Get Mystery Box with random crypto!

TIKVAH-ETHIOPIA️🇪🇹-(2)

የቴሌግራም ቻናል አርማ tikivah_ethiopiaa — TIKVAH-ETHIOPIA️🇪🇹-(2) T
የቴሌግራም ቻናል አርማ tikivah_ethiopiaa — TIKVAH-ETHIOPIA️🇪🇹-(2)
የሰርጥ አድራሻ: @tikivah_ethiopiaa
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 6.01K
የሰርጥ መግለጫ

@tikivh_ethiopia

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-08-05 08:46:23
ሰበር ዜና

ቻይና ዶንግፋንግ የተሰኙ ሚሳኤሎችን ወደ ታይዋን ተኮሰች

ዶንግ ፋንግ የተሰኘው የቻይና የረጅም እና አጭር ርቀት ባልስቲክ ሚሳኤሎች ወደ ታይዋን ባህር የትተኮሱ ሲሆን እስካሁን የደረሰ ጉዳት እንደሌለ ተገልጿል።

ቻይና በታይዋን ባህር ዙሪያ እስከ ቀጣዩ እሁድ ድረስ የሚቆይ ወታደራዊ ልምምድ በማድረግ ላይ ትገኛለች ።

የጦርነት ልምምዱ በታይዋን 20 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በስድስት አቅጣጫ እየተካሄደ ይገኛል ተብሏል።


@tikivah_ethiopiaa
1.2K viewsedited  05:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-04 21:00:59
#ሽልማት

በ18ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና አመርቂ ውጤት ላስመዘገበው የአትሌቲክስ ቡድን አባላት የማበረታቻ ሽልማት ተበረከተ።

የዛሬው ሽልማት የተበረከተው በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ነው።

በዚህም መሰረት ፦

የወርቅ ሜዳሊያ ላስገኙ አራቱ አትሌቶች ለእያንዳንዳቸው የ60 ሺህ ብር የገንዘብ ስጦታ ፤

የብር ሜዳሊያ ላስገኙት አራት አትሌቶች (የወርቅ ሜዳሊያ ያስገኘችውን ጉዳፍ ፀጋይን ጨምሮ) ለእያንዳንዳቸው የ40 ሺህ ብር ስጦታ ፤

የነሀስ ሜዳሊያ ላስገኙት ኹለት አትሌቶች ለእያንዳንዳቸው የ30 ሺህ ብር ስጦታ ፤

እንዲሁም ዲፕሎማ ላገኙ 10 አትሌቶች ለእያንዳንዳቸው የ10 ሺህ ብር ስጦታና ለተሳተፉ 16 አትሌቶች ለእያንዳንዳቸው የ7 ሺህ ብር የገንዘብ ስጦታ ተበርክቶላቸዋል።

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ኮማንደር ደራርቱ ቱሉን ጨምሮ የፌደሬሽኑ አመራሮች፣ አሠልጣኞች እና የአትሌቲክስ ልዑካን ቡድኑ መሪዎች በየደረጃቸው የተለያዩ የገንዘብ ስጦታዎች ተበርክቶላቸዋል።

@tikivah_ethiopiaa
1.2K viewsedited  18:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-04 20:54:54 ሰበር ዜና
አረብ ኢሚሬትስ ለቻይና ሉዓላዊነትና
የግዛት አንድነት ድጋፏን ገለጸች

የአረብ ኢሚሬትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የ“አንድ ቻይና” ፖሊሲን ማክበር እንደሚገባ አሳስቧል።
https://am.al-ain.com/article/the-uae-affirms-its-support-for-the-sovereignty-and-territorial-integrity-of-china
1.1K viewsedited  17:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-04 14:53:55
#GujiZone

• " እስከ ሃምሌ 15 ቀን 2014 ባለው ጊዜ የ12 ሰዎች ህይወት አልፏል ፤ ቁጥሩ ግን ሊጨምር ይችላል " - የሰባ ቦሩ ቡሳ ጎኖፋ ቢሮ

