Get Mystery Box with random crypto!

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

የቴሌግራም ቻናል አርማ ortodoxmezmur — ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit
የቴሌግራም ቻናል አርማ ortodoxmezmur — ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit
የሰርጥ አድራሻ: @ortodoxmezmur
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 136.15K
የሰርጥ መግለጫ

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ
አምላክ አሜን።
. ዝማሬ ዳዊት
የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ ትምህርቶች, መዝሙራት እና ወረባትን ከነዜማቸው ለማግኘት ቻናላችንን ይጎብኙ።
ለማንኛውም ሀሣብ, ጥቆማ, አስተያየት
@zmaredawit_messengerbot ላይ
ቢያስቀምጡልን ይደርሰናል

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2024-03-15 22:27:22 የምንጠብቀው መልስ ከላይ እንደሆነ ተነጋግረን ከጨረስን በኋላ ወደ ታች ድጋሚ መጠየቁ ስለምን ይሆን??? ምንስ አገኘን???
15.4K views19:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-15 19:21:38 ርግብና ዋኔን

ርግብና ዋኔን
አብረዉ ዘመቱና ዋኔን
ርግብ ደህና ገባች >> /2/
ዋኔን ገደሉና >> /2/

በዘርና ጎሳ ዋኔን
ሠዉ ሁሉ ተከፍሎ >>
ሰይፍንም ጨበጠ >>
ልቦናዉ ቂም አዝሎ>>
ሰላምን የሚያወርድ >>
እንድ የሚያረገንን >>
እባክህን አምላክ >>
ሙሴን አድለን >>
ሠላምህን አብዛ ምድሪቷን አሳርፍ
የቅዱሳን አምላክ በጭንቃችን ድርስ /2/


በወገን ላይ ወገን ዋኔን
ይብቃ መነሳቱ >>
ይስፈን በምድር ላይ >>
የእግዚአብሔር መንግስቱ >>
ጦራችን ይሰቀል >>
እንያዝ በገና >>
ሠላምን እናዚም >>
በፍቅር እንፅና >>
ምድሪቷን አሳርፍ ሰላምህም ይብዛ
በአንድነት አኑረን የአለሙ ቤዛ /2/


የመርገም ጨርቅ ሆነ ዋኔን
ፅድቃችን በሙሉ >>
አንተን ያልበደለ >>
ማነዉ በዘመኑ>>
አማነዉ በማታ >>
ቀን ያከበርነዉን >>
የኛ ስራ ሆኗል >>
መክሰስ የበቃው >>
ፍቅር ባትሆን ኖሮ ባያቅትህ መጥላት
አይታይም ነበር የሰዉ ልጅ በህይወት


ሊቀ ዲያቆናት ነብዩ ሳሙኤል
@ortodoxmezmur
@ortodoxmezmur
@ortodoxmezmur
13.1K views16:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-15 10:33:13 ዐብይ ጾም ለምን የንሰሐ መዝሙር ብቻ ሆነ?

ሊቀ ጉባኤ ጌታሁን ድምፀ
በዐብይ ጾም ለምን ከበሮ አይመታም
በዐብይ ጾም ለምን ፅናፅል አንጠቀመም
በዐብይ ፆም መብላት የሌለብን ምግቦች በየአመቱ ጥያቄ እሚያስነሳው ዓሳን አለመብላት

@ortodoxmezmur
@ortodoxmezmur
@ortodoxmezmur
14.1K views07:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-14 20:20:14
ቅዳሴ ክፍል 78 ይህንን ይመስላል ተለማመዱት
15.3K views17:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-14 14:46:27 እንኳን ለአባታችን ለአቡነ ገብረ መንፈስቅዱስ አመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ

#ለሀገር_ኢትነ

ለሀገር ኢትነ ሰላማ ኪያከ ተአቅብ
አባ ኦ አባ(2) ገብረ መንፈስ ቅዱስ

በዘማሪት #ገነት

@ortodoxmezmur
@ortodoxmezmur
@ortodoxmezmur
15.1K views11:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-14 08:12:40 ✞ የአምላክ ዐቃቤ ሕግ ✞

ገባሬ መንክራት በገድሉ ያወቅነው
የእግሮቹ ትቢያ የአራዊት ስንቅ ነው
ገብረ መንፈስ ቅዱስ የአምላክ ዐቃቤ ሕግ
የኢትዮጵያ ዋስ ነው ፈጥኖ የሚታደግ

