Get Mystery Box with random crypto!

✞ ተዋሕዶ ✞ 🇹 🇪 🇼 🇦 🇭 🇪 🇩 🇴

የቴሌግራም ቻናል አርማ tewahedo12 — ✞ ተዋሕዶ ✞ 🇹 🇪 🇼 🇦 🇭 🇪 🇩 🇴
የቴሌግራም ቻናል አርማ tewahedo12 — ✞ ተዋሕዶ ✞ 🇹 🇪 🇼 🇦 🇭 🇪 🇩 🇴
የሰርጥ አድራሻ: @tewahedo12
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 10.16K
የሰርጥ መግለጫ

"ሥርዓትን እማር ዘንድ ያስጨነከኝ መልካም ሆነልኝ"
መዝ 118 (119) ፥ 71
ይህ ቻናል የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ዶግማንና ቀኖናን ትውፊትን እንዲሁም አስተምሮን የጠበቁ የተለያዩ የሚያስተምሩ ነገሮች ይለቀቁበታ፡፡ ግሩፑ
http://t.me/OrthodoxTewahedo12
ይህ Channel #ሐምሌ 26/2010 ዓ.ም አ/ጀመረ
ለአስተያየት 📥 ➩ @Tewahedo12_bot

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 6

2023-05-16 10:13:51 ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ እንዳስተማሩት (በረከታቸው ይደብን)

የኤልኬራዛ በረከቶች ከሚለው መጽሐፍ

እግዚአብሔርን ለሚወዱ ነገር ሁሉ ለበጐ ነው

ለወንድማች ቃለ ሕይወት ያሰማልን
መልካም ቆይታ

ይቀጥላል....

Share
🇹 🇪 🇼 🇦 🇭 🇪 🇩 🇴
✥••┈┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈┈••✥

@Tewahedo12

@OrthodoxTewahedo12

✥••┈┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈┈••✥
692 views✞ ባሮክ ✞, 07:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-10 19:23:13
❖ ስትጸልይ በማክበር ውስጥ መሆንን ተለማመድ፣ የልብና የሥጋ ማክበር ይኑርህ፣ የስሜቶች ሰላምም እንዲሁ፤ ቀስ በቀስ መዝሙራትን፣ ወንጌላትንና የዘወትር ጸሎቶችን አጥና፤ በሁሉም ጊዜ ውስጥ ጸሎት መጸለይን ተለማመድ፣ ስትሠራ፣ ስትራመድና ከሌሎች ሰዎች ጋር ስትቀመጥ እንኳ፣ ዘወትር ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ እኔ ኃጢአተኛውን ማረኝ እያልህ መጸለይን ተለማመድ፤ በማንኛውም ጊዜ ለሌሎች ሰዎች መጸለይን ተለማመድ፣ ለሁሉም ሰዎችም ፍቅር አሳይ፣ ለጠላቶችህና አንተን ለሚሰድቡህ ሰዎች እንድትጸልይ የሚያዝህን የእግዚአብሔር ትዕዛዝ ተለማመድና ተግባራዊ አድርግ።

ምንጭ
አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ
338 views✞ ባሮክ ✞, 16:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-10 19:23:09 ✥•••••●◉ ✞ ◉●•••••✥
"የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ከመከራም ሥጋት ያርፋል"
ምሳ 1፥33

                       
#ስንክሳር          
                  ዘግንቦት
#ሦስት (፫)        
              ✥•••••●◉ ✞ ◉●•••••✥
264 views✞ ባሮክ ✞, 16:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-10 19:22:11 ✥•••••••••••••••••••●◉ ✞ ◉●•••••••••••••••••••✥

"ልብህን በእርጋታ አኑረው፤ የሁሉም መጨረሻ እና የሁሉም አገልጋይ ለመሆን በጣም ትጋ ለከንቱ ንግግር ዘገምተኛና ሰነፍ ሁን፤ ነገር ግን የቅዱሳት መጻህፍትን ቃል በማወቅ በመስማት ድኅነትን የሚሰጡ ናቸውና ብልህ ሁን"
ታላቁ ባስልዮስ ዘቂሳሪያ

በግንቦት ወር
#በጠዋትና በማታ #የሚነበቡ የእየለታት #የመጽሐፍ ቅዱስ #ክፍሎች

#ግንቦት


“ስለዚህ የተወደዳችሁ ወንድሞቼ ሆይ ሰው ሁሉ ለመስማት የፈጠነ ለመናገርም የዘገየ ለቍጣም የዘገየ ይሁን”
ያዕቆብ 1፥19

መልካም ንባብ

✥•••••••••••••••••••●◉ ✞ ◉●•••••••••••••••••••✥

Share
🇹 🇪 🇼 🇦 🇭 🇪 🇩 🇴
✥••┈┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈┈••✥

