Get Mystery Box with random crypto!

የእግዚአብሔር ጸጋ ወንጌል\ The Gospel of the grace of God\

የቴሌግራም ቻናል አርማ praise_to_our_god — የእግዚአብሔር ጸጋ ወንጌል\ The Gospel of the grace of God\
የቴሌግራም ቻናል አርማ praise_to_our_god — የእግዚአብሔር ጸጋ ወንጌል\ The Gospel of the grace of God\
የሰርጥ አድራሻ: @praise_to_our_god
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.97K
የሰርጥ መግለጫ

“For I am not ashamed of the gospel of Christ, for it is the power of God to salvation for everyone who believes, for the Jew first and also for the Greek.”
-Rom.1:16
ተከታታይ የሮሜ ትምህርት
@Grace_Century
@Grace_Century
Please Contact @Ephraim_Gebreyesus

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-09-02 08:09:45 #WORD_OF_THE_DAY
“.......#የተትረፈረፈ_ምስጋና_እያቀረባችሁ_ኑሩ።”
— ቆላስይስ 2፥7 (አዲሱ መ.ት)
አንድ የእግዚአብሔር ሰው እንዲህ ይላል
"Murmuring and complaining are the language of unbelief; Thanksgiving is the language of Faith"
ስለዚህ ምስጋና የእምነት ቋንቋ ነው ስለዚህ #መፅሐፍም #እያጉረመረማችሁ #ኑሩ #ሳይሆን #ምስጋና #እያቀረባችሁ #ኑሩ ነው የሚለው።
በክርስቶስ የሆነ ሰው አመስጋኝ ነው
መልካም የምስጋና ቀን
@whoweareinchrist
34 viewsSamuel Wondimu, 05:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 02:27:31
የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ጸጋ ወንጌል ቴሌግራም ቻናን ላይ ቤተሰብ የሆናችሁ ወንድሞች እና እህቶች በዚህ ቴሌግራም ላይ #ስለ_እግዚአብሔር_ጽድቅ በሚል ትምህርት በተከታታይ ስናስተምር ቆይተናን ከዚህ በፊት ፖስት የተደረጉ ትምህርቶች ሊንኩን ተጭናችሁ ማየት ትችላላችሁ።

ምዕራፍ አንድ
#የእግዚአብሔር_ጽድቅ

#ክፍል=አንድ
#ጽድቅ_ምንድነው? (መግቢያ)

https://t.me/PRAISE_TO_OUR_GOD/3035

ክፍል ሁለት
#በእምነት_የሚገኝ_ጽድቅ

https://t.me/PRAISE_TO_OUR_GOD/3036

ክፍል ሶስት

#የእግዚአብሔር_ጽድቅ_በእምነት_ወይስ_በኦሪት_ሕግ_ነው?
https://t.me/PRAISE_TO_OUR_GOD/3039

ክፍል አራት
#የእግዚአብሔር_ጽድቅ_በወንጌል_ተገልጧል

https://t.me/PRAISE_TO_OUR_GOD/3043

በቅርብ ቀን ክፍል አምስት ስለ ጽድቅ ትምህርት በዚህ ቻናን ላይ ፖስት ይደረጋል።

Join and follow
https://t.me/+LUMYTeZz9lk2MzM8
662 viewsInternational Evangelist Ephraim G. Jesus, edited  23:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 21:22:35
የጻድቅ ሰው መኖሪያው እምነት ከሆነ የጻድቅ ሰው ጸሎት በሥራዋ ምን ታደርጋለች?
Anonymous Quiz
95%
ኃይል
0%
ድካም
1%
ችግር
4%
መልስ የለም።
91 voters227 viewsInternational Evangelist Ephraim G. Jesus, 18:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 14:02:59
የጻድቅ ሰው ህይወት ምን ይመስላል?

በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ስለ ጻድቅ ሰው ህይወት በተመለከተ መጽሐፍ ምን ይላል፦

“ጻድቅ በእምነት ይኖራል ተብሎ እንደ ተጻፈ የእግዚአብሔር ጽድቅ ከእምነት ወደ እምነት በእርሱ ይገለጣልና።”
— ሮሜ 1፥17


ጻድቅ በእምነት ይኖራል ማለት የጻድቅ ሰው መኖሪያ እምነት እያለን ነው። ጻድቅ ከእምነት ውጭ ምንም አይነት የህይወት ስርዓት የለም።

እምነት የጻድቅ ሰው መተንፈሻ ኦክስጅን ነው፤ ማንም የሰው ልጅ በምድር ላይ ያለ ኦክስጅን መኖር እንደማይችል ሁሉ፣ ልክ እንደዚያ ደግሞ ጻድቅ ሰው ያለ እምነት መኖር እንደማይችል ግልጽ ነው።

በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ በተደጋጋሚ ተጽፎ የምታገኘው ቃል ቢሆን "ጻድቅ በእምነት ይኖራል" የሚል ሀሳብ ታገኛለህ። ይህ የሆነበት ምክንያት ደግሞ ጻድቅ ሰው የህይወቱ ስርዓት በሙሉ በእምነት ስለሆነ ነው።

ጻድቅ መኖሪያው ገንዘቡ ወይም ደሞዙ ወይም ስራው ሳይሆን ጻድቅ መኖሪያው እምነት ነው።

“ዓለማት በእግዚአብሔር ቃል እንደ ተፈጠሩ በእምነት እንረዳለን፤ ስለዚህ የሚታየው ነገር የተፈጠረው ከሚታየው እንዳልሆነ እንገነዘባለን።”
— ዕብራውያን 11፥3 (አዲሱ መ.ት)

ስለዚህ ከመንፈሳዊ ዓለም ያለውን መልካም ነገር ወደ ስጋዊ ዓለም የምንቀበለው በእጃችን ሳይሆን በእምነታችን ነው።

ይቀጥላል
የእግዚአብሔር ሰው ኤፍሬም ገ/ኢየሱስ


https://t.me/PRAISE_TO_OUR_GOD
1.3K viewsInternational Evangelist Ephraim G. Jesus, edited  11:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 03:24:44
ክፍል አራት

#የእግዚአብሔር_ጽድቅ_በወንጌል_ተገልጧል።

“በወንጌል የእግዚአብሔር ጽድቅ ተገልጦአልና፤ ጽድቁም ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻ በእምነት የሆነ ነው፣ “ጻድቅ በእምነት ይኖራል” ተብሎ እንደ ተጻፈው።”
  — ሮሜ 1፥17 (አዲሱ መ.ት)

በመጀመሪያ ደረጃ ወንጌል ምንድነው?

ወንጌል ተብሎ የተተረጎመዉ የግሪኩ ቃል Euaggelion የሚል ነው፤ ትርግሙም መልካም ዜና ማለት ነው። በዚህም፣ መልካም ዜና ያልሆነ ሁሉ ወንጌል አይባልም።

#ወንጌል_ማለት_ለማመን_የሚከብድ_የምስራች_ነው። ይህ የምስራች ደግሞ ለሰው ሁሉ የሚነገር መልካም ዜና ነው።

“በወንጌል አላፍርም፤ ምክንያቱም ለሚያምን ሁሉ ለድነት የሚሆን የእግዚአብሔር ኀይል ነው፤ ይህም በመጀመሪያ ለአይሁድ፣ ቀጥሎም ለአሕዛብ ነው።”
  — ሮሜ 1፥16 (አዲሱ መ.ት)

#_ወንጌል_ማለት_የእግዚአብሔር_ጽድቅ_የተገለጠበት_ታላቅ_የምስራች_ነው።
ሐዋርያው ጳውሎስ በወንጌል አላፍርም ያለበት ዋነኛ ምክንያት የእግዚአብሔር ጽድቅ የተገለጠበት መንገድ ስለተረዳ ነው። ወንጌል አያሳፍርም፤ ምክንያቱም ደግሞ ለሚያምን ሁሉ ድነት የሚሆን የእግዚአብሔር ሀይል ስለሆነ ነው።

#ደህንነት ኃጢአተኛው ሰው በመስቀል ሥራ የጸደቀበት ብቻ ሳይሆን ይህንን #የጽድቅ_ሕይወት_መኖር_የሚችልበትን_የእግዚአብሔር_ኃይል_ያገኘበት_ነው።

