Get Mystery Box with random crypto!

✞ ተዋሕዶ ✞ 🇹 🇪 🇼 🇦 🇭 🇪 🇩 🇴

የቴሌግራም ቻናል አርማ tewahedo12 — ✞ ተዋሕዶ ✞ 🇹 🇪 🇼 🇦 🇭 🇪 🇩 🇴
የቴሌግራም ቻናል አርማ tewahedo12 — ✞ ተዋሕዶ ✞ 🇹 🇪 🇼 🇦 🇭 🇪 🇩 🇴
የሰርጥ አድራሻ: @tewahedo12
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 10.16K
የሰርጥ መግለጫ

"ሥርዓትን እማር ዘንድ ያስጨነከኝ መልካም ሆነልኝ"
መዝ 118 (119) ፥ 71
ይህ ቻናል የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ዶግማንና ቀኖናን ትውፊትን እንዲሁም አስተምሮን የጠበቁ የተለያዩ የሚያስተምሩ ነገሮች ይለቀቁበታ፡፡ ግሩፑ
http://t.me/OrthodoxTewahedo12
ይህ Channel #ሐምሌ 26/2010 ዓ.ም አ/ጀመረ
ለአስተያየት 📥 ➩ @Tewahedo12_bot

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 9

2023-05-01 12:50:20 ፫) ከ6ኛው-15ኛው መቶ ክፍለ ዘመን

➯ በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያንን በተመለከተ የተለያየ ቊጥር የነበረ ሲኾን፥

ለምሳሌ
➯ ሦስተኛው መ.ክ.ዘ. ድረስ ጥምቀትና ቊርባን በይፋ ምሥጢራት ተብለው ይቈጠሩ ነበር፤ በአምስተኛው መ.ክ.ዘ. ደግሞ በቅዱስ ዲዮናስዮስ ስም በተጻፈ ጽሑፍ ላይ፥ ከምሥጢረ ጥምቀትና ምሥጢረ ቊርባን ጋር ምሥጢረ ሜሮን ተጨምሮ እናገኘዋለን፤ ጥቂት ቆይቶ ደግሞ ምሥጢረ ክህነትን አካትቶት እናያለን፤ አሁን ያለውና ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን ሰባት መኾናቸውን ለመጀመሪያ ጊዜ የምናገኘው ዓሥራ ኹለተኛው መ.ክ.ዘ. ላይ ነው፤ ስለዚህ ይህ ዘመን በታወቀ በተረዳ መልኩ ጋብቻ ከሰባቱ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን አንዱ የኾነበት ጊዜ ነው፤ በሌላ አገላለፅ፥ አሁንም ጋብቻ ወደ ምን ያህል ደረጃ እንዳደገ የሚያስረዳን ነው፤ በተለይም እነ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ እነ ዘርዓ ያዕቆብ ስለ ቤተሰብ ሕይወት ያስተማሯቸው ትምህርቶችና ያወጧቸው ዐዋጆች እጅጉን ተጠቃሾች ናቸው፡፡
ይቀጥላል.....

"የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ከመከራም ሥጋት ያርፋል"
ምሳ 1፥33

" #ወአንቢበክሙ አንትሙ #ለዘኢያንበበ አይድኡ
➘ #እናንተ_አንብባችሁ_ላላነበበው_ንገሩ"

አዘጋጅ
ዲ/ን ባሮክ



ለተጨነቀች ነፍስ ዕረፍት የሆነው የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ፤ እኔም ለእናንተ ከአዘጋጀው በኃዋላ የተጣልሁ እንዳልሆን ስለ እኔ ጸልዩ     

"ልብህን በእርጋታ አኑረው፤ የሁሉም መጨረሻ እና የሁሉም አገልጋይ ለመሆን በጣም ትጋ ለከንቱ ንግግር ዘገምተኛና ሰነፍ ሁን፤ ነገር ግን የቅዱሳት መጻህፍትን ቃል በማወቅ በመስማት ድኅነትን የሚሰጡ ናቸውና ብልህ ሁን"
ታላቁ ባስልዮስ ዘቂሳሪያ

