Get Mystery Box with random crypto!

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

የቴሌግራም ቻናል አርማ ortodoxmezmur — ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit
የቴሌግራም ቻናል አርማ ortodoxmezmur — ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit
የሰርጥ አድራሻ: @ortodoxmezmur
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 136.15K
የሰርጥ መግለጫ

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ
አምላክ አሜን።
. ዝማሬ ዳዊት
የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ ትምህርቶች, መዝሙራት እና ወረባትን ከነዜማቸው ለማግኘት ቻናላችንን ይጎብኙ።
ለማንኛውም ሀሣብ, ጥቆማ, አስተያየት
@zmaredawit_messengerbot ላይ
ቢያስቀምጡልን ይደርሰናል

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 44

2023-01-28 20:19:41 መልክአ ማርያም
ሰላም ለመቃብርኪ ለኢየሩሳሌም በአድያማ፤ እንተ ይእቲ ጌቴሴማኒ ስማ፤ ማርያም ሰንበት ዕረፍተ ጽዑራን እምፃማ፤ አመ ኀደረ ላዕሌኪ ፀሐየ ቅዱሳን ዘራማ፤ ኃይለ ልዑል ጸለለኪ በመንክር ግርማ።

ዚቅ
ኢይሜንንዋ ኪያሃኒ ወአድያሚሃኒ ነያ ጽዮን ቅድስት ሀገረ እግዚአብሔር።

ማኅሌተ ጽጌ
እግዚአብሔር ጽጌ ትንቢት ለቢሶ ሥጋኪ ሥጋ ዚአነ፤ አመ አስተርአየ በምድር ወተአምረ ለነ፤ ንዌድሰኪ እንዘ ንብል ምክሃ ዘመድነ፤ ዮም በፍሥሃ ለማርያም እምነ፤ አስተርእዮ በሰማይ ኮነ።

ዚቅ
አስተርአየ ዘኢያስተርኢ፤ ኮነ እሙነ አስተርእዮቱ ለመድኃኒነ ክርስቶስ፤ እሙነ ኮነ አስተርእዮቱ፤ እምድንግል ተወልደ፤ እሙነ ኮነ አስተርእዮቱ፤ በሥጋ ረቂቅ፤ እሙነ ኮነ አስተርእዮቱ፤ በ፴ ክረምት በዮርዳኖስ ተጠምቀ፤ በበህቅ ልህቀ።

አንገርጋሪ
ኢኮነ ነግደ ወፈላሴ ሀገሪቶሙ ለቅዱሳን፤ ንሕነ ሰብአ ቤቱ ለእግዚአብሔር ኲልነ፤ አምላክ ኀደረ ውስተ ሥጋ ተአቊረ፤ እንዘ ኢይትጋባዕ በሙላድ፤ ዘድንግል መናሥግተ ኢያርኂዎ፤ ዘኪሩቤል ኢርእዮ።

አመላለስ
ዘድንግል መናሥግተ ኢያርኂሆ/፪/
ኢያርኂሆ ዘኪሩቤል ኢርእዮ ኢያርኂዎ ኢርእዮ ዘኪሩቤል/፪/

ወረብ
'አምላክ ኀደረ'/፪/ ውስተ ሥጋ ተዓቊረ እንዘ ኢይትጋባዕ አምላክ ኀደረ/፪/
ዘድንግል መናሥግተ 'ኢያርኂዎ'/፪/ ኢርእዮ ዘኪሩቤል/፪/

እስመ ለዓለም
እግዝእትየ እብለኪ ወእሙ ለእግዚእየ እብለኪ፤ ቃል ቅዱስ፤ መንበሩ ዘኪሩቤል ኀደረ ላዕሌኪ፤ ዘመንበሩ ዓቢይ ውእቱ፤ ያቀድም አእምሮ ኅሊና ሰብእ፤ መንበሩ ዘኪሩቤል ኀደረ ላዕሌኪ፤ ግሩም እምግሩማን፤ ዘመጽአ ውስተ ዓለም፤ መንበሩ ዘኪሩቤል ኀደረ ላዕሌኪ፤ ስብሐት ዘኢየኃልቅ፤ ወሰን ዘኢያንጸበርቅ፤ መንበሩ ዘኪሩቤል ኀደረ ላዕሌኪ፤ ዘይሥዕሎሙ ለሕፃናት፤ ወይነግሥ ለመላእክት መንበሩ ዘኪሩቤል ኀደረ ላዕሌኪ፤ እስመ ንጉሥ ውእቱ ሰከበ በጎል፤ ሰገዱ ሎቱ ሰብአ ሰገል፤ መንበሩ ዘኪሩቤል ኀደረ ላዕሌኪ፤ እምግርማሁ ትርዕድ ምድር ዜናዊ ስቡሕ ዘለዓለም፤ ወእስከ ለዓለም ንጉሥ ውእቱ።

