Get Mystery Box with random crypto!

TIKVAH-ETHIOPIA️🇪🇹-(2)

የቴሌግራም ቻናል አርማ tikivah_ethiopiaa — TIKVAH-ETHIOPIA️🇪🇹-(2) T
የቴሌግራም ቻናል አርማ tikivah_ethiopiaa — TIKVAH-ETHIOPIA️🇪🇹-(2)
የሰርጥ አድራሻ: @tikivah_ethiopiaa
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 6.01K
የሰርጥ መግለጫ

@tikivh_ethiopia

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-08-26 21:04:01
ፎቶ : ኮሎኔል አትሌት ደራርቱ ቱሉ በባህርዳር ገቡ።

ባህር ዳር ዩንቨርስቲ በነገው እለት በሚያካሂደው የተማሪዎች ምረቃ ወቅት ለብፁዕ አቡነ ኤርምያስ እንዲሁም ለኮሎኔል አትሌት ደራርቱ ቱሉ የክብር ዶክትሬት እንደሚሰጥ ማሳወቁ ይታወሳል።

ይህን ተከትሎ አትሌት ደራርቱ ቱሉ ዛሬ በባህርዳር ገብተዋል።

ባህር ዳር አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የባህርዳር ዩንቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ፍሬው ተገኘ በተገኙበት አቀባበል ተደርጎላቸዋል።

Photo Credit ፦ WMCC
903 views18:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-25 21:28:35 #ECSOC

የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ም/ ቤት በሰሜኑ የኢትዮጵያ ክፍል ዳግም የተቀሰቀሰው ትጥቅን ያካተተ ግጭትን እንዲረጋጋ እና የተጀመረው የሰላም ሂደት በአስቸኳይ እንዲቀጥል አበክሮ ጠይቋል።

ም/ቤቱ በሰሜኑ የኢትዮጵያ ክፍል መልሶ ያገረሸው የትጥቅ ግጭት በእጅጉ እንደሚያሳስበው ገልጿጻ።

ከዚህ በፊት የተፈጠረው የትጥቅ ግጭት ተነግሮ የማያልቅ የሰው ልጅ ስቃይ እና ከፍተኛ መሰረተ ልማቶች መውደም ምክንያት መሆኑን ይታወቃል ያለው ም/ቤቱ አሁን ዳግም የተቀሰቀሰው የትጥቅ ግጭት እንዲረጋጋና ግጭቱ እንዳይባባስ አፈላጊው ሁሉ እንዲደረግ አሳስቧል።

በተጨማሪም ም/ቤቱ አስቸኳይ የሰብዓዊ ተኩስ አቁሙ መከበር ለሰብአዊ ዕርዳታ አቅርቦት ቀጣይነት እና ለሰላም ሂደቱ ስኬታማነት ወሳኝ እንደሆነ ገልጾ አለመግባባቶች በፖለቲካዊ ውይይት መፈታት እንዳለባቸው በጥብቅ እንደሚያምን ገልጿል።

ለዚህም የሰላም ማስፈን ሂደቱ በአስቸኳይ እንዲቀጥልና ሀገሪቱንና ዜጎቿን ከተጨማሪ ጥፋት ለመታደግ የሰላም ሂደቱ በቅን ልቦና እንዲካሄድ ምክር ቤቱ ጠይቋል።

የጉዳዩን አሳሳቢነት ከግንዛቤ በማስገባት የአፍሪካ ህብረት (AU) የፌደራል መንግስትን እና ህወሃትን የማደራደር ሚናውን በእጥፍ በማሳደግ ሰላማዊ እልባት ላይ እንዲደረስ የበኩሉን እንዲወጣ ምክር ቤቱ ጥሪ አቅርቧል።

የሰላም ማስፈን ሂደቱን አስፈላጊ ሆኖ በተገኘ በማንኛውም መንገድ ለመደገፍ ያለውን ቁርጠኝነት እና ዝግጁነትም በድጋሚ አረጋግጧል።
1.0K views18:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-16 20:45:41
" ውጤቱን አልቀበልም " - ኦዲንጋ

ራይላ ኦዲንጋ የምርጫውን ውጤት አልቀበለም ብለዋል።

ትላንትና ሰኞ የኬንያ ምርጫ ኮሚሽን የኬንያን ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ዊልያን ሩቶ ማሸነፋቸውን ማሳወቁ አይዘነጋም።

በቦማስ በተደረገው ስነስርዓት ወቅት ጭራሽ በማዕከሉ ያልተገኙት የሩቶ ተፎካካሪ ኦዲንጋ እስከ ዛሬ ከሰዓት ድረስ ስለ ምርጫው ምንም ሳይሉ ቆይተዋል።