               ወስብሐት ለእግዚአብሔር
                              ይቆየን 

───────────
                    Channel
    https://telegram.me/Tewahedo12

        FB Like Page (የፌስቡክ ፔጅ)
  http://facebook.com/Tewahedo12  

        YouTube Subscribe (ሰብስክራይብ)
https://www.youtube.com/channel/UCvYxUdv1D-5juH_P6iE7XXw
 ───────────
674 views✞ ባሮክ ✞, edited  09:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-01 12:50:20

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ
           አሜን


“ሕያውን ከሙታን መካከል ስለ ምን ትፈልጋላችሁ፤ ተነሥቶአል እንጂ በዚኽ የለም"
ሉቃ 24፥5

"በበጎ ሥራ ሁሉ ፍሬ እያፈራችሁ በእግዚአብሔርም እውቀት እያደጋችሁ፥
ለጌታ እንደሚገባ ትመላለሱ ዘንድ እንለምናለን"
ቆላስይስ 1፥10-11

                    ቀናችንን በጸሎት እንጀምር

ክፍል ፫
    ✥•••••●◉ ✞ ◉●•••••✥         
ስለ ጋብቻ
    ✥•••••●◉ ✞ ◉●•••••✥

ጋብቻና በብሉይ ኪዳን ዘመናት የነበረው እድገቱ

➯ በአምስቱ የሙሴ መጻሕፍት በብሉይ ኪዳን የጋብቻ ትልቁ ዓላማ ኾኖ የምናየው ልጅ መውለድን ነው፤ በተለይ አርእስተ አበው በነበሩበት ዘመን ልጅ ትልቅ ሥፍራ የሚሰጠው ነበር፤ ከሦስቱ አርእስተ አበው መካከል በአብርሃምና በያዕቆብ የምናየው ይህንን ነው፤ የታሪክ መጻሕፍቱ ላይ ግን ምንም እንኳን በዘመኑ የነበሩት ሰዎች አብዛኞቹ ባይችሉትም ጋብቻ በአበው ከነበረው ደረጃ ጥቂት ከፍ ብሎ በአንድ ባልና በአንዲት ሚስት መካከል ብቻ እንዲከናወን ይፈለግ ነበር፡፡

➯ በጥበብ መጻሕፍት ደግሞ ልጆችን ከመውለድና ብዙ ሚስቶችን ካለማግባት በተጨማሪ አሁንም ከፍ ብሎ ልጆችን በአግባቡ ማሳደግ የጋብቻ ዓላማ ኾኖ መጥቷል፡፡

➯ ጋብቻ በእግዚአብሔርና በእስራኤል ዘሥጋ መካከል ላለው ፍቅር ትእምርት መኾኑ በግልፅ ማስተማር የተጀመረው በነቢያት ዘመን ነው፤ በዚህ ዘመን ጋብቻ
“ልጆችን ወለድሁ፤ አሳደግሁም” ከሚለውና ልጆችን ከመውለድና በአግባቡ ከማሳደግ በተጨማሪ እግዚአብሔር እንደ ሙሽራ እስራኤልም እንደ ሙሽሪት ኾነው ቀርበዋል፡፡
ኢሳ 1፥2

➯ ከዚህ ኹሉ ማጠቃለል የምንችለው፥ የመዋትያን ጋብቻ ራሱ ምን ያህል (እስከ ሰዶማዊነት ድረስ) እየወደቀ እንደ ኼደ፣ እስራኤላውያን ትርጕሙንና ለምን እንደ ተሰጣቸው እንዲያውቁት ብዙ ክፍላተ ዘመናት እንደ ወሰደባቸው ነው፤ በርግጥ ይህ የኾነበት ዋና ምክንያት ምን እንደ ኾነ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ የሮሜ መልእክትን በተረጎመበት ዓሥራ አንደኛው ድርሳኑ ላይ እንዲህ ያስረዳናል