ወንጌል ለሰው ልጆች ሀጢአት አይናገርም፤ ወንጌል የሚናገረው ስለ እግዚአብሔር ጽድቅ ነው።

በወንጌል የተገለጠው የእግዚአብሔር ጽድቅ ሰዎች ሁሉ በክርስቶስ ኢየሱስ በማመን የሚገኘው ጽድቅ በእምነት እንዲቀበሉ የሚያደርግ የምስራች ነው።

#ወንጌል_የተገለጠው_የእግዚአብሔር_ጽድቅ_እንጂ_ሀጢአት_አይደለም።

   ይቀጥላል
የእግዚአብሔር ሰው ኤፍሬም ገ/ኢየሱስ

https://t.me/PRAISE_TO_OUR_GOD
676 viewsInternational Evangelist Ephraim G. Jesus, edited  00:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-24 08:13:40
የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ጸጋ ወንጌል ቴሌግራም ቻናን ላይ ቤተሰብ የሆናችሁ ወንድሞች እና እህቶች በዚህ ቴሌግራም ላይ #ስለ_እግዚአብሔር_ጽድቅ በሚል ትምህርት በተከታታይ ስናስተምር ቆይተናን ከዚህ በፊት ፖስት የተደረጉ ትምህርቶች ሊንኩን ተጭናችሁ ማየት ትችላላችሁ።

ምዕራፍ አንድ
#የእግዚአብሔር_ጽድቅ

#ክፍል=አንድ
#ጽድቅ_ምንድነው? (መግቢያ)

https://t.me/PRAISE_TO_OUR_GOD/3035

ክፍል ሁለት
#በእምነት_የሚገኝ_ጽድቅ

https://t.me/PRAISE_TO_OUR_GOD/3036

ክፍል ሶስት

#የእግዚአብሔር_ጽድቅ_በእምነት_ወይስ_በኦሪት_ሕግ_ነው?
https://t.me/PRAISE_TO_OUR_GOD/3039

በቅርብ ቀን ክፍል አራት ስለ ጽድቅ ትምህርት በዚህ ቻናን ላይ ፖስት ይደረጋል።

Join and follow
https://t.me/+LUMYTeZz9lk2MzM8
1.1K viewsInternational Evangelist Ephraim G. Jesus, edited  05:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-22 07:43:40 #ሳልወድህ_የወደድከኝ
===================
ሳልወድህ የወደድከኝ ሳልመርጥህ የመረጥከኝ
በከበረው ደም ገዝተህ እንዲያው ልጅህ ያረከኝ
አበሳዬን አራከው ቀንበሬን ሰባበርከው
(ፍቅርህ ለእኔ ልዩ ነው ስምህን ላሞጋግሰው) (፪x)

ኃጢአተኛ ሳለሁ ጽድቅ የማይገባኝ
መርገሜን ወሰደው ኢየሱስ በደሙ አነጻኝ
የከሰሰኝ ጠላት እግሬ ስር ወደቀ
በረሃው ሕይወቴ ምንጭን አፈለቀ

ሳልወድህ የወደድከኝ ሳልመርጥህ የመረጥከኝ
በከበረው ደም ገዝተህ እንዲያው ልጅህ ያረከኝ
አበሳዬን አራከው ቀንበሬን ሰባበርከው
(ፍቅርህ ለእኔ ልዩ ነው ስምህን ላሞጋግሰው) (፪x)

የዕዳ ጽህፈቴን በደሙ ደምስሶ
ጠላቴን በእጄ እረግጦ ሰጠኝ አሳልፎ
ጽኑ ስልጣን አለኝ የአምላክ ልጅ ሆኛለሁ
የፈታኝን ጌታ ተፈትቸ አከብረዋለሁ

ሳልወድህ የወደድከኝ ሳልመርጥህ የመረጥከኝ
በከበረው ደም ገዝተህ እንዲያው ልጅህ ያረከኝ
አበሳዬን አራከው ቀንበሬን ሰባበርከው
(ፍቅርህ ለእኔ ልዩ ነው ስምህን ላሞጋግሰው) (፪x)

