Get Mystery Box with random crypto!

የዛሬ መረጃ ®

የቴሌግራም ቻናል አርማ todaynewsethiopia — የዛሬ መረጃ ®
የቴሌግራም ቻናል አርማ todaynewsethiopia — የዛሬ መረጃ ®
የሰርጥ አድራሻ: @todaynewsethiopia
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 42.26K
የሰርጥ መግለጫ

#መረጃ_አይናቅም ‼️
ትኩስ ና አዳዲስ የሀገር ውስጥ ና የአለም ዜናዎችን በፍጥነት ሰብስበን ወደናንተ እናደርሳለን Today News Ethiopia።
መረጃዎች ለወዳጅ ዘመድዎ ሼር በማድረግ አብሮነታችሁ ያሳዩ
#ለእውነት ና #ለትክክለኛ #መረጃ ብቻ እንሰራለን።

Ratings & Reviews

3.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

2

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2023-06-13 09:23:41
በአዲስ አበባ ወንዝ ዉስጥ የገባው የ45 ዓመት ሰዉ አስከሬን ከ2 ሰዓታት ፍለጋ በኃላ ተገኘ

አንበሳ ጋራዥ ላይ በደረሰ የእሳት አደጋ አራት አዉቶቢሶች ተቃጥለዋል


ማክሰኞ ሰኔ 6 ቀን 2015 (አዲስ ማለዳ) ትላንት ሰኔ 5/2015 በአዲስ አበባ ከተማ፣ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 ልዩ ቦታዉ ተባበር በርታ እየተባለ በሚጠራዉ አካባቢ በሚገኝ ወንዝ ዉስጥ እድሜዉ 45 ዓመት የተገመተ ሰዉ ሕይወቱ አልፎ መገኘቱን የእሳትና አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል።

የኮሚሽን መ/ቤቱ ጠላቂ ዋናተኞች ከኹለት ሰዓት ፍለጋ በኋላ ከምሽቱ 12:00 ሰዓት ሲሆን አስከሬኑን አግኝተዉ ለፖሊስ ማስረከባቸው ተገልጿል።

በሌላ በኩል፤ በዚያዉ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተ ወረዳ 5 አንበሳ ጋራዥ ላይ በደረሰ የእሳት አደጋ አራት አዉቶቢሶች መቃጠላቸውን ኮሚሽኑ አስታውቋል።

የእሳት አደጋዉ የአጋጠመዉ የአንበሳ አዉቶቢስ የተሽከርካሪዎች ጥገና ጋራዥና የነዳጅ መቅጃ ማዕከል ላይ ሲሆን፤ የተቃጠሉት አዉቶቢሶች ከቅጥር ጊቢ ዉጭ ቆመዉ የነበሩ ናቸዉ ተብሏል።

የእሳት አደጋዉን ለመቆጣጠር አምስት የእሳት አደጋ መቆጣጠር ተሽከርካሪ እና 31 የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች መሰማራታው የተነገረ ሲሆን፤ የእሳት አደጋዉ ወደ ነዳጅ ታንከርና ጋራዡ ላይ ተሳፋፍቶ ተጨማሪ ጉዳት ሳይደርስ መቆጣጠር መቻሉ ተገልጿል።

የእሳት አደጋዉን ለመቆጣጠር 1:30 ሰዓት የፈጀ ሲሆን በሰዉ ላይ የደረሰ ጉዳት አለመኖሩንም ኮሚሽኑ አስታውቋል።
____
ትክክለኛውን የአዲስ ማለዳ ሶሻል ሚዲያ በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ
@TodayNewsEthiopia
@TodayNewsEthiopia
187 views06:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-12 21:47:30 የችሎት ዜና
ጋዜጠኞቹ መስከረም አበራና ጎበዜ ሲሳይን ጨምሮ በእነ ዶ/ር ወንድወሰን አሰፋ መዝገብ የተከሰሱ ተጠርጣሪዎች ችሎት ለህዝብ ክፍት እንዲደረግ ታዘዘ