“ከክርስቶስ መምጣት በፊት ሰውነታችን ኃጢአት በቀላሉ የሚያጠቃው ነበር፤ በሰው ልጆች ላይ ሞት ከተፈረደ በኋላ ቊጥር የሌላቸው ፍትወታትም አብረው ወደ ባሕርዩ ዘልቀው ገብተዋልና፤ ከዚህ የተነሣም ምግባር ትሩፋትን ለመያዝ መፋጠን ቀላል አልነበረም የሚረዳ መንፈስ ቅዱስ ወይም ኃይል የምትኾን ጥምቀት ገና አልነበሩምና፤ በታሰረለት ልጓም መሠረት የማይጓዝ ፈረስ እንዲሁ ወደ መራው እንደሚኼድና ደጋግሞ እንዲወድቅ ምን መሥራት እንዳለባቸውና ምን መሥራት እንደሌለባቸው ይነግራቸው ዘንድ የተሰጠው ሕግም በቃላት ደረጃ ምክር ከመስጠት የዘለለ ኃይል አልሰጣቸውም ነበር”


የጋብቻ እድገት በሐዲስ ኪዳን

➯ በብሉይ ኪዳኑ እድገት ላይ እንዳየነው ጋብቻ በዘመናት ኺደት እያደገ መጥቷል፤ ሐዲስ ኪዳን ሲቃረብ ደግሞ የበለጠ እጅግ ከፍ አለ፤ የሐዲስ ኪዳን ምልክት ኾነው የመጡት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምና መጥምቁ ዮሐንስ ደናግል ናቸውና፡፡

➯ ጌታችን ኃይለ ጥምቀትን ከሰጠ በኋላ ደግሞ ፍጹም ተለወጠ፤ ቀድሞ በብሉይ ኪዳን ኃይለ ጥምቀት ስላልነበረች በአንዲት ሚስት መጽናት ያቅት የነበረው አሁን ግን አንዲት ሚስትም መተው ወደሚቻልበት ዓቅም አደገ እስኪ በዘመናት ከፋፍለን እንየው

፩) በመጀመሪያው መቶ ክፍለ ዘመን

➯ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከተጠመቀ በኋላ ሳይውል ሳያድር መጀመሪያ የኼደው ወደ ገዳም ነበር፤ በሌላ አገላለፅ የመጀመሪያው የቅድስና መንገድ አድርጎ ያሳየን ድንግልና (ምንኵስና) ነበረ ዳግማዊ አዳም እንደ መኾኑም፥ ቀዳማዊ አዳም ሊኖረው ይገባው የነበረውን ሕይወት ኖረ፡፡
ማቴ 4፥1

➯ በገዳመ ቆሮንቶስ አርባ ቀንና አርባ ሌሊት ከቆየ በኋላም አገለግሎቱን የጀመረው በሰርግ ቤት ነው፤ በዚህም የድንግልና ሕይወትን መኖር ለማንችል ሰዎች የጋብቻ ሕይወትን ሲባርክልን ነው፤ መባረክ ብቻ ሳይኾን ሲያስተምርም እነ ረቢ ሒለልና ረቢ ሻማይ የተለያዩበትን ትርጓሜ ለጠየቁት ፈሪሳውያን አማናዊ ትርጕሙን ሰጣቸው፡፡
ዮሐ 2፥1-11

➯ ሰዎች በጋብቻ ላይ የነበራቸው እምነት እየተስተካከለ እንዲኼድና እግዚአብሔር ጋብቻን ለሰዎች የሰጠበት ዋና ዓላማ ዓላማቸውን አድርገው እንዲኖሩበት አስተማራቸው፤ እንዲህ በማለት
“ሙሴ ስለ ልባችሁ ጥንካሬ ሚስቶቻችሁን ትፈቱ ዘንድ ፈቀደላችሁ፤ ከጥንት ግን እንዲህ አልነበረም”
ማቴ 19፥8