ወረብ
ዘመንበሩ ዓቢይ መንበሩ ውእቱ መንበሩ ዘኪሩቤል/፪/
ያቀድም 'አእምሮ'/፪/ ኅሊና ሰብእ/፪/

@ortodoxmezmur
@ortodoxmezmur
@ortodoxmezmur
19.5K views17:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-28 20:19:41 ጥር 21 የአስተርእዮ ማርያም ክብረ በዓል ሥርዓተ ማኅሌቱ ከሊቃውንቱ ጋር ለማመስገን እንዲረዳን እንደሚከተለው ተዘጋጅቷል #በፍጥነት_ሼር_Share_ያድርጉ

አዘጋጅ በለጠ ከበደ(የጣፈጡ ልጅ)

የማንኛውም ወርኃ በዓልና ክብረ በዓል ሥርዓተ ማኅሌት መጀመሪያ "ሥርዓተ ነግሥ"
ስምዓኒ እግዚኦ ጸሎትየ ሃሌ ሉያ፤ ሃሌ ሉያ ወይብጻሕ ቅድሜከ ገዓርየ ሃሌ ሉያ፤ ሃሌ ሉያ ወኢትሚጥ ገፀከ እምኔየ፤ በዕለተ ምንዳቤየ አጽምእ ዕዝነከ ኀቤየ ሃሌ ሉያ፤ ሃሌ ሉያ አመ ዕለተ እጼውአከ ፍጡነ ስምዓኒ ሃሌ ሉያ፤ ሃሌ ሉያ ለዓለም ወለዓለመ ዓለም፤ ሃሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል፤ ንወድሶ ለዘሃሎ እግዚአብሔር ልዑል፤ ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኲሎ ዓለመ፣ በአሐቲ ቃል።

መልክአ ሥላሴ
ሰላም ለኲልያቲክሙ እለ ዕሩያን በአካል፤ ዓለመክሙ ሥላሴ አመ ሐወጸ በሣህል፤ እምኔክሙ አሐዱ እግዚአብሔር ቃል፣ ተፈጸመ ተስፋ አበው በማርያም ድንግል፤ ወበቀራንዮ ተተክለ መድኃኒት መስቀል።

ዚቅ
ሃሌ ሉያ ለአብ፤ ሃሌ ሉያ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ሥላሴ ዋህድ፤ ዕፎኑመ እመ አምላክ በከየት ደንጊፃ፤ ከመ ኲሉ ሰብእ ሞት ሶበ ሐወጻ፤ ዮሐንስ በልብሱ ከደነ ገፃ።

ወረብ
እፎኑመ እመ አምላክ በከየት ደንጊፃ በከየት እመ አምላክ/፪/
ከመ ኲሉ ሰብእ ሞት ሶበ ሐወጻ በከየት/፪/

ነግሥ
ሰላም ለዝክረ ስምኪ ዘመንክር ጣዕሙ፤ ለወልድኪ አምሳለ ደሙ፤ መሠረተ ሕይወት ማርያም ወጥንተ መድኃኒት ዘእምቀዲሙ፤ ኪያኪ ሠናይተ ዘፈጠረ ለቤዛ ዓለሙ፤ እግዚአብሔር ይትባረክ ወይትአኮት ስሙ።

ዚቅ
ሃሌ ሃሌ ሉያ፤ መጽአ ውስተ ዓለም፤ ወዓለሙኒ ኢክህለ ፀዊሮቶ፤ ፆረቶ ወአግመረቶ ማርያም።

ነግሥ
ለምንት ይዜኃር ኃያል በኃይሉ፤ ወባዕል በብዝኃ ብዕሉ፤ ኢያድለወ ሞተ ክርስቶስ ለሥጋ አባሉ፤ ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ፤ ሞታ ለማርያም የአፅብ ለኲሉ።