@Tewahedo12

@OrthodoxTewahedo12

✥••┈┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈┈••✥
246 views✞ ባሮክ ✞, 16:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-10 19:21:31 https://telegra.ph/ስንክሳር-ዘወርኀ-ግንቦት-05-07-5
232 views✞ ባሮክ ✞, 16:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-10 15:35:31 https://telegra.ph/ኦርቶዶክሳዊ-የወጣቶች-ሕይወት-02-06
457 views✞ ባሮክ ✞, 12:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-10 13:33:21

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ
           አሜን

"በበጎ ሥራ ሁሉ ፍሬ እያፈራችሁ በእግዚአብሔርም እውቀት እያደጋችሁ፤ ለጌታ እንደሚገባ ትመላለሱ ዘንድ እንለምናለን"
ቆላስይስ 1፥10-11

           ቀናችንን በጸሎት እንጀምር

    ✥•••••●◉ ✞ ◉●•••••✥
             ርክበ ካህናት    
    ✥•••••●◉ ✞ ◉●•••••✥

❖ የዚህ ዓመት (ዘመነ ሉቃስ ፳፻፲፭) ርክበ ካህነት ግንቦት ፪(2) ይሆናል

❖ ርክበ ማለት ረከበ ከሚለው የግእዝ ዘር የተገኘ ሲሆን ረከበ አገኘ ርክበ ማግኘት መቀበል ማለት ነው፤ ርክበ ካህናት ስንልም የክህነት መቀበል ማግኘት መገናኛ ተብሎ ይተረጎማል፡፡

❖ በቤተክርስቲያናችን ሥርዓት ከትንሳኤ በኋላ በ25ኛው ዕለት ወይም የበዓለ ሃምሳ እኩሌታ ላይ የሚውል በዓል ሲሆን ምን ጊዜም ዕለተ ረቡዕ ላይ ይውላል፡፡

❖ ርክበ ካህናት ለምን በባዕለ ሃምሳ ኣጋማሽ በዕለተ ረቡዕ ሆነ ቢሉ

❖ ለቅዱስ ጴጥሮስ ( ለቤተክርስቲያን ) በጎቼን ጠብቅ፣ ጠቦቶቼን አሰማራ፣ ግልገሎቼን ጠብቅ በማለት ሥልጣነ ክህነት የተሰጠው በበዓለ ሃምሳ ኣጋማሽ በ25ኛው ዕለት በዕለተ ረቡዕ በመሆኑ ነው፡፡
ዮሐ 21፥15-17

❖ ጌታችን ለሐዋርያት ስልጣነ ክህነትን እንደሰጣቸው ከላይ ካየነው ጥቅስ ባሻገር

‹‹እውነት እውነት እላችኋለሁ፤ በምድር የምታስሩት በሰማይ የታሰረ ይሆናል፤ በምድርም የምትፈቱት በሰማይ የተፈታ ይሆናል›› የሚለው እና ‹‹ …ይህን ብሎ እፍ አለባቸው፤ እንዲህም አላቸው መንፈስ ቅዱስን ተቀበሉ፤ ኃጢአታቸውን ይቅር ያላችሁላቸው ይሠረይላቸዋል፤ ይቅር ያላላችኋቸው ግን አይሰረይላቸው››
ማቴ 18፥18
ማቴ16፥19
ዮሐ 20፥22-23 ተጨማሪ ማስረጃዎች ናቸው፡፡

❖ እናት ቤተ ክርስቲያን በዚህ ዕለት ከምታከናውናቸው ሥርዓት አሉ ከእነዚህ መካከልም

፩ . ሲኖዶስ

❖ ሲኖዶስ ማለት ቃሉ የግሪክ ሲሆን ትርጉሙ ኣባቶች ስለነገረ ክርስቲያን የሚገናኙበት ጉባኤ ማለት ነው፤ ጉባኤ የግዕዝ ቃል ሲሆን ትርጓሜውም ቅዱስ ስብሰባ ማለት ነው፡፡