በአማራ ክልል ከልዩ ሀይል መፍረስና ፋኖን ትጥቅ ማስፈታት ጋር ተያይዞ በሽብር ወንጀል ተጠርጥረዋል ተብለው ለእስር የተዳረጉ በአማራ ጉዳይ ላይ የሚሰሩ ፖለቲከኞች፣ ጋዜጠኞችና ምሁራን ዛሬ ሰኔ 5/2015 ዓ/ም ከሰዓት በኋላ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ችሎት ቀርበዋል።
ችሎቱ ለዛሬ ተቀጥሮ የነበረው አቃቤ ህግ በእያንዳንዳቸው ተከሳሾች ላይ በሬጅስትራር በኩል የተረጋገጠ ክስ እንዲያቀርብ ነበር።
ሆኖም አቃቤ ህግ የተረጋገጠ ክስ ለሬጅስትራር ሰጥቻለሁ ቢልም ሬጅስትራር ግን ሊደርስልኝ የቻለው የ13 ተከሳሽ ክስ ብቻ ነው የሚል ምላሽ ሰጥቷል።
በዚህም አቃቤ ህግ ባሉበትና በሌሉበት በሚል ክስ ከመሰረተባቸው 51 ተጠርጣሪዎች መካከል ለአስራ ሶስቱ የክስ ቻርጅ እንደተሰጣቸው ሮሃ ቲቪ በችሎት ተገኝታ ተከታትላለች።
በዚህ ላይ አስተያየት የሰጡት የተከሳሽ ጠበቆችም " የአስራ ሶስቱ ተከሳሾች ጉዳይ መታየት ይችላል ችግር የለብንም " ብለዋል።
ለችሎቱ የሰብዓዊ መብት አያያዛቸውን በተመለከተ ለችሎቱ አስተያየት የሰጡት ረዳት ፕሮፌሰር ሲሳይ አውግቸው በበኩላቸው " ዶክመንተሪ ተሰርቶብን ስማችን የጠፋ የፖለቲካ እስረኞች ስለሆንን  ችሎቱ ለቤተሰቦቻችን በተለይም ለአማራ ህዝብ ክፍት ተደርጎ በሰፊ አዳራሽ እንዲታይልን" ሲሉ ጥያቄ አቅርበዋል።
ጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ በበኩሉ "ሌላ ቦታ የተሰደብነውና የተደበደብነው  ሳያንስ በችሎት አዳራሽ ፊት በፖሊሶች እንሰደባለን፣ ከጠበቆቻችን ጋር እንዳናወራ እንደረጋለን" ብሏል።
ዶ/ር መሰረት ቀለመወርቅ ደግሞ "የደረሰብንን የሰብዓዊ መብት ጥሰት አቅርበን ነበር አሁን ግን የጊዜ ቀጠሮ ችሎቱ ወደ መደበኛ ችሎት ስለተቀየረ ምን ላይ እንዳለ አናውቅም ፣ ከምን እንደደረሰ ግልፅ ይደረግልን" ሲሉ ጠይቀዋል።
47ኛ ተከሳሽ ማስረሻ እንየው " በህግ ማስከበር ዘመቻው ወቅት ሰውነቴ ውስጥ የቀረ ጥይት አለ ፣እንዳልታከም ተደርጌያለሁ ፣በቀጠሮዬ ቀንም ህክምና እንዳልቀርብ ተደረወጌያለሁ፣ በዚህም ለ75 ቀናት ገላዬን እንኳን መታጠብ አልቻልኩም " ብሏል ለችሎቱ።
ችሎቱም ረዳት ፕሮፌሰር ሲሳይና ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው ላቀረቡት "ጉዳያችን በክፍት አዳራሽ ይታይ" ጥያቄ በሰጠው ምላሽ በቀጣይ ጉዳያቸው በትልቅ አዳራሽ እንዲታይና ለህዝብ ክፍት እንዲሆን አዟል።
በጊዜ ቀጠሮ መዝገብ በኢሰመኮ  እንዲጣሩ ውሳኔ የተሰጠባቸውን መዝገቦች እኛ እናጣራለን ብሏል የፌደራሉ ከፍተኛው ፍርድ ቤት መደበኛ ችሎት።
ዶክመንተሪ ሰርተው ተጠርጣሪዎቹ በህግ ፊት ነፃ ሆኖ የመታየት መብታቸውን ያሳጡ የተባሉት የመንግስት ሚዲያዎች በስም የተጠሩ ሲሆን ፣ ይህንንም ጉዳይ እንደሚያጣራ ነው  ችሎቱ ያሳወቀው።
አቃቤ ህግ ግን "ዶክመንተሪ የሰራው የጋራ ግብረሃይሉ ነው እኔን አይመለከተኝም" ብሏል።
"ለአስራ ሶስቱ ተከሳሾች የቀረበው ክስና የሰነድ ማስረጃን በተመለከተ  ሃላፊነቱን የወሰደው አቃቤ ህግ ስምና ፊርማ የለም ፣ሃላፊነት የሚወስድ አካል ያስፈልጋል " ሲሉም የተከሳሽ ጠበቆች ጠይቀዋል።
አቃቤ ህግም" ሃላፊነቱን የሚወስደው ፍትህ ሚኒስቴር ነው ፣ የፍትህ ሚኒስቴር ማህተም እስካለ ድረስ ሃላፊነቱን የሚወስደው ተቋሙ ነው "የሚል ምላሽ ሰጥቷል።
የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በዚህና በሰብዓዊ መብት ጉዳዮች ዙሪያ በተነሱ ጥያቄዎች ላይ ብይን ለመስጠት ለሰኔ 9/2015 ቀጠሮ ሰጥቷል።