➯ “ስለ ልባችሁ ጥንከሬ” ማለትም ስለ በደላችሁ ስለ ኃጢአታችሁ ከዚሁ የተነሣም ስለ መድከማችሁ ሲል ነው፤ ባል ሚስቱን ሲጠላት ልቧን እያሸ የሚገድላት ስለ ኾነ ሴቲቱም ባሏን ስትጠላው መርዝ አጠጥታ ሥራይ አብልታ የምትገድለው ስለ ኾነች፥ ከሚገዳደሉ እንዲለያዩ ፈቀደላቸው፤ አሁን ግን ይህ ተከለከለ ፍቺ፣ ዝሙት ፈጽሞ የማይቻል ኾነ፡፡

➯ የቅዱስ ጳውሎስ መልእክታትን በተለይም የቆሮንቶስንና የኤፌሶን መልእክትን ስናያቸው ደግሞ ቅዱስ ጳውሎስ ቢቻል ቢቻል ሰው ኹሉ እንደ እርሱ ድንግል እንዲኾን አስተማረ፤ ራሱን መግዛት የማይችል፣ የዝሙት ጠንቅ ያለበት ግን እንዲያገባ ፈቀደለት፤ ይህ ያገባ ሰውም ግን ቢያገባም አንድ ሰው ሳይርበው እንደማይበላ፣ ሳይጠማው እንደማይጠጣ፣ እንቅልፉ ሳይመጣ እንደማይተኛው ባለ ትዳርም ምንም እንኳን የሚያርፍበት አስተማማኝ ቦታ ያለው ቢኾንም፥ ፈቃዱ ሳያስቸግረው እንዲሁ እንዳገኘው ሩካቤ እንዳይፈጽም አስተማረው፤ ለጸሎት ሲተጉ፣ ሲጾሙ ይህን እንዳያደርጉ በስምምነት እንዲከላከሉ አዘዛቸው፤ ጸሎት የሌለበት ጊዜ ስለሌለም በተዘዋዋሪ ቢቻል ቢቻል አግብተውም ቢኾን ወደ ድንግልናዊ ሕይወት እንዲያድጉ መከራቸው፤ ሚስት ያለችው ሚስት እንደሌለቺው ይኹን አለ፤ ዝሙትንና ፍቺንም እጅግ አጥብቆ ተጸየፋቸው፡፡

፪) ከ2ኛው-5ኛው መቶ ክፍለ ዘመን

➯ በዚህ ዘመን ውስጥ ጋብቻ እጅግ ከፍ ወዳለ ደረጃ ያደገበት ነው፤ ከኹለተኛው ሦስተኛው ከሦስተኛውም አራተኛው መ.ክ.ዘ. ጋብቻ እጅግ ከፍ ወዳለ ደረጃ ያደገበት ነው፤ ድንግልናና ጋብቻና ኹለቱ የቅድስና መንገዶች በቅዱስ አትናቴዎስ አጠራርም “ኹለቱም ጸጋዎች” በተለይም በአራተኛው መ.ክ.ዘ. እጅግ የተመነደጉበት ነው፡፡

➯ የምሥጢረ ሥላሴ ትምህርት ጥንቱንም የነበረ ቢኾንም በቀጰዶቅያ አባቶች ይበልጥ እንደ ተብራራ ኹሉ፥ የድንግልናና የጋብቻ ትምህርትም ይበልጥ የተብራራው በዚህ ጊዜ ነው፤ የድንግልና ሕይወት ወደ ምንኵስና ያደገው በዚህ ጊዜ ነው፤ የድንግልና ሕይወት መምራት ያልቻለው ደግሞ የጋብቻ ሕይወቱን ትንሽዋ ቤተ ክርስቲያን በማለት በትንሽዋ ቤተ ክርስቲያን በሚያደርጋቸው አገልግሎቶች ድኅነቱን እንዲፈጽም የተደረገው በዚህ ጊዜ ነው፡፡