ዚቅ
እንበይነዝ አእምሩ በውስተ ፍትሕ ከመ ኢያደሉ፤ ትጥዓም ሞተ እሙ ወእመ ኲሉ፤ አዘዘ ወልድ በርቱዕ ቃሉ።

መልክአ ማርያም
ሰላም ሰላም ለዝክረ ስምኪ ሐዋዝ፤ እምነ ከልበኔ ወቊስጥ ወእምነ ሰንበልት ምዑዝ፤ ማርያም ድንግል ለባሲተ ዓቢይ ትእዛዝ፤ ይስቅየኒ ለለጽባሑ ወይነ ፍቅርኪ አዚዝ፤ ከመ ይሰቅዮ ውኂዝ ለሠናይ አርዝ።

ዚቅ
ለዛቲ ድንግል ሠረቀ ላዕሌሃ ብዕለ ጸጋሁ ለአብ፤ ወአግአዛ እምእኩይ ውስተ ሠናይ፤ እሞት ውስተ ሕይወት፤ ወረሰየ ይዝክሩ ስማ ውስተ ኲሉ ዓለም።

ወረብ
ለዛቲ ድንግል ሠረቀ ላዕሌሃ ብዕለ ጸጋሁ ለአብ/፪/
ወአግአዛ እምእኩይ ውስት ሠናይ እሞት ውስተ ሕይወት/፪/

መልክአ ማርያም
ሰላም ለእስትንፋስኪ ዘመዓዛሁ ሕይወት፤ ከመ መዓዛ ዕፅ ኅሩይ ዘውስተ ገነት፤ ማርያም ድንግል ቤተ ቅድሳት፤ ጽንሕኒ ውስተ ሠናይ ወሰውርኒ እሞት፤ በአክናፍኪ ርግብየ ኅሪት።

ዚቅ
አንጺሆ ሥጋሃ ቀዲሶ ኪያሃ፤ ኃደረ ቃል ላዕሌሃ፤ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፤ ወይቤላ ለድንግል፤ ሃሌ ሃሌ ሉያ፤ ሰሎሞን ይቤላ እኅትየ መርዓት ርግብየ ሠናይት፤ ፍናወ ዚአኪ ገነት፤ እስመ ኪያኪ ኀረየ ለታዕካሁ፤ ከመ ትኩኒዮ ማኅደረ ለልዑል።

ወረብ
'አንጺሆ ሥጋሃ'/፪/ ላዕሌሃ ኃደረ/፪/
ቀዲሶ ኪያሃ 'ሃሌ ሉያ'/፪/ ይቤላ ለድንግል/፪/

መልክአ ማርያም
ሰላም ለገቦኪ ዘሐመልማለ ወርቅ ክዳኑ፤ በከመ ዳዊት ይዜኑ፤ ማርያም ድንግል ለያዕቆብ ሞገሰ ስኑ፤ በልኒ እግዝእትየ አፈቅረከ አኮኑ፤ እንዘ ረዳኢትከ አነ ዘይክለከ መኑ።

ዚቅ
እምሰማያት ወረደ ወገብረ መድኃኒተ በማዕከለ ምድር፤ ኖላዊ ኄር ኖላዊሆሙ ለ፳ኤል፤ ወረደ ስኖ ለያዕቆብ ዘአፍቀረ፤ ወስኑሰ ለያዕቆብ ዘይቤ ይእቲ ሥጋ እንተ ነሥአ፤ መድኅን እማርያም።

ወረብ
ወስኑሰ ለያዕቆብ 'ዘይቤ'/፪/ ያዕቆብ/፪/
'ይእቲ ሥጋ'/፪/ እማርያም እንተ ነሥአ መድኅን/፪/

መልክአ ማርያም
ሰላም ለፀአተ ነፍስኪ እንበለ
ፃዕር ወፃማ፤ ለነቢር ዘልፈ በየማነ ወልድኪ ፌማ፤ ማርያም ድንግል ለባሲተ ሞገስ ወግርማ፤ አጽንዒ በረድኤትኪ ለሕይወትየ ድካማ፤ እምሕይወተ ኄራን አበው ኢታሕጽጺ ዐቅማ።

ዚቅ
ጊዜ ዕረፍታ ለሶልያና ወረደ ወልድ እምዲበ ልዕልና፤ ጠሊላነ ንግሥ ሶቤሃ ከደና።

ወረብ
ጊዜ ዕረፍታ ለማርያም 'ጊዜ'/፫/ ዕረፍታ ለማርያም/፪/
ወረደ ወልድ ዲበ እምዲበ ልዕልና ወረደ/፪/

መልክአ ማርያም
ሰላም እብል በድነ ሥጋኪ ጽሩየ፤ ዘተመሰለ ባሕርየ፤ ማርያም ድንግል ዐጸደ ወይንየ፤ ንስቲተ ለዕበየኪ እንተ አቅረብኩ ግናየ፤ ኢይትኃደግ ዲበ ምድር ምሥጢ ሰማየ።