ፀሐይ(2)የምድራችን ፀሐይ
በገድሉ ያበራል እስከ ጥልቁ ቀላይ
የመላዕክት ወዳጅ(2)ገብረሕይወት ሰማይ
አዝ
መብረቅ(2)ሰረገላው መብረቅ
የቃልኪዳኑ ወንዝ ቢጠጣ የማይደርቅ
የፍጥረቱ ደስታ(2)ገብረሕይወት ፃድቅ
አዝ
ኮከብ(2)ክብረገድላን ኮከብ
ዓለምን የሚያስንቅ መዐዛው የሚስብ
አርከ ሥሉስ ቅዱስ(2)ገብረሕይወት ኪሩብ
አዝ
ስኂን(2)ፄና ልብሱ ስኂን
የነፍስን አዳራሽ በገድል የሚሸፍን
የሚነበብ መፃፍ(2)ገብረሕይወት ድርሳን
አዝ
መቅረዝ(2)የማኅቶት መቅረዝ
ምድረከብድ ዝቋላን ያለመለመ ወንዝ
የዝጊቲው ፈዋሽ(2)ገብረሕይወት ምርኩዝ

ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ!
@ortodoxmezmur
@ortodoxmezmur
@ortodoxmezmur
15.5K views05:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-14 07:07:13 ​​​​ እንኳን ለአባታችን ገብረ መንፈስ ቅዱስ በዓለ እረፍታቸው በሰላም አደረሰን!

ቀኑ መጋቢት 5 ዕለቱ ቅዳሜ ለእሁድ አጥቢያ ሰዓቱ ከሌሊቱ ስድስት ሰዓት ሆኗል፤ አሁንም ህማሙን እየታገለ እያላበው በድካም ለፍጥረቱ ሁሉ ይለምናል፤

“አቤቱ ህዝብህን አድን ርስትህን ኢትዮጰያንም ባርክ” ይላል።

ህመም የጀመረው መጋቢት 3 ዓርብ ቀን ነው፤ መታመሙን የሰሙ እንደርሱ ቅዱሳን የሆኑት ዘርአቡሩክ፤ ፍሬ ቅዱስ፤ ያዕቆብ፤ ብንያምና ዮሴፍ እንዲሁም በወቅቱ የኢትዮጰያ ንጉስ የነበረው እንድርያስ ሊጠይቁት ተሰብስበዋል ወደ አጠገቡ መድረስ ግን አልተቻላቸውም አባታችን ገብረ መንፈስ ቅዱስ የሚጋርደው እንጨት ዛፍ በሌለበት በርሃ እንደ አንበሳ ተኝቶ አዩት በላዩ ያረፈው የእግዚአብሔር ጸጋ ከፊቱ የሚወጣው ብርሃን ቀይ መልኩ ረዥም የራስ ጠጉሩ እንደ ነጭ ሐር የሚሆን ጽሕሙ አስደነቃቸው።

ከሌሊቱ ሰባት ሰዓት ሲሆን ከሰማይ ታላቅ ነጎድጓድ ድምጽ ተሰማ ጌታችን መላአክትን አስከትሎ ወደ አባታችን ወረደ፤ ከሰማይ ወደ ምድር ህብሩ አምሳያው ልዩ ልዩ የሆነ እንደ ጸሐይና እንደ ጨረቃ የሚያበራ እንደ ወንጪፍ ድንጋይ ይወረወር ነበር ከዚያ የነበሩ ሁሉ ፈሩ ወደ ኋላም ሸሹ ምድር ራደች ተራሮች ኮረብቶች ተናወጡ ብርቱ ጩኸት ንውጽውጽታ ሆነ።

“ወዳጄ ገብረመንፈስ ቅዱስ ሰላም ላንተ ይሁን” እነሆ የማይታበል ቃል ኪዳን እገባልሃለው ስምህን የጠራ መታሰቢያህን ያደረገውን እጣን ቋጥሮ ግብር ሰፍሮ መባ ይዞ ቤትህ የመጣውን እምርልሃለው አንተ ከገባህበት ገነት መንግስተ ሰማያት አገባዋለሁ አለው፤

አባታችንም “አቤቱ ጌታ ሆይ የኢትዮጰያን ህዝብ ማርልኝ” አለው፤ እነሆ ምሬልሃለው አስራት በኩራት አድርጌም ሰጥቼሃለው፤ ከመጋቢት አምስት ቀን ጀምሮ ዝክርህን ያድርጉ በአማላጅነትህም ይማጸኑ አለው።

