2022-05-21 14:51:28
ከ አማራ ህዝባ ሀይል (ፋኖ) የተሰጠ መግለጫ።
የአማራ ሕዝብ በኑሮ ውድነት፣ በህልውና ስጋት፣ በወረራ እና በመሳሰሉት ችግሮች ውስጥ እንዲዳክር ያደረገው መሰረታዊ ምክንያት የሀገሪቱ የፖለቲካ ብልሽት እንደሆነ ይታወቃል። ይህንን የፖለቲካ ብልሽት ያመጡት ደግሞ ደካሞች እና ግብዞች የተሰባሰቡበት የአማራ ብልፅግና ነው።
በሀገሪቱ የፖለቲካ የኃይል ሚዛን ውስጥ የሚወክለውን ህዝብ ወርድ እና ቁመት የሚመጥን የኃይል አሰላለፍ ማስመር ያልቻለው እና ከስህተቱ መማር የማይችለው ቡድን ከዚህ ቀደም በኮራባሎች አሁን ደግሞ በቴክኖክራቶች ታግዞ አንድ ጋት አሻግሮ መመልከት በማይችለው እይታው አማራውንም ኢትዮጵያንም ወደ ከፋ አዘቅት ውስጥ እየከተተ ይገኛል።
"የኦህዴድ-ኦነግ-ኦፌኮን ጥምረት" ለማስደሰት በሚደረግ ሩጫ ውስጥ ውድ የአማራ ልጆችን ህይወት ለመቅጠፍ ሌት ከቀን እየባዘነ ይገኛል። የፌደራል መንግስትም ሆነ የክልሉ መንግስት ባወጡት መግለጫ ህግ የምናስከብረው ሰዉ ወጦ መግባት ስላልቻለ፣ ስለተዘረፈ ነው ይበሉ እንጅ እነሱ እየጨፈጨፉት ያለው ይህንኑ ወንጀል ተሰራበት የሚሉትን ህዝብ ነው።
ኦነግ ሸኔ በሽወች የሚቆጠሩ አመራሮችን ገድሏል። ሁለት ሶስት ዞኖችን ተቆጣጥሯል። በብዙ የወለጋ እና ምዕራብ ሸዋ አካባቢወች ባንዲራውን ሰቅሏል። የሚታገለውም የኦሮሞ ነፃ መንግስት ለመመስረት መሆኑ ይታወቃል። ፋኖን ከሸኔ ጋር ለማመጣጠን የሚያበቃ አንዳችም ነገር ባይኖርም ብአዴን የኦሮሞ ብሔርተኞችን ለማስደሰት በሚያደርገው ሩጫ ውስጥ ራሱን ጠልፎ እየጣለ መሆኑን ሊገነዘበው ይገባል።
ሞጣ፣ ወልድያ እና መርዓዊን ጨምሮ ከቀናት በፊት የሰላም አየር የነበረባቸውን ከተሞች የወራሪ ጦር ዘመቻ በሚመስል መልኩ በንፁሃን የደም ጎርፍ ያጠበው ክልሉን አስተዳድራለሁ የሚለው ኋላ ቀር መንግስት መሆኑ የአደባባይ ሐቅ ነው።
በብዙ የክልሉ አካባቢወች አፈናውን የሸሹ ወጣቶች፣ ፋኖወች እና ምሁራን ጫካ ገብተዋል። በአንዳንድ አካባቢወችም አፈናውን የመከላከል ውጊያ እየተደረገ ነው። ይሁን እንጅ የክልሉ መንግስት በያዘው የእብሪት እና የግብዝነት አቋም በመቀጠሉ ክልሉ በከፍተኛ ውጥረት ውስጥ ይገኛል።
ስለሆነም በህግ ማስከበር ስም ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ፣ ያለ ተጨባጭ ወንጀል፣ ያለ አስቸኳይ ግዜ አዋጅ ግለሰቦችን የማፈን እና ወደ Concentration ካምፕ የማስገባት ህገ ወጥ አሰራር እንዲቋረጥ እንዲሁም በኑሮ ውድነት እየተጠበሰ ባለው ከተሜ እና በማዳበሪያ እጥረት በሚሰቃየው አርሶ አደር ላይ የተጀመረው "ወረራ" በአስቸኳይ እንዲቆም ሁሉም በየድርሻው ርብርብ እንዲያደርግ እናሳስባለን።
አዲስ ትውልድ! አዲስ አስተሳሰብ! አዲስ ተስፋ!
ግንቦት 13 ቀን 2014 ዓ.ም
ባሕር ዳር-ኢትዮጵያ
@shewapress
@Shewapress
11.8K viewsedited 11:51