ራይላ ኦዲንጋ ዛሬ ከሰዓት በሰጡት መግለጫ የምርጫውን ውጤት ሙሉ በሙሉ ተቀባይነት እንደሌለውና እሳቸውም እንደማይቀበሉት አሳውቀዋል።

ከዚህ በተጨማሪ ሁሉም ሰው እንዲረጋጋ እና ህግ እንዲያከብር አሳስበዋል።
@tikivah_ethiopiaa
1.9K viewsedited  17:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-11 11:06:55 #BREAKING

የታላቁ ኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሁለተኛው ተርባይን የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት ጀመረ።

ጠ/ሚር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድን ጨምሮ የተለያዩ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች በቤንሻንጉል ጉሙዝ ጉባ ወረዳ በታደሙበት ዝግጅት ነው በዛሬው ዕለት ሁለተኛው ተርባይን ኃይል ማመንጨት የጀመረው።

የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ካሉት 13 ተርባይኖች መካከል ዩኒት 9 የሚባለው ሁለተኛው ተርባይን የተሳካ ተከላ እና ሙከራ ከተደረገ በኋላ ኃይል የማመንጨት ስራው እውን መሆኑን ብሄራዊ የቴሌቪዥን ጣቢያ ዘግቧል።

ዛሬ በይፋ ሥራ የጀመረው ሁለተኛው ዩኒት 375 ሜጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም እንዳለው ተገልጿል።
2.2K views08:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-07 20:20:28 #የዩኒቨርሲቲ_መምህራን !

በዩኒቨርሲቲ መምህራን ማህበራት በኩል የቀረቡ ጥያቄዎች ፦

• መንግሥትን የደመወዝ ጭማሪ እና የዕርከን ዕድገት እንዲያደርግ ጠይቀዋል።

• ለዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ እና ቴክኒካል ረዳቶች የተሰራውን አዲሱን የስራ ደረጃ ማሻሻያ JEG በተመለከተ ቅሬታ አላቸው።

• የመምህራን የቤት አበልን በተመለከተ በፍጥነት አሁን ያለው የቤት ኪራይ ዋጋ ከግምት አስገብቶ ተሻሽሎ ተግባራዊ እንዲደረገ ጠይቀዋል።

• በመንግስት የተደረገው የደረጃ ማሻሻያ ረጅም ጊዜ በዩንቨርሲቲ ያስተማሩ መምህራንን ልምድ ያላገናዘበ በመሆኑና በመምህራን መካከል በቀጣይ ፍትሀዊ የደምወዝ ልዩነት እንዲኖር ስለማያስችል የደረጃ ማሻሻየው የመምህራንን ልምድ እና ማዕረግ ያገናዘበ እንዲሆን ጠይቀዋል።

• የረዳት ፕሮፌሰር የአካዳሚክ ማዕረግ ዝቅተኛ ተፈላጊ ችሎታ የ3ኛ ዲግሪ መደረጉን በተመለከተ ያለን ቅሬታ አላቸው።

• የአካዳሚክ ቴክኒክ ረዳቶች ዝቅተኛው ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ የመጀመሪያ ዲግሪ መሆኑ ላይ አቤቱታ አላቸው።

• የቺፍ ቴክኒካል ረዳት II የትምህርት ደረጃን ፒ ኤችዲ ዲግሪ መሆኑም ላይ አቤቱታ አላቸው።

ጥያቄዎቻችን መልስ ይሰጣቸው እያሉ የሚገኙት መምህራኑ ይህ ካልሆነ እስከ ስራ የማቆም አድማ መምታት ድረስ ዕርምጃ እንደሚወስዱ ገልፀዋል።

ትምህርት ሚኒስቴር ለሪፖርተር ፥ " ጥያቄ እንዳለ እናውቃለን። ነገር ግን አሁን ላይ ለውጦች ለማምጣት ጥናት እየተካሄደ ነው። ከዚህ ባለፈ የምንለው ነገር የለም። የደመወዝ ጉዳይ የትምህርት ሚኒስቴር ብቻ አይደለም የሲቪል ሰርቪስ ጉዳይም ነው "

ያንብቡ : telegra.ph/ETH-08-07-2
2.6K views17:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-06 22:02:57
" ፍትህ ይሰጠኝ ፣ ህግ ይፍረደኝ " - ወላጅ አባት