ከዚህ በኃላ ሰባቱ ሊቃነ መላክት የአባታችንን ነፍስ ሊቀበሉ ወረዱ በታላቅ ምስጋናም ወደ ሰማይ አሳረጉት ስጋውንም ይዘውት ሄዱ የት እንደተቀበረ ግን እስካሁን አይታወቅም አንዳንዱ በእየሩሳሌም ነው ይላሉ፤ ሌላው በምድረ ከብድ ነው ይላል ግን እስካሁን ልክ እንደ ሊቀ ነብያት ሙሴ ስጋ የት እንደ ተቀበረ አይታወቅም።

ገድሉ ትሩፋቱ ከሰማይ ከዋክብት ከምድር አሸዋ ይበዛል ኢትዮጰያን አብዝቶ ይወዳታል፤ ምድራዊ ምግብ አልተመገበም የእናቱን ጡት እንኳን አልጠባም፤ ልብስ፤ መጠለል አልፈለገም፤ የክረምት ቁር የበጋ ሐሩር እየተፈራረቀበት በተጋድሎ 562 ዓመት ኖረ፤ በዛሬዋ ቀን #መጋቢት_5 ሩጫውን ጨረሰ።

ለእግዚአብሔር ክብር ምስጋና ይሁን እኛንም ከአባታችን በረከት ያሳትፈን፤ ከመጣብን ክፉ መቅሰፍት ይሰውረን! አሜን።

መጽሐፈ ስንክሳር ዘመጋቢት

#ሼር
@ortodoxmezmur
@ortodoxmezmur
@ortodoxmezmur
15.4K views04:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-13 21:54:28 ​​#ክፍል_2
#ጾም_እና_ሩካቤ|ግብረስጋ ግንኙነት|

ከተጋባን በኋላስ ድንግልና ሳይሆን ወሲብ ቦታውን ይይዛል። በጋብቻ ወስጥ ሩካቤ |ግብረ ስጋ ግኑኝነት| በመጽሐፍ ቅዱስ እንዴት ይገለጻል ??

ዕብ 13፡4 ‹‹ መጋባት በሁሉ ዘንድ ክቡር መኝታውም ንጹሕ ይሁን፤ ሴሰኞችንና አመንዝሮችን ግን እግዚአብሔር ይፈርድባቸዋል››፡፡ ስለሆነም በጋብቻ ውስጥ ያለው መኝታ/ግብረ ስጋ
ግኑኝነት/ ንጹሕ ነው፤ ነውር የለበትም።

ይሄ ማለት ግን ባል እና ሚስት ሌላ ስራ
የለባቸውም፤ ሁሌም ከአልጋ አይውረዱ ማለት አይደለም። መጽሐፍ ቅዱስ በሁሉ ነገራችን መመሪያ አለው… ‹‹ነገር ግን ሁሉ በአገባብና በሥርዓት ይሁን።›› 1ኛቆሮ 14፡40፡፡

☞ ስለሆነም ሩካቤ ስጋ በቤ/ክ ገደብ ይጣልበታል ሁሌ አይፈጸምም… መቼ እንዴት ብንል?
1ኛ ቆሮ 7፡4 ‹‹ ሚስት በገዛ ሥጋዋ ላይ ሥልጣን የላትም፥ ሥልጣን ለባልዋ ነው እንጂ፤ እንዲሁም ደግሞ ባል በገዛ ሥጋው ላይ ሥልጣን የለውም፥ ሥልጣን ለሚስቱ ነው እንጂ። ለጸሎት ትተጉ ዘንድ ተስማምታችሁ ለጊዜው ካልሆነ በቀር፥ እርስ በርሳችሁ አትከላከሉ ፤ ራሳችሁን ስለ አለመግዛት ሰይጣን እንዳይፈታተናችሁ ደግሞ አብራችሁ ሁኑ።›

ይሄ የቅዱስ ጳውሎስ መልዕክት ስለ ግብረስጋ ግኑኝነት ግልጽ መመሪያ ነው። ሚስትም ባልም በገዛ ስጋቸው ስልጣን የላቸውም ስልጣኑ የትዳር አጋራቸው ነው ማለት። ባል ወይም ሚስት ከሁለት አንዳቸው ግብረ ስጋ ግኑኝነት ቢፈልጉ ሌላውን ወገን "አካሉ የኔ ነው" ብሎ መከልከል የለበትም ፤ ስልጣኑ የሱ አይደልም… ይልቁን ለትዳር አጋራችሁ
ፍላጎት የነቃችሁ ሁኑ ማለት ነው… ነገር ግን ሁሌ መፈጸም አትችሉም አለ እና የማይፈጸምበት ጊዜን ሲገልጽ ‹‹ ለጸሎት ትተጉ ዘንድ ተስማምታችሁ ለጊዜው ካልሆነ በቀር፥ እርስ በርሳችሁ አትከላከሉ ፤›› 1ኛ ቆሮ 7፡5፡፡

#ይቀጥላል
በቀጣይ ክፍል መቼ ነው ለጸሎት የምንተጋው?

