Get Mystery Box with random crypto!

የእግዚአብሔር ጸጋ ወንጌል\ The Gospel of the grace of God\

የቴሌግራም ቻናል አርማ praise_to_our_god — የእግዚአብሔር ጸጋ ወንጌል\ The Gospel of the grace of God\
የቴሌግራም ቻናል አርማ praise_to_our_god — የእግዚአብሔር ጸጋ ወንጌል\ The Gospel of the grace of God\
የሰርጥ አድራሻ: @praise_to_our_god
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.97K
የሰርጥ መግለጫ

“For I am not ashamed of the gospel of Christ, for it is the power of God to salvation for everyone who believes, for the Jew first and also for the Greek.”
-Rom.1:16
ተከታታይ የሮሜ ትምህርት
@Grace_Century
@Grace_Century
Please Contact @Ephraim_Gebreyesus

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2022-07-29 00:53:30
አዲስ_ፍጥረት__[ለጥያቄዎ_መልስ]_ሐዋርያ_ዘላለም_ጌታቸው_-_Apostle_Zelalem_Getachew(720p).mp4

Join and follow
http://t.me/PRAISE_TO_OUR_GOD
1.8K viewsInternational Evangelist Ephraim G. Jesus, edited  21:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-28 19:35:10
1ኛ ዮሐንስ 4
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁵ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ በሚታመን ሁሉ እግዚአብሔር በእርሱ ይኖራል እርሱም በእግዚአብሔር ይኖራል።
¹⁶ እኛም እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን ፍቅር አውቀናል አምነንማል። እግዚአብሔር ፍቅር ነው፥ በፍቅርም የሚኖር በእግዚአብሔር ይኖራል እግዚአብሔርም በእርሱ ይኖራል።

http://t.me/PRAISE_TO_OUR_GOD
2.1K viewsInternational Evangelist Ephraim G. Jesus, edited  16:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-28 11:54:01 ኢየሱስ የመጣው ለመሞት ሳይሆን እኛን ለመግደል ነው!!!!
=======================================
#የሞተስ_ከኃጢአቱ_ጸድቋልና።” ሮሜ 6፥6
የፀደቅነው ኢየሱስ ስለሞተ ሳይሆን እኛ ስለሞትን ነው፤ የኢየሱስ መሞት ብቻውን አላፀደቀንም። *ይሄ ምን ማለት ነው??

ኢየሱስ ለመሞት አልመጣም እኛን ለማዳን እንጂ
ኢየሱስ ለመዋረድ አልመጣም እኛን ለማክበር እንጂ
ኢየሱስ ዝቅ ለማለት አልመጣም እኛን ከፍ ለማድረግ እንጂ። የኢየሱስ አላማ አሁን እኛ የሆንነው ነው እንጂ ያኔ እርሱ የሆነው አይደለም፤ እና ለመዋረድ አልመጣም ስል ምን እያልኩ ነው?
ሲጀመር እርሱን ማንም አጨብጭቦና ተስማምቶ አላከበረውም ልክ እንደዚሁ የሮም ወታደሮችም ይሁን ሌሎች ተስማምተው አያዋርዱትም!! ያከበረው አባቱ ነው እንጂ አህዛብም ይሁኑ አይሁድ አይደሉም።አለም ሳይፈጠር በፊትም የከበረ ነበር፤ ክብር የሚለው #ቃል ሳይኖር እርሱ ከብሮ ይኖር ነበር!!

ነገር ግን እኛን ከፍ ለማድረግ ከነበረው ከፍታ፥ የነበርንበት ዝቅታ ድረስ መውረድ ነበረበት። ልክ አንድ እቃ ወድቆብን ልናነሳው ዝቅ እንላለን የዛኔ አላማው የእኛ ዝቅ ማለት ሳይሆን የእቃው መነሳት ነው ስለዚህ ያ እቃ በወደቀበት ዝቅታ ልክ ዝቅ ማለታችን የግድ ይሆናል።
ልክ እንደዚሁ ኢየሱስ የመምጣቱ አላማ፣ ዝቅ ለማለት ሳይሆን እኛን ከፍ ለማድረግ ነው።

ወደ መጀመርያው ሀሳብ ስመጣ ደግሞ፣ ኢየሱስ የመጣው ለመሞት ሳይሆን እኛን ለመግደል ነው። ይህንን ስል እርሱ ከመምጣቱ በፊት ለህግ ለሀጥያት,ለርኩሰት ባጠቃላይ ለጨለማው ዓለም ህያው የነበርን፥ለእግዚአብሔር ዓለም ግን ሙት የነበርን ሰዎች በኤፌ 2:1-2 እንደሚለው "በበደላችንና በኃጥያታችን ሙታን (ለእግዚአብሔር ዓለም)፤ በማይታዘዙ ልጆች ላይ ለሚሰራው መንፈስ ግን ህያው ሆነን የምንመላለስ የነበርንን ሰዎች ለህግና ለሀጥያት ገድሎን ለራሱ ህያው ሊያደርገን ወደደ።

