Get Mystery Box with random crypto!

✞ ተዋሕዶ ✞ 🇹 🇪 🇼 🇦 🇭 🇪 🇩 🇴

የቴሌግራም ቻናል አርማ tewahedo12 — ✞ ተዋሕዶ ✞ 🇹 🇪 🇼 🇦 🇭 🇪 🇩 🇴
የቴሌግራም ቻናል አርማ tewahedo12 — ✞ ተዋሕዶ ✞ 🇹 🇪 🇼 🇦 🇭 🇪 🇩 🇴
የሰርጥ አድራሻ: @tewahedo12
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 10.16K
የሰርጥ መግለጫ

"ሥርዓትን እማር ዘንድ ያስጨነከኝ መልካም ሆነልኝ"
መዝ 118 (119) ፥ 71
ይህ ቻናል የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ዶግማንና ቀኖናን ትውፊትን እንዲሁም አስተምሮን የጠበቁ የተለያዩ የሚያስተምሩ ነገሮች ይለቀቁበታ፡፡ ግሩፑ
http://t.me/OrthodoxTewahedo12
ይህ Channel #ሐምሌ 26/2010 ዓ.ም አ/ጀመረ
ለአስተያየት 📥 ➩ @Tewahedo12_bot

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2023-06-11 19:28:13 ✥•••••••••••••••••••●◉ ✞ ◉●•••••••••••••••••••✥

"ልብህን በእርጋታ አኑረው፤ የሁሉም መጨረሻ እና የሁሉም አገልጋይ ለመሆን በጣም ትጋ ለከንቱ ንግግር ዘገምተኛና ሰነፍ ሁን፤ ነገር ግን የቅዱሳት መጻህፍትን ቃል በማወቅ በመስማት ድኅነትን የሚሰጡ ናቸውና ብልህ ሁን"
ታላቁ ባስልዮስ ዘቂሳሪያ

በሰኔ ወር
#በጠዋትና በማታ #የሚነበቡ የእየለታት #የመጽሐፍ ቅዱስ #ክፍሎች

#ሰኔ


“ስለዚህ የተወደዳችሁ ወንድሞቼ ሆይ ሰው ሁሉ ለመስማት የፈጠነ ለመናገርም የዘገየ ለቍጣም የዘገየ ይሁን”
ያዕቆብ 1፥19

መልካም ንባብ

✥•••••••••••••••••••●◉ ✞ ◉●•••••••••••••••••••✥

Share
🇹 🇪 🇼 🇦 🇭 🇪 🇩 🇴
✥••┈┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈┈••✥

@Tewahedo12

@OrthodoxTewahedo12

✥••┈┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈┈••✥
637 views✞ ባሮክ ✞, 16:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-11 19:28:02 https://telegra.ph/ስንክሳር-ዘወርኀ-ሰኔ-06-08-5
493 views✞ ባሮክ ✞, 16:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-11 10:05:59
"እውነተኛ ክርስቲያን አባቱ ክርስቶስን ይመስላል፤ ይሰደዳል እንጂ አያሳድድም፤ ይሰደባል እንጂ አይሳደብም፤ የጠፉትን ፍለጋ ይደክማል እንጂ ይባስ ብሎ አይገፈትርም፤ በወንድሙ ውድቀት ያለቅሳል እንጂ አይደሰትም፤ እንዲህ ካልሆነ ግን አባቱ ሌላ ነው፤ለእግዚአብሔር የምናቀርበው ምስጋና በጊዜውም ያለ ጊዜውም ሊሆን ይገባል፤ ባገኘን ጊዜ ብቻ ሳይሆን ባጣንም ጊዜ፤ ባለጤና በሆንን ጊዜ ብቻ ሳይሆን በታመምንም ጊዜ፤ ሲሳካልን ብቻ ሳይሆን ባልተሳካልንም ጊዜ ማመስገን መለማመድ አለብን፤ የምስጋናችን ምንጭ የሁኔታዎች መለዋወጥ ሳይሆን ስለ አምላካችን ብቻ ሊሆን ይገባዋል፤ ይህን ማድረግ ስንለማመድ በክብር ላይ ክብር ይጨመርልናል፤ እንደ አባታችን ኢዮብ የዲያብሎስን አፍ እንዘጋለን፤ ተአምራትን ማድረግ ትፈልጋላችሁን? እንኪያስ በዘፈን የደነቆረን ጀሮ መዝሙር እንዲሰማ አድርጉት፤ ሴትን በመመኘት የታወረው ዐይን ፈጣሪውን እንዲያይ አድርጉት፤ በስርቆት የሰለለ እጅ በምጽዋት እንዲዘረጋ አድርጉት፤ ወደ ኃጢአት ቤት በመሄድ ሽባ የሆነውን እግር ወደ እግዚአብሔር ቤት እንዲሮጥ አድርጉት፤ ሐሜትን በማውራት ዲዳ የሆነውን ከንፈር መልካም ንግግርን እንዲናገር አድርጉት፤ ከተአምራት ሁሉ የበለጠ ተአምር ይሄ ነው"