❖ በክርስቶስ አምነው ክርስትና በተቀበሉት አሕዛብ እና በክርስትና ባመኑት አይሁድ መካከል የተነሳውን ችግር ለማስወገድ

❖ ሐዋርያት የመጀመሪያውን አድርገዋል፤ ይህ ሲኖዶስ /የኃይማኖት ጉባኤ/ ከ49-50 ዓ.ም መካከል በጌታ ወንድም በያዕቆብ አማካኝነት ተከናወነ፡፡

የሐዋርያት ሲኖዶስ ውሳኔ

❖ ከአህዛብ የሚመለሱ ክርስቲያኖች ከዝሙት እንዲጠበቁ "አይሁዳውያን ይህንን ጥያቄ ያነሱባቸው ነበርና ከዚህ ይቆጠቡ ዘንድ ይህንን ውሳኔ አስተላልፈዋል መፈተን ይኖራል ያልተፈተነ ክብር ስለማያገኝ እንዲጠነክሩ በማሰብ"።

❖ አህዛብ ደም ኣንቅቶ የሞተውን እንዳይበሉ "ያልተባረከ ከብት እንዳይመገቡ ሲል ነው"
ለጣኦት የተሰዋውን እንዳይበሉ።

❖ አህዛብን በመምከርና በማስተማር የሙሴን ሕግ እንዲያውቁ ማድረግ እንጂ ማግለል እንደማይገባ ውሳኔ አስተላልፈዋል

❖ በተጨማሪም ስለቤተክርስቲያን፣ ስለሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን፣ ስለካህናት አገልግሎት፣ ስለምዕመናን ድርሻ አብጥሊስ ግፅው ዲድስቂልያ በተሰኘ መጽሐፋቸው ወስነዋል፡፡
የሐዋ 15/16 1-3

❖ ሐዋርያዊት የሆነችው ቤተ ክርስቲያናችንም ሐዋርያት አብነት አድርጋ ለነገሮች ሁሉ ምላሽ ለመስጠት በዓመት ሁለት ጊዜ ሲኖዶስን ታደርጋለች፤ ዕለታቱም ጥቅምት 12 እና የበዓለ ሃምሳ እኩሌታ ናቸው፡፡

❖ ጥቅምት 12 ታላቁ ወንጌላዊ ማቴዎስ ሰማዕትነትን የተቀበለበት (ያረፈበት ዕለት ነው) እንደሚታወቀው ይህ ወንጌላዊ ኢትዮጵያ መጥቶ ያስተማረ፣ ስለ ኢትዮጰያውያን ከሌሎቹ ወንጌላውያን በተለየ በወንጌሉ ላይ የጻፈ በወንጌሉ ላይ ስለ ኢትዮጵያውያን መጻፋ ኢትዮጵያ ሃገር መጥቶ እንደነበር ማስረጃ መሆኑን አበው ሊቃውን ያስረዳሉ፡፡

❖ ይኸውም ስለ ኢትዮጵያዊትዋ ንግሥት ማክዳ በምዕራፍ 12 ላይ ጽፏል፤

❖ በምዕራፍ 2 ደግሞ ስለ ሰብዓ ሰገል ጽፏል፤ ከሰብዓ ሰገል መካከል ኢትዮጵያውያን እንደነበሩ ቅዱስ ዳዊት በ71ኛው ዝማሬው

‹‹ የሳባ ነገሥታት እጅ መንሻን ያመጡልሃል›› ያለው አስረጅ ነው፡፡

❖ ስለዚህ ቅዱስ ማቴዎስ ስለ ኢትዮጵያውያን በወንጌሉ ስለጻፈ እና በሃገራችን መጥቶ ስላስተማረ ለእርሱ መታሰቢያ እንዲሆን በዕለተ ዕረፍቱ በጥቅምት 12 ዕለት ሲኖዶስን ታደርጋለች፡፡

❖ በዓመት ሁለት ጊዜ ሲኖዶስ እንዲደረግ መሆኑ ኦሪታዊ መሠረት አለው ይኸውም በኦሪ. ዘኁ ምዕ 10 ከቁጥ 1 ጀምሮ ስንመለከት

‹‹ እግዚኣብሔር ሙሴን እንዲህ ብሎ ተናገረው ሁለት የብረት መለከቶች አስጠፍጥፈህ ለአንተ አድርግ፤ ማኅበሩን ለመጥራት ከሰፈራቸውም ለማስጓዝ ይሁኑልህ፡፡ ሁለቱም መለከቶች በተነፋ ጊዜ ማኅበሩ ሁሉ ወደ አንተ ወደ ምስክሩ ድንኳን ይሰብሰቡ ›› እንዳተባለው ይህ መሠረት ሁኖ ሁለቱ መለከቶች ሲነፋ ማኅበሩ ይሰበሰቡ እንደነበረ ዛሬም ይህ ምሳሌ በማድረግ በዓመት ሁለት ጊዜ ቅዱስ ስበሰባ ይደረጋል፡፡
ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ ቄርሎስ