@ortodoxmezmur
@ortodoxmezmur
@ortodoxmezmur
15.4K views18:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-13 14:44:25 ​​ባለ ትዳሮችን ብቻ ሳይሆን የዝሙት ሱሰኞችንም ይጨምራል ሁላችሁም ሼርርርርርር : አድርጉ !!!

ዝሙት የሚሰራውን ብቻ ሳይሆን በዝሙት ሀሳብና ፍትዎት የታመምነውንም ይጨምራል ይህ ትምህርት ለእገሌ ነበር ሳይሆን ለኔ ነው ብለን ልናነበው ይገባል ለሁላችንም ይሆን ዘንድ ከኔ የበረታችሁ አስቡኝ በጸሎታችሁ

ከ10 አንዱ ሊማርበት ስለሚችል ሸር አድርጉት

በጾም ወራት ባለትዳሮች ከግብረ-ስጋ ግንኙነት እንዲታቀቡ ቤተክርስትያን የምትመክረው

#መጽሐፍ_ቅዱሳዊ_ነውን?

፠ ከባለትዳር ወዳጄ ለተጠየኩት ፠
በቤተክርስትያችን ትምህርት ሰው ለአቅመ አዳም እና ለአቅመ ሔዋን ከደረሰ በኋላ ሕይወቱን የሚመራበት ሁለት አይነት ምርጫ አለው፤ ጋብቻ ወይም ምንኩስና።

❖ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለምንኩስና እንዲህ ብሎ ነበር።
#መነኩሴ ፡- ማለት መናኝ ፣ ብቻውን የሚኖር ፣ሴት የማያውቅ ድንግል፣ የገዳም ሰው፣ ባተሌ፣ ከዓለም ከሕዝብ ከገንዘብ የተለየ ማለት ነው /አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መዝገበ ቃላት እና
ምንኩስና በኢትዮጵያ ላይ እንደተገለጠው/፡፡

#ምንኩስና- ለሴትም ለወንድም ይሰራል፤ ዓላማው በትዳር አሳብ ሳይጠላለፉ በሙሉ ጊዜ ፈጣሪን የማገልገያ መንገድ ነው፡፡
በአንድ ወቅት ጌታ ስለ ጋብቻ ሕግ ባስተማረ ጊዜ ደቀ መዛሙርቱ ‹‹የባልና የሚስት ሥርዓት እንዲህ ከሆነ መጋባት አይጠቅምም ›› ሲሉት እንዲህ ብሎ ዘርዝሮ ነገራቸው።

ከሴት ርቆ ከወንድ ርቆ ንጽህናን ጠብቆ መኖር ስጦታ ነው እንጂ ሁሉ የሚችለው
አይደለም ሲል ‹‹ይህ ነገር ለተሰጣቸው ነው እንጂ ለሁሉ አይደለም›› አለ። ማቴ 19፡11፡፡
ቀጠለና ቁጥር 12 ላይ ‹‹በእናት ማኅፀን ጃንደረቦች ሆነው የተወለዱ አሉ፥ ሰውም
የሰለባቸው ጃንደረቦች አሉ፥ ስለ መንግሥተ ሰማያትም ራሳቸውን የሰለቡ ጃንደረቦች አሉ። ሊቀበለው የሚችል ይቀበለው አላቸው።›› አለ፡፡

ይሄ የጌታ ንግግር የሚያረጋግጠው .. ሶስት ነገሮችን ነው። ደግሞም ብልቶቻቸውን ለግብረስጋ ግኑኝነት የማይጠቀሙበት ሰዎች አሉ ማለት ነው። በነገራችን ላይ ጃንደረባ ማለት ብልቱ የተቆረጠ ማለት ነውና፡፡