ምንጭ
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
864 views✞ ባሮክ ✞, 07:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-10 20:25:32
ትሑትና ትዕግሥተኛ ሁን

❖ በምድረ ገጽ ላይ ከነበሩት ሰዎች ሁሉ ይልቅ እጅግ ትሑት የነበረውን ነቢዩን ሙሴን ምሰል

“ሙሴም በምድር ላይ ካሉት ሰዎች ሁሉ ይልቅ እጅግ ትሑት ሰው ነበረ”
ዘኁ 12፥3

❖ ሁል ጊዜ መሐሪ እና ይቅር ባይ ለመሆን ሞክር ሐዋርያው

“ለማንም ስለ ክፉ ፋንታ ክፉን አትመልሱ በሰው ሁሉ ፊት መልካም የሆነውን አስቡ... ተወዳጆች ሆይ ራሳችሁ አትበቀሉ ለቁጣ ፋንታ ስጡ እንጂ ...”  ብሏልና።
ሮሜ 12፥17-19

❖ እንዲሁም ቁጣን ጊዜያዊ ስሜትን እና ንዴትን እንድናስወግድ
“ክፉውን በመልካም አሸንፍ እንጂ በክፉ አትሸነፍ” በማለት ይጠይቀናል።
ሮሜ 12፥21

❖ በእርግጥ መታገስ የሚችል ሰው ዕድለኛ ሲሆን ይህንን የማይችል ግን ደካማ ነው፤ ለዚህ ነው ሐዋርያውም
“እኛም ኃይለኞች የሆንን የደካሞችን ድካም እንድንሸከም ራሳችንንም ደስ እንዳናሰኝ ይገባናል” ያለው።
ሮሜ 15፥1

❖ ሌሎች አንተ እንዳሰብካቸው ፍጹም የሚስማሙ እንዲሆኑ አትፈልግ ነገር ግን መሆን እንዳለባቸው ሳይሆን እንደሆኑት አድርገህ ተቀበላቸው ሁላችንም ተፈጥሮን እንደራሷ አድርገን ተቀብለናል፤ ወቅቶችን ዝናባማ፤ ማዕበላማም ይሁን ሞቃታማ ተፈጥሮ ራሱን እንዲለውጥ ሳንጠይቅ ተቀብለነዋል፤ ከሰዎችም ጋርም ልክ እንዲሁ እናድርግ።

❖ ሰዎች ሁሉ ጻድቅና መልካም አይደሉም፤ ብዙዎቹ ድክመቶች ወይም የተወሰኑት ባሕርያቸውን ተቆጣጣሪ የሆነ አመሎች አሉባቸው፤ ሰዎች የተለያዩ ዓይነቶች ናቸው፤ ከእነዚህ አንዳንዶች ሁከተኞች ናቸው፤ ስለዚህ በጠባያቸው ተጽዕኖ እንደማይደረግበት ተመልካች እንሁን፤ ባሕሪያቸውንም በጥበብ እንቀበላቸው።

ምንጭ
ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ
856 views✞ ባሮክ ✞, 17:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-10 20:24:27 ✥•••••●◉ ✞ ◉●•••••✥
"የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ከመከራም ሥጋት ያርፋል"
ምሳ 1፥33
                       