ከሰሞኑን በአ/አ በአንድ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋም ውስጥ አንድ ተማሪ እጅግ አሰቃቂ በሆነ ሁኔታ ተገድሏል። ጉዳዩ ምንም እንኳን በህግ ቢያዝም ቤተሰቦች ተገቢውን ፍትህ እንዲያገኙ ጠይቀዋል።

በሚማርበት ተቋም ውስጥ የተገደለው ተማሪ ዮሐንስ አሰፋ ይባላል።

ተማሪ ዮሐንስ እድሜው 20 እስከ 12ኛ ክፍልም በኮከበፅብአ ት/ቤት ትምህርቱን ተከታትሏል።

የከፍተኛ ትምህርት ተቋም ውጤት አምጥቶም ወደ ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ቢመደብም አባት አቅም ስለሌላቸውና አጠገባቸው እንዲሆን ቅ/ማርያም ዩኒቨርሲቲ (ዋቢ ሸበሌ) ትምህርቱን እንዲጀምር ያደርጋሉ።

ዮሐንስን ትምህርቱን (በአካውንቲንግ) በከፍተኛ ውጤት እየተከታተለ 2 ዓመት ድረስ መድረስ ችሏል።

የተማሪውን ባህሪ የሚያውቁ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላትና የዮሐንስ ወላጅ አባት ልጃቸው ከሰው ጋር የማይጋጭ፣ በቤተክርስቲያን አስተምሮ ያደገ፣ የቤተክርስቲያን አገልጋይ፣ ጨዋና ሰዎችን ቀና ብሎ የማያይ እንደሆነ ገልፀዋል።

ነገር ግን ከሰሞኑን በትምህርት ተቋሙ ውስጥ በርካታ የሰውነቱ ቦታ ላይ በአሰቃቂ ሁኔታ በስለት ተወጋግቶ ተገድሏል።

አባት፤ "ልጄ እንደበግ ነው የታረደው" ያሉ ሲሆን "ህግ ፍትህ ይስጠኝ፤ የኢትዮጵያ ህዝብ ይፍረደኝ ፣ የልጄ ደም ይውጣልኝ፤ ህግ ካለ መንግስት ካለ ፍትህ ይስጠኝ" ብለዋል።

ወላጅ አባት ጉዳዩ በህግ እንደተያዘ ገልፀው " ህግ ይፍረደኝ የልጄን ደም ይፈልግልኝ፤ የኢትዮጵያ ህዝብ ይፍረደኝ፤ ንፁህ ኢትዮጵያዊ በኤርትራ ምድር ደሜ ፈሷል ቆስያለሁ ቆስዬ ጡረታም የለኝ፣ የምሰራው በአትክልተኝነት ነው ልጄን በብዙ ችግር ነው ያሳደኩት የኢትዮጵያ ህዝብ ይሄን አይቶ ይፍረደኝ" ሲሉ ተማፅነዋል።

ያንብቡ telegra.ph/Yohannes-Asefa-08-06
1.9K views19:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-06 07:10:58
#ድርድሩ

በአዲስ አበባ ከፌዴራል መንግስት ጋር እንዲሁም መቐለ ተጉዘው ትግራይ ክልልን እያስተዳደረ ካለው ህወሓት ጋር ሰሞኑን የተወያዩት የአውሮፓ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አኔቴ ዌበር ከጀርመን ሬድዮ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ በፌዴራል መንግስት እና ህወሓት መካከል ይደረጋል ተብሎ ለሚጠበቀው የሰላም ድርድር " የመተማመን መጥፋት " መሰናክል መሆኑን ተናግረዋል።

ዌበር ለሬድዮ ጣቢያው " ዋነኛው መሰናክል (ለሰላም ድርድሩ) የእምነት እጦት ነው ብዬ አስባለሁ። አንዱ ከሌላው ጋር በቅን ልቦና እየተደራደሩ ለመሆናቸው የበለጠ መተማመኛ እንደሚፈልጉ 2ቱም ግልፅ አድርገዋል።

ሁለቱ ወገኖች ዝግጁነታቸውን ከማሳወቅ ባሻገር ወደ ድርድሩ እንዲመጡ የሚያስፈልገውን መተማመን የአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑክ ኦሊሴንጉን ኦባሳንጆ ያጠናክራሉ ብዬ ተስፋ አድርጋለሁ።

የፌዴራል መንግስት ተጨማሪ ቅድመ ሁኔታዎች እንደሌሉት አረጋግጧል። ከመንግስት በኩል የተቋረጡ መሰረታዊ አገልግሎቶችን መልሶ ለማስጀመር ምልክት ከሰጠ ወይም ካስጀመረ ህወሓት በጠረጴዛ ዙሪያ ለመደራደር ዝግጁ መሆኑን በመቐለ ጉብኝታችን ተረድቻለሁ " ሲሉ ተናግረዋል።