➯ ለዚህ ዋና ምክንያት ተብሎ የሚጠቀሰውም ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ ስለ አባ እንጦንስ የጻፈው ገድል ነው፤ ገድሉ በጊዜው ወደ ሌሎች ቋንቋዎች መተርጐሙም ከፍ ያለ አስተዋጽኦ አድርጓል፡፡
654 views✞ ባሮክ ✞, edited  09:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-30 18:35:13
"ሰማዕትነት ስር ነው፤ ክርስቲያኖች ደግሞ ከዚኽ ስር የሚያቆጠቁጡ ምርጥ ዘሮች ናቸው፤ ብዙ ዛፍ የሚያቆጠቁጥበት ስር በለም አፈር ስለሚሸፈን አይታይም፤ ከዚያ በሚያቆጠቁጡ ዛፎች ግን ስሩ እንዴት እንደተመቸው ይታወቃል፤ ሰማዕታትም በግዙፉ ዓይናችን እንደምን ያለ አክሊል ሽልማት እንደተቀበሉ አይታየንም፤ ፍሬያቸው ግን እነርሱን መስለው እነርሱን አኽለው በሚጋደሉ ምርጥ ዘሮች ይታወቃል፤ ሰማዕታት አክብሩን ብለው አይናገሩም፤ ነገር ግን በክርስቲያኖች ልብ የሚዘሩት ፍሬ ምእመናንን በፍቅር ያስገድዳል፤ እነርሱን እንዲመስሉ ያሳስባል፤ ሰማዕታት እንደ ፍቅረኛ ናቸው፤ አንድ ሰው የፍቅረኛውን ስም በየአጋጣሚው ያነሣል፤ በዓይነ ሕሊናው ያስባል በተለያየ መልኩ ያያል ሰማዕታትም ለክርስቲያኖች እንደዚያ ናቸው፤ እጅግ የተወደዱና በፍጹም ከሕሊና የማይጠፉ ተወዳጆች ናቸው፤ የልጆቻችንን ስም በነርሱ ስም የምንሰይመው፣ ሥዕላቸውን ሥለን የምንተሻሸው የምንስመው ለሰማዕታቱ ያለንን ጥልቅ ፍቅር የምንገልጽበት መንገድ ስለኾነ ነው"

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

🇹 🇪 🇼 🇦 🇭 🇪 🇩 🇴

@Tewahedo12

@OrtodoxTewahedo12
810 views✞ ባሮክ ✞, 15:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-30 18:35:02               ✥•••••●◉ ✞ ◉●•••••✥
"የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ከመከራም ሥጋት ያርፋል"
ምሳ 1፥33
                        #ስንክሳር          
             ዘሚያዚያ #ሃያ ሦስት (፳፫)        
              ✥•••••●◉ ✞ ◉●•••••✥
533 views✞ ባሮክ ✞, edited  15:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-30 18:33:40 ✥•••••••••••••••••••●◉ ✞ ◉●•••••••••••••••••••✥

"ልብህን በእርጋታ አኑረው፤ የሁሉም መጨረሻ እና የሁሉም አገልጋይ ለመሆን በጣም ትጋ ለከንቱ ንግግር ዘገምተኛና ሰነፍ ሁን፤ ነገር ግን የቅዱሳት መጻህፍትን ቃል በማወቅ በመስማት ድኅነትን የሚሰጡ ናቸውና ብልህ ሁን"
ታላቁ ባስልዮስ ዘቂሳሪያ

ሚያዚያ ወር 
#በጠዋትና በማታ #የሚነበቡ የእየለታት #የመጽሐፍ ቅዱስ #ክፍሎች

#ሚያዚያ


“ስለዚህ የተወደዳችሁ ወንድሞቼ ሆይ ሰው ሁሉ ለመስማት የፈጠነ ለመናገርም የዘገየ ለቍጣም የዘገየ ይሁን”
ያዕቆብ 1፥19

                መልካም ንባብ 

✥•••••••••••••••••••●◉ ✞ ◉●•••••••••••••••••••✥

Share   
           🇹 🇪  🇼 🇦  🇭 🇪 🇩 🇴
    ✥••┈┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈┈••✥

              
@Tewahedo12

      
@OrthodoxTewahedo12

   ✥••┈┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈┈••✥
646 views✞ ባሮክ ✞, 15:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-30 18:33:21 https://telegra.ph/ስንክሳር-ዘወርኀ-ሚያዝያ-04-29-3
707 views✞ ባሮክ ✞, 15:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-29 20:25:50 ከበዓል በኃላ ለሰርጎ , ለልጆቾ ክርስትና የዲኮር ስራ ማሰራት ይፈልጋሉ ?



