቱ ግልፅ ባልተደረገበት ሁኔታ ገደብ ከተደረገባቸው ዛሬ 29ኛ ቀኑን ይዟል።

ይህን አስመልክቶ ዓለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት አምነስቲ ኢንተርናሽናል እገዳው በአስቸኳይ እንዲነሳ ጠይቋል።

አምነስቲ የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት «በሰዎች ራሳቸውን የመግለጽና መረጃ የመፈለግና የማግኘት መብት ጣልቃ የመግባት ልምዳቸውን እንዲያቆሙ»ም አሳስቧል።

ከዚህ ቀደም የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለ በማኅበራዊ ትስስር ዘዴዎች ላይ የተደረገው እገዳ እንዲነሳ መጠየቃቸው ይታወሳል።
1.2K views14:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-08 23:05:21 በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከነገ ጀምሮ የባጃጅ ትራንስፖርት አገልግሎት ተከለከለ

ከነገ ጀምሮ በከተማዋ በየትኛውም አካባቢ ላልተወሰነ ጊዜ የባጃክ አገልግሎት መከልከሉን የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ አስታውቋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት ቢሮ "የባጃጅ ትራንስፖርት አገልግሎት አሰጣጥን በተሻለ መልክ ለመምራት እንዲያስችል አሰራር ማሻሻያ ስራዎችን በማከናወን ላይ እገኛለው" ብሏል።

የአሰራር ማሻሻያ ስራው ተጠናቆ እንዲሁም የአገልግሎቱ አስፈላጊነት በዝርዝር ተጠንቶ ውሳኔ እስኪያገኝ ድረስ ከነገ የካቲት 30/2015ዓ.ም ጀምሮ በከተማዋ በየትኛውም አከባቢ ላልተወሰነ ጊዜ የባጃጅ ትራንስፖርት አገልግሎት የታገደ መሆኑን ቢሮው አሳውቋል።

http://t.me/TodayNewsEthiopia
925 views20:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-08 16:43:41 ከጎረቤት ጋር የጀመረችውን ፍቅር ስላወቀባት ልጇን የተመረዘ በሶ አጠጥታ ህይወቱ እንዲያልፍ ያደረገችው እናት!

በደቡብ ክልል ወላይታ ዞን ሶዶ ዙሪያ ወረዳ በአይጥ መርዝ የተመረዘ በሶ ለልጇ አጠጥታለች የተባለችዉ የ32 ዓመቷ ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር መዋሏ ፖሊስ አስታወቀ።

በዞኑ ሶዶ ዙሪያ ወረዳ ቶሚ ገረራ ቀበሌ ነዋሪ የሆነችዉ ወይዘሮ ጎረቤት ከሚገኝ አባወራ ጋር በድብቅ የፍቅር ግንኙነት መጀመሯ በሰዎች ዘንድ የሚወራዉ ወሬ ከ16 አመቱ ታዳጊ ልጇ ጆሮ ገብቶ ኖሮ የሰማዉን ነገር በአይኑ አይቶ ለማረጋገጥ በትእግስት ነገሩን ሲከታተል ቆይቷል።

ልጅ እናቱ በመንደርተኛዉ የታማችበትን የፍቅር ግንኙነት ትክክል መሆኑ የእርግጠኛ በሆነ ጊዜ በምድራዊ ህይወት መልካም ስምና ክብርን የሚያኮስስ በሰማያዊዉ ቤትም የፈጣሪን ህግ በመጣስ የሚያስጠይቅ ነዉና ልጅ ለእናቱ የእናትነት ክብር ሳይነፍግ በትህትና ቀርቦ መክሮ ሊመልሳት በሞከረ ጊዜ በእሺታ ተቀብላዉ ነበር።

የልጇን ምክር ተቀብላ በእሺታዋ ከመፅናት ይልቅ የእሱን ምክር ወደጎን ትታ ከሰዉየዉ ጋር የነበራትን ግንኙነት አጠናክራ ቀጠለች በዚህም በሰዉ ትዳር ላይ ተደርባ የጀመረችዉ ፍቅር እናቱን ሊያሳጣዉ እንደሚችል ስጋት የገባዉ ልጅ በድጋሚ እናቱን መክሮ ሊመልስ ጥረት ማድረጉ ቀጠለ።

እናት ከጎረቤት የምትሰማዉ የፍቅር ቋንቋ ከልጇ ምክር ጋር ስታነፃፅረዉ የልጇ ምክር ለጆሮዋ ያልተመቸ ሆኖ ቢሰማት የጀመረችዉ የፍቅር ግንኙነት ከማቋረጥ ይልቅ ልጇን ከአጠገቧ ገለል ልታረገዉ ከዉሳኔ ደረሰች።

የካቲት 23 ቀን 2015 ዓ.ም ከቀኑ 7:00 ሰዓት አካባቢ የ16 ዓመቱ ታዳጊ ከወላጅ እናቱ የቀረበለት ቤት ያፈራዉን ማእድ ከቀማመሰ በኋላ ለተመገበዉ ምግብ ማወራረጃ ይሆን ዘንድ ያዘጋጀችለት በሶ ጠጥቶ ፈጣሪዉንም እናቱንም አመስግኖ ከቤት ወጣ ይላል።