1. የመጀመሪያዎቹ በጌታ አገላለጽ በእናት ማኅፀን ጃንደረቦች ሆነው የሚወለዱ ያላቸው ፦
አካል ሳይኖራቸው የሚወለዱ ወይም አካሉ ቢኖርም ተፈጥሮአዊ ሙቀት ሳይኖራቸው የሚወለዱት ናቸው።

2. ሁለተኛዎቹ ደግሞ ሰው የሰለባቸው ጃንደረቦች ናቸው / ይሄ በአንዳንድ የአገራችን ክፍሎች በጎሳዎች መካከል ሲጣሉ እና ለጋብቻ ማጫ እንደሚሰልቡ የሚታወቁ ቦታዎች አሉ… የሚገርመው ነገር እነሱ በጉዳዩ ሊጠቀሙ የሌላውን መጠቀሚያ አካል ቆርጦ ማጫ
ማቅረብ… ምን ያህል… ኢ ፍታዊነት እንደሆነ መረዳት ይቻላል፡፡

3. በጌታ አነጋገር ሶስተኛው አይነት ጃንደረባነት ‹‹ስለ መንግሥተ ሰማያትም
ራሳቸውን የሰለቡ ጃንደረቦች አሉ›› ያላቸው ሲሆኑ... ይሄም ምንኩስና ነው፤ ለመንግስተ ሰማያት ተብሎ ከጾታ ግኑኝነት ራስን ማራቅ ማለት ነው።

❖ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ሰለምንኩስና ምን አለ?
1ኛ ቆሮ 7፡17 ቅዱስ ጳውሎስ "እንዳያገቡ አወዳለው" ማለቱ ሲሆን ነገር ግን ‹‹ነገር ግን እያንዳንዱ ከእግዚአብሔር ለራሱ የጸጋ ስጦታ አለው፥ አንዱ እንደዚህ ሁለተኛውም
እንደዚያ።>> በማለት ሁሉ ተመሳሳይ ጸጋ እንደሌለው አረጋግጧል…አንዱ እንደዚህ /አያገባም/ ሁለተኛው እንደዚያ ሲል ደግሞ /ያገባል/ ማለት ነው፡፡

ልክ ጌታ በማቴ 19 ፡12 ‹‹ ሊቀበለው የሚችል ይቀበለው ›› እንዳለ ሊቀበለው የሚችል ሁሉ አይደለም፡፡

ቅዱስ ጳውሎስ ዘርዘር ሲያደርገው፦
1ኛ ቆሮ 7፡32 ‹‹ነገር ግን ያለ አሳብ ልትኖሩ እወዳለሁ። ያላገባው ጌታን እንዴት ደስ እንዲያሰኘው የጌታን ነገር ያስባል፤ ያገባው ግን ሚስቱን እንዴት ደስ እንዲያሰኛት የዓለምን ነገር ያስባል፥ ልቡም ተከፍሎአል። በአገባብ እንድትኖሩ ሳትባክኑም በጌታ እንድትጸኑ ነው›› ስለሆነም ቅዱስ ጳውሎስ በአጠቃላይ መልዕክቱ ልባቹ እንዳይከፈል ከቻላችሁ አታግቡ ብሎ መክሯል … በመጨረሻው ንግግሩም ‹‹ድንግልን ያገባ መልካም አደረገ ያላገባም የተሻለ አደረገ።›› በማለት ድንግልን ማግባት መልካም ቢሆንም የተሻለው ግን አለማግባት ነው፡፡

ስለዚህ ነገር አንድ የቤ/ክ ሊቅ እንዲህ ብለው ነበር ጳውሎስ ጋብቻን ክቡር ነው ቢልም እርሱ አላገባምና ይ ብልጠቱን ተመልከቱ ብለው ነበር፡፡
እንግዲህ ይሄን የቅዱስ ጳውሎስ ብልጠቱን ማየት /አለማግባት/ ሳይቻለን ቀርቶ ጸጋችን ጋብቻ መሆኑን አውቀን ለማግባት ከመረጥን ደግሞ ቅድመ ጋብቻ ወሲብ እንደማይገባ አውቀን የምንጋባው በድንግልና ነው፡፡ ‹‹ዳሩ ግን ማግባት ወደሚገባው ዕድሜ በደረሰ ጊዜ ስለ ድንግልናው ያፈረ ሰው ቢኖር፥ የወደደውን ያድርግ፤ ኃጢአት የለበትም፤ ይጋቡ።›› 1ኛ ቆሮ7፡36፡፡