፪ . አምላክ ለመረጠው በቅቶም ለተገኘው ( ሥርዓተ ጵጵስናን ላሟላ ) ሥልጣን ክህነት ( ጳጳሳትን ትሾማለች) ይሰጣል፡፡

❖ ከላይ እንደገለጥነው በዚህ ዕለት በቅዱስ ጴጥሮስ በኩል ለቤተክርስቲያን ሥልጣነ ክህነት የተሰጠበት ስለሆነ በዚህ ዕለት የተገባውን በመሾም በዚያውም የሐዋርያትን ሹመት መታሰቢያ ታደርጋለች፡፡

"የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ከመከራም ሥጋት ያርፋል"
ምሳ 1፥33

" #ወአንቢበክሙ አንትሙ #ለዘኢያንበበ አይድኡ
➘ #እናንተ_አንብባችሁ_ላላነበበው_ንገሩ"

ምንጭ
አምኃ ሥላሴ /መኩሪያ ተስፋዬ/



ለተጨነቀች ነፍስ ዕረፍት የሆነው የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ፤ እኔም ለእናንተ ከአዘጋጀው በኃዋላ በድካሜ ብዛት ሳይገባኝና ሳይገባኝ በምጽፈው ድርሳንወ ገድላት መጽሐፍት ላይ የቃላት (የፊደል) ሕፀፅ ቢገኝ በጎደለው እየሞላችሁ በጠመመው እያቃናችሁ አንብቡ በረከት ተካፈሉ እላለሁ ከምንም ጊዜ በላይ ለሀገራችንና ለዓለም ሰላም እንዲሁም ለደካማው ወንድማችሁ እንድበረታ (የተጣልሁ) እንዳልሆን ስለ እኔ ጸልዩ

"ልብህን በእርጋታ አኑረው፤ የሁሉም መጨረሻ እና የሁሉም አገልጋይ ለመሆን በጣም ትጋ ለከንቱ ንግግር ዘገምተኛና ሰነፍ ሁን፤ ነገር ግን የቅዱሳት መጻህፍትን ቃል በማወቅ በመስማት ድኅነትን የሚሰጡ ናቸውና ብልህ ሁን"
ታላቁ ባስልዮስ ዘቂሳሪያ

               ወስብሐት ለእግዚአብሔር
                              ይቆየን 

───────────
                    Channel
    https://telegram.me/Tewahedo12

        FB Like Page (የፌስቡክ ፔጅ)
  http://facebook.com/Tewahedo12  

        YouTube Subscribe (ሰብስክራይብ)
https://www.youtube.com/channel/UCvYxUdv1D-5juH_P6iE7XXw
 ───────────
479 views✞ ባሮክ ✞, 10:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-10 12:04:13 ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ እንዳስተማሩት (በረከታቸው ይደብን)

ጸሎት

ለወንድማች ቃለ ሕይወት ያሰማልን
መልካም ቆይታ

የመጨረሻው ክፍል ይቀጥላል....

Share
🇹 🇪 🇼 🇦 🇭 🇪 🇩 🇴
✥••┈┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈┈••✥

@Tewahedo12

@OrthodoxTewahedo12

✥••┈┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈┈••✥
372 views✞ ባሮክ ✞, 09:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-10 10:00:37

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ
           አሜን

"በበጎ ሥራ ሁሉ ፍሬ እያፈራችሁ በእግዚአብሔርም እውቀት እያደጋችሁ፥
ለጌታ እንደሚገባ ትመላለሱ ዘንድ እንለምናለን"
ቆላስይስ 1፥10-11

“ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን” (ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ ተነሣ)
“በዐቢይ ኀይል ወሥልጣን” (በገናና ኀይልና ሥልጣን)
“ዐሠሮ ለሰይጣን” (ሰይጣንን ዐሰረው)
“አግአዞ ለአዳም” (አዳምን ነጻ አወጣው)
“ሰላም” (ፍቅር አንድነት ሆነ)
“እምይእዜሰ” (ከእንግዲህስ)
“ኮነ” (ሆነ)
“ፍሥሐ ወሰላም” (ደስታ ሰላም)