ለዚህ የሚያበቃ ጽድቅ እንኳን ሳይኖረኝ
በሰማዩ ስፍራ በቀኙ እንዲሁ አከበረኝ
ምህረቱ ብዙ ይሄ ታላቅ ጌታ
ከእኔ ጋር ሆናችሁ በዜማ አክብሩት በልልታ

ሳልወድህ የወደድከኝ ሳልመርጥህ የመረጥከኝ
በከበረው ደም ገዝተህ እንዲያው ልጅህ ያረከኝ
አበሳዬን አራከው ቀንበሬን ሰባበርከው
(ፍቅርህ ለእኔ ልዩ ነው ስምህን a ላሞጋግሰው) (፪x)

(ዘማሪ #ተስፋዬ ጫላ)

Join and follow
https://t.me/+LUMYTeZz9lk2MzM8
303 viewsInternational Evangelist Ephraim G. Jesus, edited  04:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-20 12:00:30
እግዚአብሔር_ጽድቅ

ክፍል ሶስት

#የእግዚአብሔር_ጽድቅ_በእምነት_ወይስ_በኦሪት_ሕግ_ነው?

“ሰው በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን እንጂ፣ ሕግን በመጠበቅ እንደማይጸድቅ እናውቃለን። ስለዚህ ሕግን በመጠበቅ ሳይሆን፣ በክርስቶስ በማመን እንጸድቅ ዘንድ እኛም ደግሞ በክርስቶስ ኢየሱስ አምነናል፤ ሕግን በመጠበቅ ማንም አይጸድቅምና።”
— ገላትያ 2፥16 (አዲሱ መ.ት)

ሐዋርያው ጳውሎስ በገላ.2፥16 ላይ ያለው ሀሳብ ስንመለከት በዚህ ጥቅስ ላይ ሦስት ጊዜ ሕግን በመጠበቅ መጽደቅ እንደማይቻል ሲያመለክት፣ ሦስት ጊዜ ደግሞ በክርስቶስ ማመን ፍጹም አስፈላጊ መሆኑን ይናገራል።

ሐዋርያው ጳውሎስ በሮሜ 3፥22 ላይ በግልጽ እንደተናገረው የእግዚአብሔር ጽድቅ በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን የሚገኝ ጽድቅ ሲሆን ይህን የእግዚአብሔር ጽድቅ መቀበል የሚቻለው በእምነት ብቻ ነው።

ማንም ሰው በሕግ ስራ በመሥራት በእግዚአብሔር ፊት ጻድቅ መሆን እንደማይቻል በግልጽ ይናገራል።
ሕጉ ሰው የማጽደቅ አቅም ሆነ ብቃት የለውም።

ማንም ሰው በሕግ ስራ በመስራት መጽደቅ እንደማይችል ከታወቀ እንግዲያውስ ሰው የእግዚአብሔር ጽድቅ ተካፋይ መሆን የሚቻለው በእምነት እንጂ በሕግ ስራ አይደለም።

“እስቲ አብርሃምን አስቡ፤ “እርሱ እግዚአብሔርን አመነ፤ ጽድቅም ሆኖ ተቈጠረለት።””
— ገላትያ 3፥6 (አዲሱ መ.ት)

ሮሜ 4 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁴ አንድ ሰው ሥራ ከሠራ ደመወዙ እንደ ስጦታ ሳይሆን እንደ ተገቢ ዋጋው ይቈጠርለታል።
⁵ ነገር ግን ለማይሠራው፣ ኃጥኡን ሰው ጻድቅ በሚያደርግ በእግዚአብሔር ለሚያምን ሰው፣ እምነቱ ጽድቅ ሆኖ ይቈጠርለታል።

ሐዋርያው ጳውሎስ በሮሜ 4፥4-5 ላይ በግልጽ እንደተናገረው ለኃጥኡን ሰው ጻድቅ የሚያደርገው በእምነቱ እንጂ በስራ አይደለም። አንድ ሰው በእምነት የእግዚአብሔር ጽድቅ ተካፋይ ከሆነ በኋላ ዳግመኛ ሀጢአተኛ ሊሆን አይችልም፤ ምክንያቱም ደግሞ በክርስቶስ ኢየሱስ በማመኑ የእግዚአብሔር ጽድቅ ተብሏል።

