ክፍል አራት
#የእግዚአብሔር_ጽድቅ_በወንጌል_ተገልጧል።
“በወንጌል የእግዚአብሔር ጽድቅ ተገልጦአልና፤ ጽድቁም ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻ በእምነት የሆነ ነው፣ “ጻድቅ በእምነት ይኖራል” ተብሎ እንደ ተጻፈው።”
— ሮሜ 1፥17 (አዲሱ መ.ት)
በመጀመሪያ ደረጃ ወንጌል ምንድነው?
ወንጌል ተብሎ የተተረጎመዉ የግሪኩ ቃል Euaggelion የሚል ነው፤ ትርግሙም መልካም ዜና ማለት ነው። በዚህም፣ መልካም ዜና ያልሆነ ሁሉ ወንጌል አይባልም።
#ወንጌል_ማለት_ለማመን_የሚከብድ_የምስራች_ነው። ይህ የምስራች ደግሞ ለሰው ሁሉ የሚነገር መልካም ዜና ነው።
“በወንጌል አላፍርም፤ ምክንያቱም ለሚያምን ሁሉ ለድነት የሚሆን የእግዚአብሔር ኀይል ነው፤ ይህም በመጀመሪያ ለአይሁድ፣ ቀጥሎም ለአሕዛብ ነው።”
— ሮሜ 1፥16 (አዲሱ መ.ት)
#_ወንጌል_ማለት_የእግዚአብሔር_ጽድቅ_የተገለጠበት_ታላቅ_የምስራች_ነው።
ሐዋርያው ጳውሎስ በወንጌል አላፍርም ያለበት ዋነኛ ምክንያት የእግዚአብሔር ጽድቅ የተገለጠበት መንገድ ስለተረዳ ነው። ወንጌል አያሳፍርም፤ ምክንያቱም ደግሞ ለሚያምን ሁሉ ድነት የሚሆን የእግዚአብሔር ሀይል ስለሆነ ነው።
#ደህንነት ኃጢአተኛው ሰው በመስቀል ሥራ የጸደቀበት ብቻ ሳይሆን ይህንን #የጽድቅ_ሕይወት_መኖር_የሚችልበትን_የእግዚአብሔር_ኃይል_ያገኘበት_ነው።
ወንጌል ለሰው ልጆች ሀጢአት አይናገርም፤ ወንጌል የሚናገረው ስለ እግዚአብሔር ጽድቅ ነው።
በወንጌል የተገለጠው የእግዚአብሔር ጽድቅ ሰዎች ሁሉ በክርስቶስ ኢየሱስ በማመን የሚገኘው ጽድቅ በእምነት እንዲቀበሉ የሚያደርግ የምስራች ነው።
#ወንጌል_የተገለጠው_የእግዚአብሔር_ጽድቅ_እንጂ_ሀጢአት_አይደለም።
ይቀጥላል
የእግዚአብሔር ሰው ኤፍሬም ገ/ኢየሱስ
https://t.me/PRAISE_TO_OUR_GOD