ሮሃ ሚዲያ ROHA MEDIA
@TodayNewsEthiopia
2.3K viewsedited  18:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-12 21:47:30
2.2K views18:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-12 21:33:52
በጉራጌ ክልል ወልቂጤ በትራንስፖርት አገልግሎት አድማ መደረጉ ተሰማ 

መንግስት አድማ ባደረጉ አሽከርካሪዎች ላይ  የነዳጅ ድጎማን እንደሚያነሳ አስጠንቅቋል


በጉራጌ ክልል ከወልቂጤ ወደ አዲስ አበባ ከአዲስአበባ ወደ ወልቂጤ የትራንስፖርት አገልግሎት መቋረጡን ብስራት ሬድዮ ሰምቷል::የትራንስፖርት ማቆም አድማዉ የተደረገዉ ተሳፋሪዎች ከዚህ ቀደም ለአሽከርካሪዉ የሚከፍሉትን የመጓጓዣ ሂሳብ በተዘጋጁ መክፈያዎች ለመንገድ ትራንስፖርት እንዲከፍሉና መንገድ ትራንስፖርት ደግሞ ለመኪናዉ አሽከርካሪ በቴሌብር እንዲከፍል ሲደረግ ቀድሞ 250 የነበረዉ ክፍያ ወደ 170 ብር ዝቅ መደረጉም የቅሬታዉ ዋነኛ አካል ነዉ።

የክፍያ ስነስርዐቱ ወደ ዲጂታል መቀየሩ መልካም መሆኑን የተለያዩ የስፍራዉ አገልግሎት ሰጪዎች ቢናገሩም ነገር ግን ከወልቂጤ ወደ አዲስ አበባ ይሰራል ተብሎ የተቆፈረዉ መንገድ ሳይሰራ መኪናችን እየተጎዳ እንዲሁም በመንገዱ ላይ ባሉ ብዛት ያላቸዉ ትራፊኮች እየተጉላላን እና ይህንን ነገር ለመቅረፍ በመንግስት በኩል የትኛዉም እርምጃ ሳይወሰድ ታሪፍ መቀነሱ ለዚ አድማ መነሻ እንደሆነ ብስራት ሬድዮ ሰምቷል፡፡

በዚህም በዛሬዉ ዕለት ከወልቂጤ ወደ አዲስ አበባ እንዲሁም ከአዲስ አበባ ወደ ወልቂጤ የትራንስፖርት አገልግሎት ባለመኖሩ ማህበረሰቡ እየተጉላላ ይገኛል፡፡ማህበረሰቡ እንዳይጉላላ በአስገዳጅ የተወሰኑ ተሽከርካሪዎች እንዲንቀሳቀሱ እየተደረገ መሆኑን እና አልሰራም ባሉ አሽከርካሪዎች ላይ ደግሞ የመንግስት የነዳጅ ድጎማን እንደሚነሳባቸዉ ማስጠንቀቅያ እየተሰጠ መሆኑን የወልቂጤ ከተማ የመንገድ ትራንስፖርት የስነምግባር ባለሙያ ይድየ ሙዲን ለብስራት ሬድዮ ተናግረዋል።

በአብርሃም ፍቅሬ
@TodayNewsEthiopia
2.4K views18:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-12 18:45:11
ህወሓት ከምርጫ ቦርድ መሠረዙን ተከትሎ በዚህ ስያሜ ለሚመጣ ማንኛዉም የተደራጀ ፖለቲካ ድርጅት በምርጫ ቦርድ አዋጅ ቁጥር 1162/2011 አንቀፅ 69 መሠረት ስያሜዉን መዉሰድ ይችላል። ነገር ግን ምርጫ ቦርድ ለ አንድ ወር ባደረገው ስብሰባ እና ጥናት መሰረት ዉድቅ አድርጎታል።የምርጫ ቦርድ ደብዳቤ ከላይ ተያይዟል።

@TodayNewsEthiopia
@TodayNewsEthiopia
3.2K views15:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-12 18:05:15
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ 20 ሺህ ሰራተኞችን ሊቀጥር ነው ?