#ስንክሳር          
             ዘሰኔ
#አራት (፬)        
              ✥•••••●◉ ✞ ◉●•••••✥
551 views✞ ባሮክ ✞, 17:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-10 20:23:22 ✥•••••••••••••••••••●◉ ✞ ◉●•••••••••••••••••••✥

"ልብህን በእርጋታ አኑረው፤ የሁሉም መጨረሻ እና የሁሉም አገልጋይ ለመሆን በጣም ትጋ ለከንቱ ንግግር ዘገምተኛና ሰነፍ ሁን፤ ነገር ግን የቅዱሳት መጻህፍትን ቃል በማወቅ በመስማት ድኅነትን የሚሰጡ ናቸውና ብልህ ሁን"
ታላቁ ባስልዮስ ዘቂሳሪያ

በሰኔ ወር
#በጠዋትና በማታ #የሚነበቡ የእየለታት #የመጽሐፍ ቅዱስ #ክፍሎች

#ሰኔ


“ስለዚህ የተወደዳችሁ ወንድሞቼ ሆይ ሰው ሁሉ ለመስማት የፈጠነ ለመናገርም የዘገየ ለቍጣም የዘገየ ይሁን”
ያዕቆብ 1፥19

መልካም ንባብ

✥•••••••••••••••••••●◉ ✞ ◉●•••••••••••••••••••✥

Share
🇹 🇪 🇼 🇦 🇭 🇪 🇩 🇴
✥••┈┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈┈••✥

@Tewahedo12

@OrthodoxTewahedo12

✥••┈┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈┈••✥
587 views✞ ባሮክ ✞, 17:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-10 20:23:12 https://telegra.ph/ስንክሳር-ዘወርኀ-ሰኔ-06-08-4
614 views✞ ባሮክ ✞, 17:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-10 13:42:34 https://telegra.ph/በጎነት-04-13
869 views✞ ባሮክ ✞, 10:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-09 07:45:22

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ
           አሜን

"በበጎ ሥራ ሁሉ ፍሬ እያፈራችሁ በእግዚአብሔርም እውቀት እያደጋችሁ፤ ለጌታ እንደሚገባ ትመላለሱ ዘንድ እንለምናለን"
ቆላስይስ 1፥10-11

           ቀናችንን በጸሎት እንጀምር

        ✥••┈••●◉ ✞ ◉●••┈••✥
ዲያብሎስን ድል የምንነሣው እንዴት ነው
        ✥••┈••●◉ ✞ ◉●••┈••✥

➯ ክብር ይግባውና ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በገዳመ ቆሮንቶስ እንዳስተማረን ወደ እግዚአብሔር በመጠጋት ፣ ምንም ዓይነት ረሀብና ቸነፈር ቢወርድብንም እግዚአብሔር እኛን መመገብ እንደሚቻለው በማመን ፣  በእጃችን ባለው ሀብት ንብረት ሳይኾን በእግዚአብሔር ስንመካ ፣ በሰው ሳይኾን በእግዚአብሔር ስንታመን ፣ ከእኛ ዓቅም በላይ ሳንጨነቅና የሚያስጨንቀንን ኹሉ ለመድኃኔዓለም አሳልፈን ስንሰጥ ዲያብሎስን ድል ማድረግ ይቻለናል፤ ስግብግብነትና የድኻውንና የምስኪኑን ማኅበረ ሰብዕ ንብረት መሻት በእኛ ላይ ሲሰለጥን ግን ዲያብሎስ ድል ያደርገናል፡፡

➯ ልጆቼ ! ሰይጣን አሁንም በሰዎች አድሮ ጌታችንን እንደፈተነው ይፈትነናል " እጅ ብትነሣልኝ ይህንና ይህን አደርግልሃለሁ " ይለናል፤ ጌታችን ዲያብልስን ድል በነሣው ጊዜ መጽሐፍ ሲናገር፤ ይኸውም ከዚያ በኋላ በሰዎች አድሮ ፈተነው እንጂ እርሱ ራሱ በቁሙ ሊፈትነው አልመጣም ሲል ነው፡፡