ስለድንግልናው ያፈረ ሰው ቢኖር ማለት…. ቆሞ ቀረ ተባልኩ ብሎ ያፈረ ሰው ቢኖር… ያግባ ነው የሚለው… ድንግል ሆኖ በመኖሩ ያፈረ ሰው ድንግልናውን በጋብቻ ብቻ ነው የሚያጣው ማለት ሲሆን ይሄም የቅዱስ ጳውሎስ ቃል ሰው ድንግልናውን ጠብቆ እስከጋብቻ መጽናት እንዳለበት ያረጋግጣል… ‹‹ድንግልን ያገባ መልካም አደረገ ›› 1ኛ ቆሮ7 ፡38፡፡ የሚለው ቃል መጋባት በድንግልና መሆኑን ያረጋግጣል፡፡

አረ ቅዱስ ጳውሎስ እንደዚህም ብሏል ‹‹ከዝሙት እንድትርቁ፥ እግዚአብሔርን እንደማያውቁ አሕዛብ በፍትወት ምኞት አይደለም እንጂ፥ ከእናንተ እያንዳንዱ የራሱን ዕቃ በቅድስናና በክብር ያገኝ ዘንድ እንዲያውቅ፤>> 1ኛተሰ 4፡5፡፡

አንድ መተርጉም ቅዱስ ጳውሎስ "የራስን ዕቃ በክብር ማግኘት" ያለው .. የሚገኝ የራስህ የሆነ የትዳር አጋርህን አካል ነው…. እሱም ያንተ የሆነ ንብረት ነው…. ግን በቅድስና እና በክብር ያገኝ ዘንድ የተባለው ደግሞ በህጋዊ ትዳር በሰርግ ደስታ…. በጋብቻ ስርዓት ተቀበለው ሲል ነው ብሎ ተርጉሞታል… ይሄን የሰማች አንድ እህት በወቅቱ …. እኔማ… ‹‹ብር አምባር ሳላሰኝ›› ሞቼ ነው ብላ ፎክራ ነበር… እኛም ይበል ብለን አልፈነዋል…
እንዲህ አይነቱን አቋም እናበረታታለን…እስካሁን ጉዳዩ ተጠብቆ ካለ… እንዲው አልሆነ ቦታም ከወደቀም… ድጋሚ አይነሳምና ከተክሊል ርቆ በመዓስባን ጋብቻ ለመጋባት የነፍስን ድንግልና በንስሐ መመለስ ነው፡፡

#ይቀጥላል
በቀጣይ ክፍል በጋብቻ ወስጥ ግብረ ስጋ ግኑኝነት በመጽሐፍ ቅዱስ እንዴት ይገለጻል ??

@ortodoxmezmur
@ortodoxmezmur
@ortodoxmezmur
12.7K views11:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-13 08:22:12 ቅዱስ

ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ ኢየሱስ ክርስቶስ
ኃያል ኃያል ኃያል አማኑኤል

አስቀድሞ የነበረ አሳልፎ የሚኖር
በሥልጣኑ ያጠፋልን ሙስና መቃብር
ከአባቱ ጋር ትክክል ነው በኃይል በጌትነት
በዓለም ሊፈርድ የሚመጣው በክብር በትስብእት

ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እግዚአብሔር
ኃያል ኃያል ኃያል አማኑኤል

የሰው ፍቅር አገብሮት ወደ ምድር የመጣ
ከሰማያት የወረደው ወደ ሰማይ የወጣ
ከምስጉኖች ይልቅ ምስጉን ከግሩማን ግሩም
የጠቢባን ጠቢብ ጌታ የሚመስልህ የለም

ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እግዚአብሔር
ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ አማኑኤል

ብንዳስሰው ብንበላው ደግሞም ብንጠጣው
ረቂቁ የገዘፈው ሥጋን ተዋሕዶ ነው
በደመናት መጋረጃ የተሰወረ እሳት
በግርግም ውስጥ አገኘነው በግዕዘ ሕፃናት

ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ ኢየሱስ ክርስቶስ
ኃያል ኃያል ኃያል አማኑኤል

ሰማያትን የዘረጋ ውኆችን የፈጠረ
የማይታይ የሚታየው በእርሱ ተፈጠረ
ሁሉን በእጁ የጨበጠ አሸናፊው ልዑል
በቤተልሔም ተወለደ ከማርያም ድንግል

ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እግዚአብሔር
ኃያል ኃያል ኃያል አማኑኤል

ዘማሪ መምህር አቤል ተስፋዬ
@ortodoxmezmur
@ortodoxmezmur
@ortodoxmezmur
12.8K views05:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