ዚቅ
ኦ ትቤ ማርያም እወጽእ እምዝንቱ ሥጋየ፤ ወአሐውር ውስተ ሕይወት ዘለዓለም፤ ኦ ተዘከርኬ ዮሐንስ ዘይቤለከ ሊቅ አመ ትረፍቅ ዲበ ዕንግድዓሁ።

መልክአ ማርያም
ሰላም ለግንዘተ ሥጋኪ በእደ ሐዋርያት አርጋብ፤ በአፈወ ዕፍረት ቅድው ዘሐሳበ ሤጡ ዕፁብ፤ ማርያም ድንግል ወለተ ኅሩያን ሕዝብ፤ ረሰይኩኪ እግዝእትየ ህየንተ እም ወአብ፤ ይሕፅነኒ ከመ ጥብ ፍቅርኪ ሐሊብ።

ዚቅ
ተጋብኡ በቅጽበት ለግንዘተ እሙ ቅድስት፤ ብፁዓን ሐዋርያት ቦኡ ኀቤሃ፤ በሰላም አምኁ ኪያሃ፤ በስብሐት ገነዙ ሥጋሃ።

መልክአ ማርያም
ሰላም ለመቃብርኪ ለጌቴሴማኒ በመርኅባ፤ እንተ ይእቲ ለኢየሩሳሌም ቅሩባ፤ ማርያም ድንግል ለሀገረ መንግሥት ርግባ፤ ትትሜጦ ወረቀ እምአፌር ወጸበለ አፈው እምሳባ፤ ጌቴሴማኒ ለሥጋኪ ምስካባ።

ዚቅ
ሃሌ ሃሌ ሉያ፤ ዓውዳኒ ዘጽድቅ ወመርኅባኒ ዘዕንቊ፤ አንቀጸ አድኅኖ ሐዳስ ንጽቅ።

@ortodoxmezmur
@ortodoxmezmur
@ortodoxmezmur
18.9K views17:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-28 20:16:04
ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ በጅማ መቆየት አይችሉም ተብለው ወደ አዲስ አበባ እንዲመለሱ ተደርጓል።

እስከ አሁን ስለተመለሱበት ምክንያት በቂ መረጃ ማግኘት አልተቻለም።
19.2K views17:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-27 11:18:01
" በዚህ ሕገ ወጥ ሂደት የሰው ሕይወት መጥፋት፣ የተከበሩ አብያተ ክርስቲያናትና ገዳማት ጥቃትና፣ የባህልና የሃይማኖት ቅርሶችን ስርቆትና ዘረፋን ለመከላከል ኃላፊነት ያለበት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ የሚመራው መንግሥት ነው"
የሰሜን አሜሪካን የሲቪክ ማኀበራት ምክር ቤት

የሰሜን አሜሪካን የሲቪክ ማኅበራት ምክር ቤት ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንን ለሁለት ለመክፈል ታስቦ በሕገ ወጥ መንገድ ቀኖና ሳይጠብቅ የተከናወነውን ሢመተ ኤጲስ ቆጶሳት በመቃወም መግለጫ አውጥቷል።

የሰሜን አሜሪካን የሲቪክ ማኅበራት ምክር ቤት የተሞከረውን መፈንቅለ ሲኖዶስ በጽኑ በማውገዝ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ በአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ከሚመራው ሕጋዊ ቅዱስ ሲኖዶስ ጋር አጋርነታችንን እናረጋግጣለን ብሏል መግለጫው።

በተጨማሪም የሲቪክ ማኅበራት ምክር ቤቱ በዚህ ሕገ ወጥ ሂደት የሰው ሕይወት መጥፋት፣ የተከበሩ አብያተ ክርስቲያናትና ገዳማት ጥቃትና፣ የባህልና የሃይማኖት ቅርሶችን ስርቆትና ዘረፋን ለመከላከል ኃላፊነት ያለበት በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የሚመራው መንግሥት መሆኑን አስታውሶ። ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ እና ለዩናይትድ ስቴትስ መንግሥት ለኢ/ኦ/ተ/ቤተ ክርስቲያን ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ በማቅረብ በዚህ ፈታኝ ጊዜ ከቅድስት ቤተ ክርስቲያን ጎን እንደሚቆም በመግለጫው ጠቅሷል። መረጃው የኢኦተቤ ቴቪ ነው፡፡
27.7K views08:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