" እስከ ጊዜው ድረስ ተወው " ይላል፡፡
ሉቃ 4፥13

➯ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዲያብሎስን ድል ባደረገው ጊዜ "መላእክት መጥተው አገለገሉት" ይላል መላእክቱን ከዚያ በፊት እንዲመጡ አላደረጋቸውም፤ ይኸውም ሰይጣን "ኢየሱስ ክርስቶስ ድል ያደረገኝ መላእክት ረድተውት ነው" ብሎ ምክንያት እንዳያመጣ ነው፡፡

➯ አንድም 'ዲያብሎስን እንዲህ ድል ስታደርጉ ቅዱሳን መላእክት መጥተው ያገለግሏችኋል' ሲለን ነው፤ ይኸውም አልዓዛር ድህነቱን፣ በሽታውን፣ አጽናኝ ማጣቱን ፣ በአጠቃላይ የደረሰበትን ችግር ሁሉ ድል ሲያደርግ መላእክት መጥተው ወደ አብርሃም ዕቅፍ እንደወሰዱት ማለት ነው።
ሉቃ 16

➯ ልጆቼ ! ይህን ታውቁ ዘንድ እወዳለው፤ ዲያብሎስ የሚፈትነው በየገዳማቱ ፣ በየዋሻውና በየገደሉ ያሉትን ብቻ አይደለም፤ ዲያብሎስ በከተማ ላለነውም እንዲኹ ይፈትነናል፤ በገበያው ቦታ ይፈትነናል፤ በየወኅኒው ቤቱ ይፈትነናል፤ በቁሙ ራሱ ላይመጣ ይችላል፤ ደቀ መዛሙርቱን በመላክ ፣ በራሳችን ምኞት አድሮም ይፈትነናል እንጂ፡፡

➯ ታዲያ ምን እናድርግ ? ፈጽመን አንመነው፤ ጆሯችንን አንስጠው አመስጋኝ መስሎ ቢመጣም ፈጽመን እንጥላው፤ አብዝቶ "ይህን ላድርግልህ" ቢለንም እኛም አብዝተን እንራቀው፤ ምክንያቱም በቀዳማይቱ ሔዋን ያደረገውን ስንመለከት አስቀድሞ ልቧ ከንቱ በኾነ ተስፋ እንዲሞላ አደረገ፤ ቆይቶ ግን በዚሁ "ተስፋ" ጣላት ፣ ታላቅ በደልም እንድትፈጽም አድርጓታልና፡፡

➯ ልጆቼ ! ዲያብሎስ እጅግ አረመኔ የኾነ ጠላት ነው፤ የተሰጠንን ጸጋ እስክንጥል ድረስ እኛን እንዲህ ባሉ ጦርነቶች አብዝቶ ይዋጋናል፤ ስለዚህ እንራቀው፤ በቃል ብቻ ግን አይደለም፤ በገቢርም እንጂ በሕሊና ብቻ አይደለም፤ በስራም ጭምር እንጂ፤ እርሱ የሚወደውን ሥራ ከመሥራት ፈጽመን እንከልከል፤ መከልከል ብቻ ግን በቂ አይደለም ፤ እግዚአብሔር የሚወደውንም ጭምር እናድርግ እንጂ፡፡

➯ ዲያብሎስ መጠነ ብዙ ተስፋ ሊሰጠን ይችላል፤ ኾኖም ይህን የሚያደርገው እኛን ለመውሰድ እንጂ ለመስጠት አይደለም፤ ከባባድ የስርቆት ወንጀሎችን ሠርተን ባለጸጋ እንድንኾን ይጋብዘናል፤ በዚህ ምድር ፍሬ ብቻ እንድንቀማጠል አግዝፎ ያሳየናል፤ ኾኖም ይህን የሚያደርገው ጽድቅ ከእኛ እንድትርቅ ፣ ደግሞም ሰማያዊውን ሀብት እንድናጣ ፈልጎ ነው፤ እዚህ ምድር ላይ ባለ ጸጋ ኾነን በላይኛው ቤታችን ለምነን እንኳን የማናገኝ ድኾች ሊያደርገን ሽቶ ነው፡፡

"የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ከመከራም ሥጋት ያርፋል"
ምሳ 1፥33

" #ወአንቢበክሙ አንትሙ #ለዘኢያንበበ አይድኡ
➘ #እናንተ_አንብባችሁ_ላላነበበው_ንገሩ"

ምንጭ
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ



ለተጨነቀች ነፍስ ዕረፍት የሆነው የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ፤ እኔም ለእናንተ ከአዘጋጀው በኃዋላ በድካሜ ብዛት ሳይገባኝና ሳይገባኝ በምጽፈው ድርሳንወ ገድላት መጽሐፍት ላይ የቃላት (የፊደል) ሕፀፅ ቢገኝ በጎደለው እየሞላችሁ በጠመመው እያቃናችሁ አንብቡ በረከት ተካፈሉ እላለሁ ከምንም ጊዜ በላይ ለሀገራችንና ለዓለም ሰላም እንዲሁም ለደካማው ወንድማችሁ እንድበረታ (የተጣልሁ) እንዳልሆን ስለ እኔ ጸልዩ

"ልብህን በእርጋታ አኑረው፤ የሁሉም መጨረሻ እና የሁሉም አገልጋይ ለመሆን በጣም ትጋ ለከንቱ ንግግር ዘገምተኛና ሰነፍ ሁን፤ ነገር ግን የቅዱሳት መጻህፍትን ቃል በማወቅ በመስማት ድኅነትን የሚሰጡ ናቸውና ብልህ ሁን"
ታላቁ ባስልዮስ ዘቂሳሪያ

               ወስብሐት ለእግዚአብሔር
                              ይቆየን 

───────────
                    Channel
    https://telegram.me/Tewahedo12

        FB Like Page (የፌስቡክ ፔጅ)
  http://facebook.com/Tewahedo12  

        YouTube Subscribe (ሰብስክራይብ)
https://www.youtube.com/channel/UCvYxUdv1D-5juH_P6iE7XXw
 ───────────
1.1K views✞ ባሮክ ✞, 04:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-08 18:54:17
❖ ከወንድሞች አንዱ ወደ አባ መቃርዮስ መጥቶ..."እባክህ  ለህይወቴ የሚሆን መመሪያ ስጠኝ" አለው፤ አባ መቃርዮስም  ያንን ወንድም "ወደ መቃብር ሂድና በሙታን ላይ ክፉ ነገር አድርግባቸው"ብሎ ላከው።

❖ ያም ወንድም በሙታኑ ላይ ድንጋይ በወርወርና በመሳደብ የተላከውን ፈጽሞ መጣ፤ አባ መቃርዮስም..." ምን አሉህ?"ሲል ጠየቀው ያም ወንድም...."ምንም አላሉኝም"ብሎ መለሰ።

❖ "በነጋታው ተመልሰህ ናና አመስግናቸው" አለው፤ በነጋታውም ያ ወንድም ወደ ቦታው ሄደና ሙታኑን... "ሐዋርያት ቅዱሳን ጻድቃን..."እያለ አመሰገናቸውና ተመለሰ፤ አባ መቃርዮስም.."ምን መለሱልህ?" አለ "ምንም" ሲል መለሰ።

❖ መቃርዮስም  "ስትሰድባቸውና በድንጋይ ስትመታቸው፣ ስታመሰግናቸውና ስታወድሳቸው ምንም አልመለሱም አንተም ለነፍስህ ድህነትን ከፈለግህ እንደ ሞተ ሰው ሆነህ ኑር፤ ሰዎች ክፉ ቢያደርጉብህም ቢያመሰግኑህም ምንም አይሰማህ" አለው.....አዎ ምንም ተባልክ ምንም ምንም እንዳልሆነ ቆጥረህ...ዝም ብለህ መኖር።

“ከዝምታ የተነሣ እንደ ዲዳ ሆንሁ ለበጎ እንኳ ዝም አልሁ”
መዝ 39፥2
1.2K views✞ ባሮክ ✞, 15:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