2022-07-11 13:41:48
#ኢትዮጵያ_ልዩ_ናት
#ሉባር እና ሰርድዮን የተሰኙ ሁለት መጽሀፍት በገበያ ላይ ማዋላችንን በመግለጽ ሀገራችንን ከዓለም ልዩ የሚያደርጋትን የገለጸ ይሸለማል በሚል ማወዳደራችን ይታወቃል፡፡ በውድድሩ አንደኛ የወጣችው ኢትዮጵያን ልዩ የሚያደርጋትን እንደዚህ ገልጻታለች፡፡
#ኢትዮጵያ_ልዩ_ናት
አዎ ኢትዮጲያ ልዪ ናት እንዴት ቢባል ስለኢትዮጲያ መግለፅ ቢከብድም፦አሁን የረር ብለን በምንጠራ ኤረርዐዳም ከገነት በተባረረ ጊዜ መላእክት ያስተማሩትን የሠማይና የምድር ሚስጥራት የህይወት መፅሀፍ (መፅሀፈ ራዚኤልን) በእግዚዐብሄር ፈቃድ በግዕዝ ቋንቋ ፅፎ በዚህ የረር(ኤረር) ተራራዎች ከመሬት በታች በሆነዉ ስዉሩ ስፍራ አኑሮታል ኢትዮጲያም ባለፉት ዘመናት ውስጥ ይህን መፅሀፍ ተጠቅማ ሀያል ሆና ነበር...
ጀርመናዉያንና ሌሎችም የዉጪ ሀገራት የግዕዝ ቋንቋን በየሀገራቸዉ በዲግሪና በማስተርስ ደረጃ የሚያስተምሩት ለጠቅላላ አዉቀት ዐይደለምኮ የቋንቋዎች ሁሉ መጀመሪያ የጥበብ መነሻ መሆኑን ስላወቁ ነዉ...
ጀምስ ብሩስ ፅድቅን ፍለጋኮ ዐይደለም በኢትዮጲያ ገዳማት ለዐመታት ግዕዝ ሲያጠናና ሲባዝን የኖረዉ ትልቁንና የስልጣኔ እንዲሁም የጥበባት ሁሉ ሚስጥራትመከማቻ የሆነዉን ኢትዮጲያ ዉስጥ ብቻ የሚገኘዉን መፅሀፈ ሄኖክን ፍለጋንጂ...
ዛሬ ላይ ምዕራባዉያኑ ከኛ በሠረቁት የጥበብ መፅሀፍት ተጠቅመው የሚሠዉር ልብስ ሰራን ሲሉ ይሰማሉ ይህ ግን ኢትዮጲያን ጠንቅቆ ለሚያዉቃት ብርቅ አይደለም ምክንያቱም የቀደሙት ዐባቶቻችን ዕፀ ልባዊትን ተጠቅመዉ በጦርነት ጊዜ ዐብያተ ክርስቲያናትን፣ ብርሀና መፃህፍታትን እንዲሁም እራሣቸዉን ይሠዉሩ ነበር ይህቺ ዕፀ ልባዊት ዐሁንም ኢትዮጲያ ዉስጥ ትገኛለች።
ገነትን ከሚያጠጡት ዐራቱ ዐፍላጋት መሀል ዐንዱ ጊዮን(ዐባይ) ኢትዮጲያ ዉስጥ ነዉ ሚገኘዉ መየ ህይወት(የህይወት ዉሀም) እዚሁ አከባቢ ሊገኝ እንደሚችል ይገመታል መነሻዉ ጣና ሀይቅም በገዳማቱና በዉስጡ ብዙ ሚስጥራትን ይዞ ዪገኛል...
በዛሬዉ ዘመን በዐዉሮጵላን በዐየር ላይ ሊኬድ ይችላል የቅኔዉ ሰዉ ተዋናይ ግን በጥበብ በደመና ተጭኖ ይጓጓዝ ነበር...
እመቤታችንን በቀራኒዮ በእናትነት ለዐለም ከመሠጠቷ በፊት እኛ ኢትዮጲያዉያን ግን የዐስራት ልጆቿ የመጀመሪያ ለጆቿ ነበርን።
እኛ አዚህ እንጊሊዘኛ ያወራ እንደምሁር ስንቆጥር ምዕራባዉያኑ ግን ግዕዝ በማስተርስ ደረጃ እየተማሩ ቅኔ ሊዘርፉብን ነዉ ምክንያቱም ኢትዮጲያ ብቻ ውስጥ የሚገኘው ግዕዝ የቋንቋ ሁሉ መጀመሪያ የጥበብ መነሻ ስለሆነ ነዉ።
እኛ እዚህ በሠጡን ካልኩሌሽን ስንባዝን እነሱ ግን ከኛ በሠረቁት የጥበብ መፅሀፍት እየተራቀቁ የስልጣኔ ጥግ ላይ ደርሠዋል...
ኢትዮጲያ የሰዉ ልጅ፣የሥልጣኔ የቋንቋ ፣የጥበብ...መጀመሪያ ናት ኢትዮጲያዉያንን ከሌሎች ጋር ለመመሣሠል እንጥራለን እንጂ ኢትዮጲያ ልዩናት...
እጹብ ጌታነህ
143 ላይክ ያገኘች
#ሉባር 3ተኛ ዕትም
#ሰርድዮን አዲስ መጽሐፍ በገበያ ላይ
*
ቤተሰብ ይሁኑ
Facebook- https://www.facebook.com/booklandbook/
Telegram- https://t.me/teklu_tilahun
3.9K views10:41