• " የሞቱት ዜጎች ምናልባት በፀጥታ ችግር ምክንያት ሊሆን ይችላል " - የጉጂ ዞን ኮሚኒኬሽን

በኦሮሚያ ክልል፣ በጉጂ ዞን ፤ ሰባ ቦሩ ወረዳ በድርቅ ምክንያት የወገኖቻችን ህይወት እያለፈ መሆኑ ተገለፀ።

በኦሮሚያ ክልል፣ በጉጂ ዞን በሰባ ቦሩ ወረዳ ረሃብ ተከስቶ 12 ሰዎች መሞታቸውን የወረዳው ቡሳ ጎኖፋ ቢሮ ማስታወቁን ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል።

ቢሮው፤ እስከ ሃምሌ 15 ቀን 2014 ዓ/ም ባለው ጊዜ ብቻ የ12 ሰዎች ህይወት ማለፉን ገልጾ ቁጥሩ ግን ሊጨምር እንደሚችል አሳውቋል።

በወረዳው 35,442 ዜጎች አስቸኳይ ምግብ እርዳት ያስፈልጋቸዋል የተባለ ሲሆን እነዚህ ዜጎች በንሳ ፣ በደጋላልቻ ፣ ሰባሎሌማሞ ፣ በኡቱሉ፣ ኦዴ ፣ ሀራጌሳ ቀበሌዎች ያሉ ናቸው ተብሏል።

የወረዳው ቡሳ ጎኖፋ ቢሮ ኃላፊ የሆኑት መኮና ሀጤሳ ፤ ለወረዳው አልፎ አልፎ የምግብ እርዳታ ቢመጣም ምግብ ከሚያስፈልጋቸው ዜጎች ጋር የሚመጣጠን አይደለም ብለዋል።

በወረዳው የሟቾች ቁጥር በየቀኑ #እየጨመረ ሲሆን ባለፉት 2 ወራት የምግብ እና መሰል እርዳታቸዎች መቋረጣቸው ማህበረሰሙ ለከፋ የምግብ እጥረት መጋለጡን ገልፀዋል።

የጉጂ ዞን የኮሚኒኬሽን ቢሮ በበኩሉ ፤ በዞኑ ቆላማ አካባቢዎች 5 ወረዳዎች ድርቅ ተከስቷል ብሏል።

የቢሮው ኃላፊ አቶ ዮሐንስ ኦልኮ፤ " በረሃብ ምክንያት ስለሞቱ ሰዎች መረጃ የለኝም " ብለዋል። ነገር ግን " በአካባቢው የፀጥታ ችግር አለ " ሲሉ መግለፃቸውን ሪፖርተር ዘግቧል።

ያንብቡ : https://telegra.ph/Guji-Zone-08-04
@tikivah_ethiopiaa
1.1K viewsedited  11:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-04 12:42:34
" ማንኛውንም ኢ-መደበኛና ህገወጥ እንቅስቃሴ አልታገስም " - የደቡብ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ

የደቡብ ክልል መንግስት ከአደረጃጀት ጥያቄ ጋር በተያያዘ የሚፈፀም ማንኛውንም ኢ-መደበኛና ሕገ -ወጥ እንቅስቃሴን አልታገሰም ሲል አስጠነቀቀ።

ጉራጌ ዞንን የሁከትና የብጥብጥ ቀጠና ለማድረግ የሚደረገውን እንቅስቃሴን መንግስት አይታገስም ብሏል።

ዛሬ በጉራጌ ዞን ወቅታዊ ፀጥታ ሁኔታ ላይ የክልሉ የፀጥታ ሴክተር፣ የኢፌዲሪ መከላከያ ሰራዊት አመራርና የዞኑ ከፍተኛ አመራሮች በወልቅጤ ከተማ ውይይት አድርገው ነበር።

በዚህም ወቅት በደቡብ ክልል በምክትል ርዕሠ መስተዳድር ማዕረግ የመልካም አስተዳደር ክላስተር ዘርፍ አስተባባሪና የክልሉ ሠላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ አለማየሁ ባውዲ ፥ በጉራጌ ዞን የሕዝብን የመዋቅር ጥያቄ ሽፋን በማድረግ የሚደረግ ኢ-መደበኛ እንቅስቃሴ ተቀባይነት የለውም፤ ይህንኑ ሕገ ወጥ ተግባር የሚፈፅሙ አካላት ላይ ጥብቅ እርምጃ ይወሰዳል ሲሉ አስጠንቅቀዋል።