ሐዋርያው ጳውሎስ እንዳለው የእግዚአብሔር ጽድቅ መቀበል የሚቻለው በእምነት እንጂ የኦሪት ሕግ በመጠበቅ አይደለም።

ሮሜ 9 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³⁰ እንግዲህ ምን እንበል? በእምነት የሆነውን ጽድቅ፣ ለጽድቅ ያልደከሙት አሕዛብ አገኙት፤
³¹ ነገር ግን የጽድቅን ሕግ የተከታተሉት እስራኤል አላገኙትም።

በእግዚአብሔር ጽድቅ ያለ ስራ እና ያለ ጥረት የመቀበል የሚቻለው በእምነት ብቻ ነው።

“ሕግ በመጠበቅ የሚገኝ የራሴ ጽድቅ ኖሮኝ ሳይሆን፣ በክርስቶስ በማመን ይኸውም ከእግዚአብሔር የሚመጣ፣ ከእምነትም በሆነ ጽድቅ በእርሱ ዘንድ እንድገኝ ነው።”
— ፊልጵስዩስ 3፥9 (አዲሱ መ.ት)

ይቀጥላል
የእግዚአብሔር ሰው ኤፍሬም ገ/ኢየሱስ

Join and follow
https://t.me/+LUMYTeZz9lk2MzM8


ምዕራፍ አንድ
#የእግዚአብሔር_ጽድቅ

#ክፍል=አንድ
#ጽድቅ_ምንድነው? (መግቢያ)

https://t.me/PRAISE_TO_OUR_GOD/3035

ክፍል ሁለት
#በእምነት_የሚገኝ_ጽድቅ

https://t.me/PRAISE_TO_OUR_GOD/3036
426 viewsInternational Evangelist Ephraim G. Jesus, edited  09:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-19 03:59:17 @whoweareinchrist
#እንደሚያስፈልግህ_ያውቃል
ማቴዎስ 6 (አዲሱ መ.ት)
³¹ ስለዚህ፣ ‘ምን እንበላለን? ምን እንጠጣለን? ምንስ እንለብሳለን?’ ብላችሁ አትጨነቁ፤
³² አሕዛብ እነዚህን ነገሮች ሁሉ ለማግኘት ይጨነቃሉና፤ #የሰማዩ #አባታችሁም #እነዚህ #ሁሉ #ለእናንተ #እንደሚያስፈልጓችሁ #ያውቃል።
መብል መጠጥ እና ልብስ የብዙ ሰው ጥያቄ ነው እንደውም ከዛም አልፎ ብዙ ሰው ምን እበላለው ምን እጠጣለሁ ምንስ እለብሳለው ብሎ ይጨነቃል።
ለዚህ ደግሞ ቅዱሱ መፅሐፍ የሰጠን መፍትሄ አይዞህ ጌታ ከከበረ ባትበላም ችግር የለውም ፣ ራቁትህን ብትሆንም አንድ ቀን ሰማይ ቤት ታርፋለህ የሚል የሀይማኖት ተረት እና ተስፋ ሳይሆን እግዚአብሔር እነዚህ ሁሉ እንደሚያስፈልጋችሁ ያውቃል ይላል። #የሚገርም #ነው #እግዚአብሔር #አይ #ምግብ #ምን #ያደርግላቸዋል #አይልም #እንደሚያስፈልግህ #ያውቃል። ስለዚህ እግዚአብሔር ምን እንደሚያስፈልገኝ ያውቃል አልጨነቅም ብለህ በጌታ ላይ የምትደገፈው። ““ስለዚህ እላችኋለሁ፣ #ስለ #ኑሮአችሁ ምን እንበላለን? ምን እንጠጣለን? ምንስ እንለብሳለን? በማለት #አትጨነቁ። ማቴዎስ 6፥25 (አዲሱ መ.ት)
ስለዚህ እግዚአብሔር ስላንተ ያስባል የሚያስጨንቅህን በእርሱ ላይ ጣል እንዴት እኖራለው አትበል። ጻድቅ በእምነት በህይወት ይኖራል።
ስለዚህ መንፈሳዊነት ማለት አጥተህ መራብ፣ መራቆት እና መጠማት አይደለም ይህ ምንኩስና/ጉስቁልና እንጂ መንፈሳዊነት አይደለም።
#እግዚአብሔር #ስላንተ #ኑሮ #ይህ #ሁሉ #እንደሚያስፈልግህ #ያውቃል። እዚ እውቀቱ ላይ አርፈህ ተደገፍ።
ጌታ አሳምሮ ያኖራል
መዝሙር 55:22፤ #ትካዜህን #በእግዚአብሔር #ላይ #ጣል፥ #እርሱም #ይደግፍሃል፤ #ለጻድቁም #ለዘላለም #ሁከትን #አይሰጠውም።
@whoweareinchrist
396 viewsSamuel Wondimu, 00:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-17 03:43:38
እግዚአብሔር_ጽድቅ