ከሀሰተኛ መረጃ ተጠንቀቁ !

በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ " ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በማህበራዊ ትስስር ገፁ 20 ሺህ #ኢትዮጵያውያን ሰራተኞችን መቅጠር እንደሚፈልግ አስታወቀ ፤ ኢትዮጵያውያን ሰራተኞችን የሚቀጥረው ትግራይ ፣ አፋር፣ ሶማሌ ክልሎችን ጨምሮ በሁሉም ክልሎች የቴሌኮም አገልግሎቱን ለማስፋፋት በማቀድ ነው ፤ የስራ ቅጥሩ ዲግሪ አይጠይቅም 10ኛ እና 12ኛ ክፍል ያጠናቀቁ ማመልከት ይችላሉ " እየተባለ የሚሰራጨው መረጃ ፍፁም #ሀሰተኛ መሆኑን ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ገልጾልናል።

ከጥዋት አንስቶ ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ የተሰራጨውን የ20 ሺህ ሰራተኞች ቅጥር መረጃ በተመለከተ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለሚመለከተው የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ክፍል " በየትኛው የማህበራዊ ትስስር ገፃችሁ ላይ ነው ይህ ያሳወቃችሁት ? መረጃው እውነት ከሆነስ በየትኛው መንገድ ነው ማመልከት የሚቻለው ? " ስንል ጥያቄ ያቀረብን ሲሆን መረጃው #ሀሰተኛ ነው የሚል ምላሽ ተሰጥቶናል።

" እኛ 20 ሺህ ሰራተኞች ለመቅጠር በየትኛውም የማህበራዊ ትስስር ገፃችን ላይ ጥሪ አላቀረብንም ፤ መሰል ሀሰተኛ መረጃዎች የሚሰራጩት ሆን ተብሎ ተመሳስለው በተከፈቱ #ሀሰተኛ_ገፆች ነው " ሲል የሚመለከተው የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ክፍል ገልጾልናል።

በመሆኑም " ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ 20 ሺህ ኢትዮጵያውያን ሰራተኞችን ሊቀጥር ነው " በሚል የሚሰራጨው መረጃ ሀሰተኛ ነው።

@TodayNewsEthiopia
3.2K views15:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-12 18:01:45
ከ ሀገር ዉጭ ዉስጥም ያላቹ የተወደዳችሁ ቤተሰቦቼ 
መርጌታ ሚካኤል የባህል መድህኒት
0929918518
0929918518

1.ለሀብት
2.ለገበያ ብዙ ደንበኛ እንዲኖረን
3.ለመስተፋቅር
4.መኖሪያ ፈቃድ በ12 ቀን ለመቀበል

የምንሰራው ጥበብ
============
5.ሰውን ለማፍዘዝ ለማደንገዝ
6. ለሰላቢ በሌላ አማርኛ ነገሮችን ለመሰወር
7.ለግርማ ሞገስ
8.ለትምህርት ዘኢያገድፍ
9.ለዐቃቤ ርዕስ ለመከላከያ
10.ሰው እንዲወደን ማድረግያ
11.ብልት ማሳደጊያ ዕፀ አብይ
12.ለስንፈተ ወሲብ
13.ለዐደበተ ርቱዕ ጥሩ ተናጋሪ እንድንሆን
14.ለቁመት መጨመርያ ዕፀ (ኤግኤል)
15.በግለ ወሲብ ለምትሰቃዩ ወይም በሴጋ
16.ለመልክ ውበት እንዲኖረን ማድረጊያ
17. ስራ እንድንቀጠር ማድረግያ
18.ፈተና አሪፍ ውጤት እንድናመጣ ማድረግያ
19.ለሴቶች ትልቅ ዳሌ እንዲኖረን ማድረግያ በዕፀዋት ብቻ
20.ፀጉር እንዲረዝም ማድረጊያ ..... ወዘተ
21.ለውፍረት
22.ለቅጥነት
23.ለስልጣን መጨመርያ
24.ለጥላ ወጊ
25.ለህዝብ ፍቅር
26.ብር እንዳይባክን ማድረግያ
27.የወደፊት ኮኮቦትን ማስነበብ
28.ለቁማር
29.ደፋር ለመሆን
30. ህልም እንፈታለን
31. ትዳር ላይ ማትስማሙ እድትስማሙ ሚያደርግ
32.ለመካን
በቴሌግራም ለማናገር የምትፈልጉ
@Merigetamikael29