በዛሬው መድረክ ፤ ሁሉም አካባቢዎች በክልል ለመደራጀት ጥያቄዎችን ማቅረባቸው ተገልጾ " ሀገራዊ ነባራዊ ሁኔታን ባገናዘበና የሕዝብን የአብሮነት፣ የልማትና የጋራ ተጠቃሚነት ብሎም በሁሉም ዘርፍ በቅርበት ለሕብረተሰቡ አገልግሎት ለመስጠት በሚያስችል መልኩ መዋቅሩ እየተሰራ ይገኛል " ተብሏል።

የጉራጌ ዞንም ከሌሎች አጎራባች ወንድም ሕዝቦች ጋር ለሀገር ግንባታ፣ ለኢኮኖሚያዊ ዕድገትና ለጋራ ብልፅግና እንዲያመች በአንድ ላይ መሆን እንደሚገባው በመድረኩ ተጠቁሟል።

ለዚህም አመራሩ ሕብረተሰቡን በቅርበት በማወያየትና ከአደረጃጀት ጥያቄ ጋር ተያይዞ በዞኑ የሚፈጠር ምንም ዓይነት የፀጥታ ችግር እንዳይኖር በከፍተኛ ትኩረት መስራት ይኖርበታል ተብሏል
ያንብቡ : telegra.ph/Gurage-Zone-08-03
@tikivah_ethiopiaa
1.1K viewsedited  09:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-03 19:04:44
#DrAbiyAhmed

ዛሬ ከሰዓት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ በተገኙበት የማክሮ ኢኮኖሚ ኮሚቴ አባላት ስብሰባ የተካሄደ ሲሆን በአጠቃላይ የማክሮ ኢኮኖሚ ጉዳዮች ላይ መክሯል።

እንዲሁም የአረንጓዴ ዐሻራ ክንውን ያለበትን ደረጃ አንስቷል።

በተጨማሪም የ2015 የበጀት ዓመት ዕቅድ የትኩረት አቅጣጫን መቃኘቱን የጠ/ሚ ፅ/ቤት አሳውቋል።





@tikivah_ethiopiaa
1.2K viewsedited  16:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-03 18:27:32
#Update

ፔሎሲ የታይዋን ጉብኝታቸውን አጠናቀው ታይዋንን ለቀው ወጥተዋል።

የአሜሪካ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ እና በሀገሪቱ የስልጣን እርከን ሶስተኛ ሰው የሆኑት ናንሲ ፔሎሲ ታይዋን ጎብኝተዋል።

ትላንት ታይዋን ሲደርሱ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።

የፔሎሲ የታይዋን ጉብኝት ብዙ ሲባልለት የነበረ እና በአሜሪካ እና ቻይና መካከል የፈጠረው ከፍተኛ ውጥረት ዓለምን ያሰጋ ነበር።

ቻይና ፔሎሲ ወደታይዋን እንደሚመጡ ከሰማች ጊዜ አንስታ ስታስጠነቅቅና እስከወታደራዊ እርምጃ ድረስ እንደምትወስድ ፤ አሜሪካም ትልቅ ዋጋ እንደምትከፍል ስትዝት ነበር።

ነገር ግን ፔሎሲ ወደ ታይዋን ገብተው ጉብኝትም አድርገው ፤ ማግኘት ያለባቸውን አካላት ባለስልጣናት አግኝተው ዛሬ ታይዋንን ለቀው ወጥተዋል።

ቻይና ጉብኝቱን ለማስቆም የወሰደችው ምንም እርምጃ ባይኖርም በአካባቢው ላይ ግን ወታደራዊ እንቅስቃሴዎች ስለመኖራቸው ታውቋል።

ትላንት የቻይና የጦር ጄቶቿ ወደ ታይዋይን የአየር ክልል ዘልቀው መግባታቸው በኦንላይ ሚዲያ ቢሰራጭም መረጃው ውሸት እንደነበር የታይዋን መከላከያ ማሳወቁ ይታወሳል።

ቻይና " ታይዋን " የራሷ ግዛት አድርጋ ነው የምታስባት ፤ #ወደ_እናት_ሀገሯ መመለስ አለባትም ብላ ታምናለች ለዚህም ታይዋንን የሚደግፉ ሁሉ በሀገር አንድነት ላይ አደጋ ያመጡ አድርጋ ነው የምትወስዳቸው።