የተቋረጡ መሰረታዊ አገልግሎቶችን በተመለከተ ዌበር በጥቂት ቀናት ውስጥ ስራ ይጀምራሉ የሚል ተስፋ እንዳላቸው ከሬድዮ ጣቢያው ጋር በነበራቸው ቃለምምልስ ወቅት ተናግረዋል።

ዌበር " እኛ አሁን እጅግ በቅርቡ ተግባራዊ ይሆናል ብለን ተስፋ እናደርጋለን።

መሰረታዊ አገልግሎቶች ስራ ከሚጀምሩበትን፤ መጀመራቸውን እየተጠባበቅን ነው። በዚህ ረገድ ከአዲስ አበባም ሆነ ከመቐለ የተቀየረ ነገር ካለ አልሰማሁም፤ ነገር ግን ይህ በማንኛውም ቀን ተግባራዊ ይሆናል ብዬ እጅግ ተስፋ አደርጋለሁ። " ብለዋል።

ያንብቡ : telegra.ph/EU-08-05
1.6K views04:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-05 21:37:52
#HappeningNow

ኢትዮ ቴሌኮም ቴሌብር መላ፤ ቴሌብር እንደኪሴ እንዲሁም ቴሌብር ቁጠባ የተሰኙ የፋይናንሻል አገልግሎቶችን ዛሬ በስካይ ላይት ሆቴል በማስተዋወቅ ላይ ይገኛል።

ቴሌ ብር መላ፦ የቴሌብር ደንበኞቹን ባንቀሳቀሱት የገንዘብ ዝውውር መሰረት ታይቶ እስከ በቀን እስከ 2,000 በወር ደግሞ እስከ 10,000 ብር የሚደርስ ብድር የሚያመቻች አገልግሎት ነው።

ቴሌ ብር እንደኪሴ ፦ በቴሌብር አማካኝነት ግብይት በሚፈጸምበት ጊዜ የቴሌብር ሂሳቦ ከሚገዙት እቃ በታች ከሆነ ቀሪውን ክፍያ ጨምሮ ለሻጭ ይከፍልና ገንዘብ ገቢ ሲያደርጉ ከሂሳቦ ላይ ተቀናሽ የሚያደርግ አገልግሎት ነው።

ቴሌብር ቁጠባ፦ ቴሌብር ላይ ካለው የገንዘብ መጠን ላይ መቆጠብ የሚያስችል አገልግሎት ሲሆን በሁለት አማራጮች ማለትም በወለድና ያለወለድ የቀረበ ነው። የወለድ መጠኑም 7% ሲሆን ወለዱ መጠን በቀን ተሰልቶ በሂሳቦ ገቢ ይደረጋል።

ተጨማሪ መረጃ እንልክላችኃለን!
1.3K views18:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-05 21:15:52
" ... አልሸባብ ዳግመኛ ወደ ድንበር እንዳይጠጋ የማረጋገጥ ስራ እየተሰራ ነው " - የሶማሌ ክልል ፕ/ት ሙስጠፌ ሙሁመድ

በቅርቡ በኢትዮጵያና ሶማሊያ ድንበር ላይ ጥቃት ፈፅሞ የነበረው የአልሸባብ ቡድን 800 ታጣቂዎቹ መገደላቸውን 100 የሚጠጉት ደግሞ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የሶማሌ ክልል ፕሬዜዳንት ሙስጠፌ ሙሁመድ በተረጋገጠ ትዊተር ገፃቸው ላይ አሳውቀዋል።

የአልሸባብ ጥቃት በሽንፈት መጠናቀቁን የገለፁት ፕሬዜዳንት ሙስጠፌ አልሸባብ ዳግመኛ ወደ ድንበር እንዳይጠጋ እና እንዳይዳፈር የማረጋገጥ ስራ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።
@tikivah_ethiopiaa
1.3K viewsedited  18:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-05 16:17:06 ቻይና ከአሜሪካ ጋር ወታደራዊ ትብብሯን አቋረጠች

ቻይና ከዚህ ውሳኔ ላይ የደረሰችው አፈ ጉባኤ ናንሲ ፔሎሲ ታይዋንን በመጎብኘቷ ነው። ቻይና በናንሲ ፔሎሲ እና ቤተሰቦቻቸው ናይ ማዕቀብ መጣሏ ይታወሳል።
https://am.al-ain.com/article/china-says-it-cuts-military-ties-with-china-over-pelosi-taiwan-visit
1.3K views13:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