ለ ሰርግ                            ለ ክርስትና
ለ ልደት                            ለ ቀለበት
ለ ገዓት                             ለ ሽምግልና
ለ ተማሪዎች ምረቃ           ለ ልጆች ልደት
ለ ቤት ምርቃት                   ለ ሆቴል ምረቃ
ለ ስብሰባ አዳራሾች          ለ ቤተሰብ ኘሮግራሞች
ለ ሰርግ ለመኪና ዲኮር
በ ቤተክርስቲያን ስርዓት ለሚፈፀሙ ሰርጎች እና ኘሮግራሞች

ለተለያዮ ዝግጅቶችም ጭምር የተለያዮ የዲኮሪሽን ስራዎችን እንሰራለን እንዲሁም የተለያዮ የዲኮር እቃዎችን እናቀርባለን !
       

     
              ይህን ይጫኑት  ...  ይህን ይጫኑት

█▓▒░        ►𝗢𝗽𝗲𝗻◄░►𝗢𝗽𝗲𝗻       ▒▓█
█▓▒░         ►𝗢𝗽𝗲𝗻◄░►𝗢𝗽𝗲𝗻      ▒▓█
█▓▒░         ►𝗢𝗽𝗲𝗻◄░►𝗢𝗽𝗲𝗻      ▒▓█
█▓▒░        ►𝗢𝗽𝗲𝗻◄░►𝗢𝗽𝗲𝗻       ▒▓█


Tel .   +251961064953
                 +251703504953
.
165 viewsመንፈሳዊ 3k, 17:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-29 19:47:56               ✥•••••●◉ ✞ ◉●•••••✥
"የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ከመከራም ሥጋት ያርፋል"
ምሳ 1፥33
                        #ስንክሳር          
             ዘሚያዚያ #ሃያ ሁለት (፳፪)        
              ✥•••••●◉ ✞ ◉●•••••✥
185 views✞ ባሮክ ✞, edited  16:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-29 19:47:16 ✥•••••••••••••••••••●◉ ✞ ◉●•••••••••••••••••••✥

"ልብህን በእርጋታ አኑረው፤ የሁሉም መጨረሻ እና የሁሉም አገልጋይ ለመሆን በጣም ትጋ ለከንቱ ንግግር ዘገምተኛና ሰነፍ ሁን፤ ነገር ግን የቅዱሳት መጻህፍትን ቃል በማወቅ በመስማት ድኅነትን የሚሰጡ ናቸውና ብልህ ሁን"
ታላቁ ባስልዮስ ዘቂሳሪያ

ሚያዚያ ወር 
#በጠዋትና በማታ #የሚነበቡ የእየለታት #የመጽሐፍ ቅዱስ #ክፍሎች

#ሚያዚያ


“ስለዚህ የተወደዳችሁ ወንድሞቼ ሆይ ሰው ሁሉ ለመስማት የፈጠነ ለመናገርም የዘገየ ለቍጣም የዘገየ ይሁን”
ያዕቆብ 1፥19

                መልካም ንባብ 

✥•••••••••••••••••••●◉ ✞ ◉●•••••••••••••••••••✥

Share   
           🇹 🇪  🇼 🇦  🇭 🇪 🇩 🇴
    ✥••┈┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈┈••✥

              
@Tewahedo12

      
@OrthodoxTewahedo12

   ✥••┈┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈┈••✥
170 views✞ ባሮክ ✞, 16:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-29 19:46:29 https://telegra.ph/ስንክሳር-ዘወርኀ-ሚያዝያ-04-25-6
161 views✞ ባሮክ ✞, 16:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