@tikivah_ethiopiaa
1.1K viewsedited  15:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-03 12:29:58 ሰበር ዜና ቻይና
የዩናይትድ ስቴትስ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ ናንሲ ፔሎሲ በእስያ ጉዟቸው ታይዋንን የሚጎበኙ ከሆነ ዩናይትድ ስቴትስ “ዋጋ ትከፍላለች” ስትል ቻይና ዛሬ አስጠንቅቃለች። ፔሎሲ በይፋ ወደ ታይዋን መጓዛቸውን ባያረጋግጡም የዩናይትድ ስቴትስ እና ታይዋን መገናኛ ብዙኃን ይህንን እየዘገቡ ይገኛሉ። የቻይና ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ሀው ቹንይንግ ቤጂንግ ላይ ዛሬ በሰጡት መደበኛ ጋዜጣዊ መግለጫ እንደተናገሩት “የቻይናን ሉዓላዊ የፀጥታ ጥቅሞች ለማዳከም አሜሪካ ለምትወስደው ርምጃ ኃላፊነቱን ትወስዳለች» ብለዋል። ፔሎሲ በርግጥ ታይዋንን የሚጎበኙ ከሆነ ከ 25 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ የጎነኙ ከፍተኛ የአሜሪካ ባለስልጣን ይሆናሉ። ቻይና ታይዋንን የራሷ አንድ አካል አድርጋ የምታይ ሲሆን ታይዋን ግን ራሷን እንደ ነፃ እና ዲሞክራሲያዊት ሀገር አድርጋ ታያለች። የፔሎሲ የታይዋን ጉብኝትን በተመለከተ ዩናይትድ ስቴትስ ቤጂንግን ለማስቆጣት ሆን ብላ ያደረገችው ነው ስትል ሩሲያ ዛሬ ለቻይና ድጋፏን አሳይታለች። ፔሎሲ ዛሬ ማሌዢያ ኩዋላ ላምፑርን ጎብኝተው ከማሌዢያ ጠቅላይ ሚኒስትር ኢስማኢል ሳብሪ ጋር እንደተገናኙ የፈረንሳይ ዜና ምንጭ ዘግቧል። የታይዋን የዜና ምንጮች እንደዘገቡት ናንሲ ፔሎሲ ዛሬ ማምሻውን ታይዋን ይገባሉ።

# DW Amharic
1.0K viewsedited  09:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-03 12:22:21
#ነዳጅ
በኢትዮጵያ ያሉ የነዳጅ ኩባንያዎች፣ ነዳጅ አመላላሽ ቦቴ ተሽከርካሪዎቻቸው ከጂቡቲ ነዳጅ ሲቀዱ ከዚህ በፊት የጫኑት ነዳጅ መዳረሻው ደርሶ ስለመራገፉ የርክክብ ሰነድ እንዲያመጡ ካልሆነ ግን ከነገ ከሐሙስ ሐምሌ 28 ቀን 2014 ዓ.ም. ጀምሮ ነዳጅ መጫን እንዳይፈቀድላቸው የነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን ትዕዛዝ ማስተላለፉን ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል
ከዚህ በተጨማፊ ቦቴዎቹ ነዳጅ ቀድተው ሲወጡ ስለመዳረሻቸው ሙሉ መረጃ ለጥፈው መውጣት እንዳለባቸው በባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰሃረላ አብዱላሂ ሐምሌ 21 ቀን 2014 ዓ.ም. ተፈርሞ የወጣውና ለኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት የተጻፈ ደብዳቤ ያሳያል
የኩባንያዎቹ ቦቴዎች የርክክብ ሰነድ የሚያገኙት በየማደያው አካባቢ ካሉ የወረዳ ንግድ ቢሮዎች ሲሆን፣ ይህም የሚሆነው የንግድ ቢሮዎች ባለሙያዎች ቦቴዎቹ ነዳጁን ለማደያዎች ሲያስረክቡ እዚያው ማረጋገጫቸውን በመስጠት ነው
ስለቀጣይ መዳረሻዎቻቸው ሙሉ መረጃ በመስጠትና በመለጠፍ ይቀዳሉ ተብሏል
የነዳጅ አቅራቢ ድርጅት በመመርያው ይህን እንዲያስቀድም የታዘዘ ሲሆን የነዳጅ ኩባንያዎቹ ይህን አውቀው የማይታዘዙ ከሆነ መጫን እንደማይችሉ ማወቅ አለባቸው ተብሏል
ባለስልጣን መ/ቤቱ ይህን ካላደረጉ ዳግም ነዳጅ ለመጫንና ሥምሪት ለማድረግ አይችሉም " ብሏል
የነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ተግባራዊ እንዲያደርግ ያዘዘው ደብዳቤ ዓላማ፣ ባለፈው ወር የወጣውን የነዳጅ ውጤቶች የሥርጭት ርክክብና ሽያጭ አፈጻጻም መመርያ ተግባራዊ ለማድረግ ታስቦ ሲሆን በዚህምከጂቡቲ እስከ ማደያ ድረስ ይፈጸማል የሚባለውን የኮትሮባንድ ንግድ ለማስቀረት ከፍተኛ አስተዋጾኦ እንደሚኖረው ታምኗል፡
ያንብቡ :