ክፍል=ሁለት

#በእምነት_የሚገኝ_ጽድቅ


ሮሜ 3 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²¹ አሁን ግን ሕግና ነቢያት የመሰከሩለት፣ ከሕግ ውጭ የሆነ፣ የእግዚአብሔር ጽድቅ ተገልጦአል።
²² ይህ የእግዚአብሔር ጽድቅ ኢየሱስ ክርስቶስን በማመን የሚገኝ ጽድቅ ነው።

በብሉይ ኪዳን ዘመን ይገለጣል የተባለው የእግዚአብሔር ጽድቅ በአሁኑ ሰአት ከሕግ ውጭ በሆነ መልኩ ተገልጧል። ይህ የእግዚአብሔር ጽድቅ የተገለጠው በሙሴ ሕግ ሳይሆን በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን የሚገኝ ጽድቅ ነው።

በክርስቶስ ኢየሱስ በማመን የሚገኘው የእግዚአብሔር ጽድቅ ለመቀበል እምነት ብቻ በቂ ነው።

በክርስቶስ ኢየሱስ በማመን የሚገኘው የእግዚአብሔር ጽድቅ በስራ እና በጥረት የሚገኝ ሳይሆን በእምነት የምትቀበለው ስጦታ ነው።

ጽድቅ የእግዚአብሔር ማንነት ስለሆነ፤ በእግዚአብሔር ዘንድ የነበረው ጽድቅ ወደ ሰዎች የመጣው በክርስቶስ ኢየሱስ በኩል ነው።

በክርስቶስ ኢየሱስ በማመን የሚገኘው ጽድቅ ሰዎች መቀበል የምችሉት በእምነት ብቻ ነው።

“ሰው በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን እንጂ፣ ሕግን በመጠበቅ እንደማይጸድቅ እናውቃለን። ስለዚህ ሕግን በመጠበቅ ሳይሆን፣ በክርስቶስ በማመን እንጸድቅ ዘንድ እኛም ደግሞ በክርስቶስ ኢየሱስ አምነናል፤ ሕግን በመጠበቅ ማንም አይጸድቅምና።”
— ገላትያ 2፥16 (አዲሱ መ.ት)

“እንግዲህ ምን እንላለን? ጽድቅን ያልተከተሉት አሕዛብ ጽድቅን አገኙ፥ እርሱ ግን ከእምነት የሆነ ጽድቅ ነው፤”
— ሮሜ 9፥30

“ማንም ሰው ሕግን በመፈጸም ሳይሆን፣ በእምነት እንደሚጸድቅ እናረጋግጣለን።”
— ሮሜ 3፥28 (አዲሱ መ.ት)

የእግዚአብሔር ጽድቅ የተገለጠው በሙሴ ሕግ ላይ የተመሠረተ ሳይሆን በክርስቶስ ኢየሱስ በማመን የተገለጠ ጽድቅ ነው። ሙሴ እና ነቢያት የመሰከሩለት የእግዚአብሔር ጽድቅ ከሕግ ውጭ ሲሆን ይህ የእግዚአብሔር ጽድቅ የተገለጠው በክርስቶስ ኢየሱስ በማመን ያገኘነው ጽድቅ በእምነት ተቀብለናል።

ይቀጥላል
የእግዚአብሔር ሰው ኤፍሬም ገ/ኢየሱስ
Join and follow
https://t.me/+LUMYTeZz9lk2MzM8
646 viewsInternational Evangelist Ephraim G. Jesus, 00:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