ስ.ቁ 09 29 91 85 18
3.2K viewsedited  15:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-10 12:39:31
የ "ጉማ አዋርድ" አዘጋጅ ዮናስ ብርሃነ ትናንት ምሽት በስካይ ላይት ሆቴል ከተካሄደው የሽልማት ስነ ስርአት በኋላ ለእስር ተዳርጓል

በስፍራው ከነበሩ ሰዎች በደረሰኝ መረጃ መሰረት ዮናስን ሲቪል የለበሱ ደህንነቶች ከምሽቱ 5 ሰአት ገደማ ከነባለቤቱ አስረው ወስደዋቸዋል። ባለቤቱ ከጥቂት ቆይታ በኋላ ብትፈታም ዮናስ አንበሳ ጋራዥ አካባቢ በሚገኝ ፖሊስ ጣቢያ እንደሚገኝ ታውቋል።

በትናንትናው ፕሮግራም ላይ "ልጅ ማኛ" በሚል የምትታወቀው ቲክቶከር ባደረገችው ሜካፕ ምክንያት "ልጅቷን አምጡ" በሚል አዘጋጆቹ ተጠይቀው እንደነበር እና እስሩም ከእሱ ጋር ሊያያዝ እንደሚችል በስፍራው የነበሩ ግለሰቦች እና ሌሎች ምንጮች አረጋግጠውልኛል።

Elias Meseret
5.5K views09:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-08 13:11:05
ከኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በሸገር ከተማ በፈረሱ መስጂዶች ዙሪያ ከኦሮሚያ ክልል መንግስት ጋር የተደረገውን ውይይት ተከትሎ የተሰጠ መግለጫ
7.3K views10:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-07 15:28:43
ቀንህ ካልሆነ በተለያየ አጋጣሚ አድርጎ ጌታ ያድንሀል!

አሁን ጠዋት 2ሰዓት ላይ ሁሉም ወደ ት/ቤትና ወደ ስራ ለመግባት እየተጣደፈ ነው!እኔም ከደቂቃዎች በፊት ወደ ቢሮ ደርሻለሁ!

ይህ የምታዩት የፖሊስ መኪና ኮልፌ18 ከትክክለኛ መንገዱ በተቃራኒ ተሻግሮ አስፓልቱን አልፎ ወደኛ ቢሮ ሲገሰግስ ቆሞ የነበረው ጥበቃ እየጮኸ ሲያመልጥ ሹፌሩም አዙሮ የቆሙ መኪናዎችን እየጠራረገ ከጎን ካለው ባንክ ጄኔሬተሩ ጋር ተላትሞ ወደ መንገድ እንደገና ገብቶ ያገኘውን የተወሰነ መኪናና ሰው ገጭቶ በተዓምር ቆመ!!

በግርግሩና በለቅሶው መሀል አንዲት ዩኒፎርም የለበሰች እየተሻገረች የነበረች ህፃን ተማሪ ወደኔ መጥታ ወዲያው የጠየቀችኝ "እናቴ ጋር ደውልልኝ" የሚል ነበር!ምንም ባትሆንም መንገዷ ስለሆነ እናቷ ስትሰማ እንዳትጨነቅ በማሰብ ደህና መሆኗን ለመንገር ነው!

አንድ ወንድሜ atm ለማውጣት ባንኩ በር ላይ ቆሞ ካርዱን እየነከሰ እያስቸገረው ትንሽ ቆይቶ ሲመለስ ሊገባባት የነበረው ያቆመውን መኪና አሽቀንጥሮታል! "ውስጥ ሆኜ ብሆን እኮ አልተርፍም ነበር ተመስገን"ብሎ በመትረፉ አምላኩን አመስግኗል!

አንዲት የባንኩ ሰራተኛም መኪናዋን አቁማ ወደ ውሰጥ እንደገባች በሰከንዶች ልዩነት ውስጥ ነበር መኪናዋ ቢጎዳም እሷም ከሞትና ከከፋ አደጋ ተርፋለች!
ታክሲዎቹ ውስጥም ከሹፌሮቹ ውጪ ሰው ስላልነበር አደጋው አሰቃቂ እንዳይሆን አድርጎታል!!

ለተጎዱት እህቶቼ አምላክ ቀላል ያድርግላችሁ ሹፌሮች ሆይ የሰው ህይወት በእጃችሁ ነውና እባካችሁ በቻላችሁት ሁሉ እየተጠነቀቃችሁ ንዱ
#በሰላም_ዋሉ ከክፉ አደጋ ይጠብቃችሁ
Via: ሄኖክ ፍቃዱ
8.0K views12:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