Credit : ሪፖርተር

@tikivah_ethiopiaa
1.0K viewsedited  09:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-03 11:52:53
የካቢኔ አባል የተደረጉት የቀድሞ የአልሸባብ ከፍተኛ አመራር ማንናቸው ?

በትላንትናው ዕለት የሶማሊያ ጠ/ሚ ሀምዛ አብዲ ባሬ 26 አባላት ያሉትን ካቢኔ ይፋ አድርገዋል።

ጠ/ሚስትሩ በጠ/ሚኒስትርነት ከተሾሙ በኃላ ካቢኔያቸውን የሚያሳውቁበት ቀን በሶማሊያውያን ዘንድ በብዙ ሲጠበቅ ነበር።

ትላንት ይፋ ባደረጉት የካቤኔ አባላት ዝርዝር ግን አንድ የቀድሞ የአልሸባብ ከፍተኛ አመራርን ማካተታቸው የሚዲያዎችን ትኩረት ስቧል።

የሶማሊያ ካቢኔ ሹመት ያገኙት መክታር ሮቦው ናቸው።

ሙክታር ሮቦው፤ የቀድሞ የአልሸባብ ምክትል መሪ የነበሩ ሲሆን አሁን የሀይማኖት ጉዳዮች ሚኒስትር ተደርገው ነው በካቢኔው የተካተቱት።

ሮቦው ከ3 ዓመታት በላይ በሶማሊያ ብሔራዊ መረጃና ደኅንነት ኤጀንሲ (NISA) በቤት ውስጥ የቁም እስረኛ ሆነው አሳልፈዋል፤እንሆ ከ3 ዓመት በኃላ ወደ ንቁ የፖለቲካ ተሳትፎ መመለሳቸው ነው የተነገረው።
በአንድ ወቅት አሜሪካ ሮቦውን ለጠቆማት 5 ሚሊዮን ዶላር እንደምትሰጥ ገልፃ ነበር
ሮቦው በታህሳስ 2018 በቀድሞው የሶማሊያ ፕሬዜዳንት ሞሀመድ አብዱላሂ ሞሀመድ (ፋርማጆ) አስተዳደር ሊታሰር ችሏል
የቀድሞው የአልሸባብ መሪ በሶማሊያና በኢትዮጵያ የጸጥታ ሃይሎች (AU) ጥምረት ነው በቁጥጥር ስር ሊውል የቻለው።
ከዚያን ጊዜ ጀምሮ በNISA የቤት ውስጥ እስረኛ ሆነው ቆይተዋል።
በጠ/ሚ ሀምዛ አብዲ ባሬ የካቢኔ አባል ተደርገው የተመረጡት ሮቦው የአልሸባብ ታጣቂዎችን ውጤታማ በሆነ መንገድ ለመዋጋት መንግስትን ይረዳሉ ተብሎ ይጠበቃ
ፕ/ት ሀሰን ሼክ ከሁሉም ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር የአልሸባብ ታጣቂዎችን በብቃት ለመታገል ቃል መግባታቸው ይታወቃል

NB : የካቢኔ አባላቱ ሹመት ወደፓርላማ ቀርቦ አፀደቀም። መቼ ፓርላማው እንደሚያፀድቀው አልታወቀም



975 viewsedited  08:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