2023-05-18 06:40:41
#ተስፋ_ቁረጥ_እግዚአብሔር_አይሰማህም!
ምንም ነገር ይሁን ካልተቆጣጠርከው ያንተ ሆኖ ሊቀጥል አይችልም። ታጣዋለህ! እግዚአብሔር መቼም የምትጸልየውን ነገር አይሰጥህም።
እግዚአብሔር ሁሌም የሚሰጥህ ነገር ልትቆጣጠረው የምትችለውን ብቻ ነው። ምናልባት አዲስ ቤት እንዲሰጥህ ጸልየሃል፤ እናም እግዚብሔር ላንተ አንድ አፓርትመንት ያያል፤ ቤቱ የተመሰቃቀለ አይነት። ቤቱን ማስተካከል ያንተ ሃላፊነት ስለሆነ ይሰጥሃል።
ስለዚህ እግዚአብሔር ሁሌም የሚሰጥህ ልትቆጣጠረው የምትችለውን ነው። አቅምህን፣ ችሎታህን አለማወቅ ያንተው ችግር ይሆናል።
አካልህን መቆጣጠር ካልቻልክ በበሽታ፣ በጉዳት በተለያዩ ነገሮች ታጣዋለህ፡፡
የትዳር ህይወትህን የማትቆጣጠር ከሆነ (ቸል የምትል ከሆነ) ከባለቤትህ ጋር በመጣላት፣ በመሰለቻቸት ታጣዋለህ።
ልጆችህን የማትቆጣጠር ከሆነ ልጆችህን በሱስ፣ በስራት አልበኝነት ... ታጣቸዋለህ።
ገንዘብህን የማትቆጣጠር ከሆነ በአላስፈላጊ ወጪ፣ እቅድን ባላማከለ አባካኝነት ... ገንዘብህ ከፊትህ ተኖ ይጠፋል።
በሃላፊነት ያሉህን ነገሮች መቆጣጠር ካልቻልክ፣ ሁሉንም ነገር በቶሎ ለማጣት ፍቃደኛ እንደሆንክ ቁጠረው።
በዚህ የተነሳ ነው የህይወት ቀውስ የሚከሰተው፤ ስለዚህ በዙሪያህ ያሉትንና ያሉህን ነገሮች ሁሉ በብልሃት ልትቆጣጠራቸው ይገባል።
የማይልስ ሙንሮ ሁለት መጽሐፍት
#አስቸጋሪ_ሁኔታዎችን_ማሸነፍ እና #የመሪነት_ሳይንስ
በየመጽሐፍት መደብሩና በአዟሪዎች እጅ ይገኛሉ
(በየቀኑ አነቃቂ መልእክቶችን፣ ከምናሳትማቸው መጽሐፍት ፒዲኤፍ፣ የገንዘብና የመጽሐፍት ሽልማቶችን ለማግኘት የፌስቡክና ቴሌግራም ገጾቻችንን ይቀላቀሉ።)
Telegram- https://t.me/teklu_tilahun
Facebook- http://shorturl.at/
2.8K views03:40