    ✥•••••●◉ ✞ ◉●•••••✥
እንኳን ርክበ ካህናት ዓመታዊ መታሰቢያ በዓል አደረሳችሁ፤ አደረሰን
    ✥•••••●◉ ✞ ◉●•••••✥

ርክበ ካህናት

❖ ይህቺ ዕለት በቤተክርስቲያን "ርክበ ካህናት" "ዕለተ ጥብርያዶስ" በመባል ትታወቃለች፤ "ዳግሚት ዕለተ አግብኦተ ግብር" የሚሏትም አሉ::

❖ ርክበ ካህናት በቁሙ "የካህናት ኖሎት (እረኞች) መገናኘትን" የሚመለከት ቃል ነው::

❖ የክብር ባለቤት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትን ድል አድርጐ ከተነሳ በኋላ ለደቀ መዛሙርቱ በየጸጋቸው መጠን እየተገለጠ ያጽናናቸው ያጸናቸው ያስተምራቸው ይባርካቸውም ነበር::

❖ እስከ ዕርገቱ ባሉ 40 ቀናትም መጽሐፈ ኪዳንን ትምህርተ ኅቡዓትን ምሥጢራተ ቤተክርስቲያንን አስተምሯቸዋል፤ በልቡናቸውም አሳድርድሮባቸዋል::

❖ ቅዱስ መጽሐፍ እንደሚል ደግሞ ከዕርገቱ አስቀድሞ ጌታ ለደቀ መዛሙርቱ 3 ጊዜ በጉባኤ ተገልጧል:፡

❖ የትንሣኤ
ዮሐ 20፥19

❖ የአግብኦተ ግብር (ዳግም ትንሳኤ)
ዮሐ 20፥26

❖ የጥብርያዶስ /ዛሬ/
ዮሐ 21፥1

❖ በተረፈው ግን ለድንግል ማርያም ሁሉን ዕለታት መገለጡን አበው ያስተምራሉ::

❖ በዚህች ዕለት በቅዱስ ዼጥሮስ መሪነት ሐዋርያቱ ወደ ጥብርያዶስ ሔዱ::

❖ አስችን ሊያጠምዱም በብዙ ደከሙ፤ ነገር ግን ጌታችን በረድኤት አብሯቸው አልነበረምና አንዳች አሣ በመረባቸው ሊገባ አልቻለም::

❖ ማጥመድ (አስተምሮ ከክህደት ወደ ሃይማኖት ከኃጢአት ወደ ጽድቅ መመለስ) የሚቻለው በረድኤተ እግዚአብሔር እንጂ በእውቀት ብዛት ወይም በአንደበተ ርቱዕነት ብቻ አይደለምና::

❖ ሲነጋ ግን መድኃኒታችን ወደ ቅዱሳን ደቀ መዛሙርቱ መጣ፤ በጥብርያዶስ ባሕር ዳርቻም ቆሞ ታያቸው፤ ከሚወደው ደቀ መዝሙሩ ቅዱስ ዮሐንስ በቀር የለየው ግን አልነበረም::

❖ ቸሩ አባት "ልጆቼ አንዳች የሚበላ ነገር አላችሁ" ሲል ጠየቀ፤ "ጌታ ሆይ የለም" አሉት::

"የለንም" ብሎ የሌለንን ነገር በጌታ ፊት ማመኑ እጅግ መልካም ነው፤ ምክንያቱም ያጣነውን ነገር ያን ጊዜ ሊጠቁመን ቸርነቱ ብዙ ነውና::

❖ ያን ጊዜ ሐዋርያቱን መረባቸው በመርከብ ቀኝ እንዲጥሉ አዘዛቸው፤ እነርሱም በደስታ ጣሉ::

❖ በአግራሞት እስኪሞሉ ድረስ መረባቸውም ሊቀደድ እስኪደርስ ድረስ 153 ዓሦች ተያዙላቸው::

❖ ያን ጊዜም የሚወደው ደቀ መዝሙሩ ቅዱስ ዮሐንስ ምሥጢር አወጣ፤ ለቅዱስ ዼጥሮስ "ጌታ እኮ ነው" አለው፤ ሽማግሌው ቅዱስ ግን ራቁቱን ነበርና ወደ ባሕሩ ተወረወረ::

❖ ከአፍታ በኋላም ጌታችን ከሐዋርያቱ ጋር በድጋሚ (ለ2ኛ ጊዜ) ለምሳ ተቀመጠ፤ ባርኮ ሰጥቶ ልባቸውን ሊያጸና አብሯቸው በላ::