ስለዚህም የራሱን ስጋ ተጠቅሞ እኛን ገደለ። “እንዲሁ፥ ወንድሞቼ ሆይ፥ እናንተ ደግሞ በክርስቶስ ሥጋ ለሕግ ተገድላችኋል፤ ለእግዚአብሔር ፍሬ እንድናፈራ፥ እናንተ ለሌላው፥ ከሙታን ለተነሣው፥ ለእርሱ ትሆኑ ዘንድ።” ሮሜ 7፥4

ለዛ ነው የሞተስ ከሀጥያቱ ፀድቋል የሚለን፤ በክርስቶስ ስጋ ሆነን ሞተናል፤ መሞታችንንም ስናምን መፅደቃችንን እናውቃለን። ገላ 2:20 "ከክርስቶስ ጋር ተሰቅያለሁ፤ እኔም አሁን ህያው ሆኜ አልኖርም ክርስቶስ ግን በእኔ ይኖራል"።

በአዳም ወገብ ሆነን ለፅድቅ ሞተን እንደነበረ ሁሉ፤ በክርስቶስ ወገብ ሆነን ለኃጥያት ሞተናል። ሮሜ 7:6

ስለዚህ ኢየሱስ የመጣው ለመሞት ሳይሆን በስጋው በኩል እኛን ለጨለማው አለም ገድሎ ለራሱ ዓለም ህያው ሊያደርገን ነው። #አላማው_የእርሱ_መሞት_ሳይሆን_የእኛ_መገደል_ነው።

የመረጃ ምንጭ Hani Kurabachew Facebook page የተወሰደ መልዕክት ነው።


http://t.me/PRAISE_TO_OUR_GOD
793 viewsInternational Evangelist Ephraim G. Jesus, edited  08:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-28 03:17:06
.....አማኝ ነኝ!!!

እግዚአብሔር ለአዳም...

ዘፍጥረት 2
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁶ እግዚአብሔር አምላክም ሰውን እንዲህ ብሎ አዘዘው፦ ከገነት ዛፍ ሁሉ ትበላለህ፤
¹⁷ ነገር ግን መልካምንና ክፉን ከሚያስታውቀው ዛፍ አትብላ፤ ከእርሱ በበላህ ቀን ሞትን ትሞታለህና።

አለው... እንግዲህ አሁን ትዕዛዙ ይሄ ነው። አዳም ስለተሰጠው ትዕዛዝ ለማጣራት ከእርሱ በፊት የነበረ ሰው ባለመኖሩ ያለው ብቸኛ አማራጭ እግዚአብሔር የነገረውን ማመን ብቻ ነው።

በተቃራኒው ደግሞ ሰይጣን ለነአዳም...

ዘፍጥረት 3
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁴ እባብም ለሴቲቱ አላት፦ ሞትን አትሞቱም፤
⁵ ከእርስዋ በበላችሁ ቀን ዓይኖቻችሁ እንዲከፈቱ እንደ እግዚአብሔርም መልካምንና ክፉን የምታውቁ እንድትሆኑ እግዚአብሔር ስለሚያውቅ ነው እንጂ።

እግዚአብሔር "...ትሞታላችሁ..." ሲል ሰይጣን "...አትሞቱም..." አለ።

እንግዲህ አሁን ማንን እንመን የሚል ጥያቄ ውስጥ ገቡ፤ ሰይጣን የሆኑትን ትሆናላችሁ በማለት ከሆኑት አስወጥቶ በመጨረሻም እግዚአብሔርን ባለማመን ውድቀት ውስጥ ከተታቸው።

ስለዚህ የመጀመሪያው ሰው አዳም ውድቀት መንስኤ እግዚአብሔርን አለማመኑ ነው።

እምነት በእግዚአብሔር እና እግዚአብሔር በተናገረው ቃል ላይ የሚኖረን መተማመን ወይንም ድፍረት ነው።

በክርስቶስ ኢየሱስ በማመን በአለማመን ከወደቀው አዳም ተዋጅተን ለጀመርነው የክርስቲያን ህይወት እምነት መኖሪያችን ነው።

“ጻድቅ በእምነት ይኖራል ተብሎ እንደ ተጻፈ. . . . .”
— ሮሜ 1፥17

እኔ አማኝ እንጂ አላማኝ አይደለሁም!

መልካም ቀን
ሬቨረንድ ተዘራ ያሬድ

http://t.me/PRAISE_TO_OUR_GOD
1.7K viewsInternational Evangelist Ephraim G. Jesus, edited  00:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