ታዳጊዉ ከደቂቃዎች በኋላ ከወደ ሆዱ በሚሰማዉ የህመም ስሜት ምክንያት ፊቱን ላብ አጥምቆት እራሱን ስቶ ይወድቅና ነብስ ዉጪ ግቢ ጭንቀቱ በረታ።

የአካባቢዉ ህብረተሰብ ታማሚዉን አፈፍ አድርጎ በፍጥነት ነበር ሶዶ ክርስቲያን ሆስፒታል ያደርሱታል። ሀኪሞች የወጣቱ ዉስጥ መመረዙ በሁኔታዉ በመረዳታቸዉ ህይወቱን ለማትረፍ አስፈላጊዉ ህክምና ቢያደርጉለትም ከቆይታ በኋላ የወጣቱ ህይወት ማለፉ እዉን ሆነ።

እናት ዘጠኝ ወራትን በሆዳ አመታትን በጀርባዋ ተሸክማ የደሟ ተዋፅኦ የሆነዉን ወተት ከጡቶችዋ እያስማገች የምታሳድግ አሳድጋም ለቁምነገር ለማብቃት ስለ ፍቅሯ ዋጋ የምትኸፍል መሆኗ የሚታወቅ ሀቅ ነዉ።

በሶዶ ዙሪያ ወረዳ የቶሚ ገረራዋ እናት ግን ለልጇ ከምግብ በኋላ ለማወራረጃነት በሰጠችዉ የተበጠበጠ በሶ ዉስጥ የአይጥ መርዝ አድርጋበት ኖሮ ለዘለአለሙ መልሳ ላታገኘዉ የአብራኳ ክፋይ እንዲህ ባለ ጭካኔ እቺን አለም ሊሰናበት የግድ ሆነ።

እቺህ ተጠርጣሪ ልጇን የሰዋችለት የጎረቤት ፍቅር ከነ አካቴዉ መልሳ ላታገኘዉ እንደምትችል አልጠረጠረችምና አሁን በፈፀመችዉ የግድያ ወንጀል ተጠርጥራ ፖሊስ በቁጥጥር ስር አዉሎ ምርመራ ማጣራት ጀምሯል።

ከሀለት ያጣች ሆና በድርጊቷ ብትፀፀት የፈሰሰ ዉሃ አይታፈስም አይነት ግራ ተጋብቶ ዉስጥን ጭንቀት ቢሞላዉ ዉጤቱ የዜሮ ብዜት ነዉና ምንስ ሊፈይ መረጃው የደቡብ ፖሊስ ኮሚሽን ነው።
http://t.me/TodayNewsEthiopia
3.0K views13:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-07 19:20:26
የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በነበረበት ይቀጥላል፦ የንግድ እና ቀጠናዊ ትሥሥር ሚኒስቴር

ከአውሮፕላን ነዳጅ ውጪ የሌሎች ነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በነበረበት እንደሚቀጥል የንግድ እና ቀጠናዊ ትሥሥር ሚኒስቴር በላከው መግለጫ አስታወቀ።

http://t.me/TodayNewsEthiopia
2.3K viewsedited  16:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-05 11:10:59 አዋሽ ባንክ በቦረና ዞን በድርቅ ለተጎዱ ዜጎች 30 ሚሊየን ብር ድጋፍ አደረገ

አዋሽ ባንክ በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ቦረና ዞን በድርቅ ለተጎዱ ዜጎች የ30 ሚሊየን ብር ድጋፍ አደረጉ።

አዋሽ ባንክ ባለፈው ዓመትም በቦረና እና ጉጂ ዞኖች በድርቅ ለተጎዱ ወገኖች 60 ሚሊየን ብር መለገሱን ከባንኩ ማኅበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ አመላክቷል። ባንኩ ከዚህ ቀደም በምዕራብ ኦሮሚያ ተከስቶ በነበረው ግጭት ተፈናቅለው ለነበሩ ዜጎችና በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ንፋስ ቀላቅሎ በጣለው ከባድ ዝናብ ቤት ለፈረሰባቸው ዜጎች የገንዘብ ድጋፍ ማድረጉንም አስታውሷል።

http://t.me/TodayNewsEthiopia
3.4K views08:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-03 14:56:56
አሜሪካ ከቻይና ጋር ወደ ጦርነት መግባቷ እርግጥ ወደ መሆኑ መቃረቡን አስታውቃለች::

ዋሽንግተን ከቻይና ጋር ሊኖራት ስለሚችለው ጦርነትም እቅድ በማውጣት ላይ እንደምትገኝ ነው የተነገረው።

የአሜሪካ መከላከያ ሚንስትር ዋና ጸሀፊ ክሪስቲን ዋርሙዝ ጦርነቱ አይቀሬ መሆኑን የሚያሳይ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

ከቢጂንግ ጋር የሚደረገውን ጦርነት በድል ለመደምደምም አሜሪካ ተጨማሪ ወታደሮቿን በእስያ ለማስፈርና የበይነ መረብ ጥቃቶችን በስፋት ለማካሄድ ስለማሰቧ ዋና ጸሃፊው ተናግረዋል።

http://t.me/TodayNewsEthiopia
1.9K viewsedited  11:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