❖ በዚያች ሰዓት ቅዱስ ዼጥሮስን 3 ጊዜ "ትወደኛለህን" ሲል ጠየቀው::

❖ ቅዱሱ አረጋዊም እየደጋገመ "ለሊከ ተአምር ከመ አነ አፈቅረከ (እንድወድህ አንተ ታውቃለህ)" ሲል መለሰ::

❖ ጌታም በበጐች ሐዋርያት (ካህናት) በጠቦቶች አርድእት (ዲያቆናት) በአባግዕት 36ቱ ቅዱሳት አንስት (ምዕመናን ወምዕመናት) ላይ ሁሉ እረኛ እንዲሆን ሾመው::

❖ ቀጥሎም የሰማዕትነቱን ምስጢር ገልጦለት "ተከተለኝ" (ለጊዜው በእግር በኋላ ግን በግብር ምሰለኝ) ብሎታል፤ ወልደ ነጐድጉዋድ ወፍቁረ እግዚእ ቅዱስ ዮሐንስም ሞትን እንደማይቀምስ እንዲሁ ተናግሮለታል::

❖ ይህች ዕለትም እነዚህ ሁሉ ተግባራት የተከናወኑባት ናትና በእጅጉ ትከበራለች፤ አባቶቻችን ዻዻሳትም ከጌታና ከደቀ መዛሙርቱ አብነትን ነስተው በዚህች ቀን 2ኛውን ታላቅ ሲኖዶስ ያደርጋሉ::

❖ መንፈስ ቅዱስ እየተራዳቸው ለቤተ ክርስቲያንና ለኛ ለልጆቿ የሚጠቅም መመሪያን ያወጣሉ ብለን እንጠብቃለን::

❖ በተረፈው ደግሞ ቤተ ክርስቲያንን የወረራት የጠላትን ጦር የሚሰብር ምክራቸውን የሚመክት ክፋታቸውን የሚያኮላሽ ውሳኔ ከአባቶቻችን እንጠብቃለን::

❖ መንጋው ባዝኗልና እረኝነት የተሰጣቸው አባቶቻችን እንዲነቁልንም ከተስፋ ጋር እንማጸናለን::

የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ መንፈሱ ከአባቶቻችንና ከእኛ ከኃጥአኑ ጋር በረድኤት ይኑር::

"የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ከመከራም ሥጋት ያርፋል"
ምሳ 1፥33



ለተጨነቀች ነፍስ ዕረፍት የሆነው የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ፤ እኔም ለእናንተ ከአዘጋጀው በኃዋላ በድካሜ ብዛት ሳይገባኝና ሳይገባኝ በምጽፈው ድርሳንወ ገድላት መጽሐፍት ላይ የቃላት (የፊደል) ሕፀፅ ቢገኝ በጎደለው እየሞላችሁ በጠመመው እያቃናችሁ አንብቡ በረከት ተካፈሉ እላለሁ ከምንም ጊዜ በላይ ለሀገራችንና ለዓለም ሰላም እንዲሁም ለደካማው ወንድማችሁ እንድበረታ (የተጣልሁ) እንዳልሆን ስለ እኔ ጸልዩ

"ልብህን በእርጋታ አኑረው፤ የሁሉም መጨረሻ እና የሁሉም አገልጋይ ለመሆን በጣም ትጋ ለከንቱ ንግግር ዘገምተኛና ሰነፍ ሁን፤ ነገር ግን የቅዱሳት መጻህፍትን ቃል በማወቅ በመስማት ድኅነትን የሚሰጡ ናቸውና ብልህ ሁን"
ታላቁ ባስልዮስ ዘቂሳሪያ

               ወስብሐት ለእግዚአብሔር
                              ይቆየን

───────────
                    Channel
  https://telegram.me/Tewahedo12

        FB Like Page (የፌስቡክ ፔጅ)
  http://facebook.com/Tewahedo12 

        YouTube Subscribe (ሰብስክራይብ)
https://www.youtube.com/channel/UCvYxUdv1D-5juH_P6iE7XXw
───────────
516 views✞ ባሮክ ✞, 07:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-09 18:25:33 ✥•••••●◉ ✞ ◉●•••••✥
"የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ከመከራም ሥጋት ያርፋል"
ምሳ 1፥33
                       
#ስንክሳር          
                  ዘግንቦት
#ሁለት (፪)        
              ✥•••••●◉ ✞ ◉●•••••✥
572 views✞ ባሮክ ✞, 15:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