Get Mystery Box with random crypto!

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

የቴሌግራም ቻናል አርማ ortodoxmezmur — ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit
የቴሌግራም ቻናል አርማ ortodoxmezmur — ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit
የሰርጥ አድራሻ: @ortodoxmezmur
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 136.56K
የሰርጥ መግለጫ

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ
አምላክ አሜን።
. ዝማሬ ዳዊት
የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ ትምህርቶች, መዝሙራት እና ወረባትን ከነዜማቸው ለማግኘት ቻናላችንን ይጎብኙ።
ለማንኛውም ሀሣብ, ጥቆማ, አስተያየት
@zmaredawit_messengerbot ላይ
ቢያስቀምጡልን ይደርሰናል

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 35

2023-02-10 19:14:29 እግድ ተሰጠ ማለትም ክስ ቆመ ማለት እንዳልሆነ ያስታወሰው ኮሚቴው የምንጠይቃቸው የወንጀልና የሰብአዊ መብት ጥሰቶች ይቀጥላሉ ብሏል።

የፌደራል ፖሊስ ፣ የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት፣ የኦሮሚያ ፖሊስና ሰላም ሚኒስቴር እግዱን እንዲያስፈጽሙ ኃላፊነት የተጣለባቸው ተቋማት ናቸው።
13.9K views16:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-10 19:14:29
በሕገ ወጡ ሹመት ላይ የተሳተፉ የቀድሞ ሊቃነ ጳጳሳትና ግለሰቦች ከዛሬ የካቲት 3 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አብያተ ክርስቲያናት እንዳይገቡ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አግዷል።

ዛሬ በነበረው የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቀጠሮ የሕግ አማካሪዎች መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ በዚህም ሹመት የሰጡት በቀድሞ ስማቸው “አባ ኤዎስጣቴዎስ”፣ “አባ ዜና ማርቆስ”፣ “አባ ሳዊሮስ” እና እነርሱ በሕገ ወጥ መልኩ ሾመናችኋል ብለው ከሕገ ቤተ ክርስቲያን ውጪ አስኬማ ያቀዳጇቸው 25 ግለሰቦች እንዲሁም አቶ ኃይለ ሚካኤል ታደሰ የተባሉ ግለሰብ በፍትሐ ብሔር ሕግ ቁጥር 156 መሠረት በኢትዮጵያ ውስጥ በሚገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ግቢ እንዳይገኙ በጊዜያዊነት አግዷቸዋል። ይህንን እግድ የተላለፈ ማንኛውም አካል የወንጀል ተጠያቂነት ይኖርበታል። በሀገሪቱ የሚገኙ የሕግ አስፈጻሚ አካላት እግዱን እንዲያስፈጽሙ ትዕዛዝ ተሰጥቷል። ቤተ ክርስቲያኗ በቀጣይ በሰብአዊ መብት፣ በአስተዳደር፣ በወንጀልና በፍትሐ ብሔር ለደረሰው ኪሣራ ተጠያቂዎችን በመለየት በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ መሠረት በሕግ ትጠይቃለች።

በዚህም በሕገ ወጡ ሹመት ላይ የተሳተፉ የቀድሞ ሊቃነ ጳጳሳትና ግለሰቦች ከዛሬ የካቲት 3 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አብያተ ክርስቲያናት እንዳይገቡ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አግዷል።
14.4K views16:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-10 19:12:45
"በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ መሪነት በፍፁም መንፈሳዊ መሪነትና ክብር ሄደናል፤ እግዚአብሔር ሰምቶናል፤ ከጠቅላይ ሚኒስትሩም ለጥያቄዎቻችን መልስ ተሰጥቶናል::" ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ

ዛሬ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር የነበረውን ውይይት አስመልክቶ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ እና የኒዮርክ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ መግለጫ ተሰጥቷል፡፡

በመግለጫውም ብፁዕነታቸው እንደገለጹት ትናንት በሰጠነው መግለጫ “በአስቀመጥነው ቅድመ ሁኔታ መሠረት በጠቅላይ ሚኒስትሩ ተጠርተን ጥያቄያችንን አቅርበናል፡፡ ጥያቄያችንም አንድ ነው ሕገ ቤተ ክርስቲያን ይከበር፤ በሀገሪቱ ያለው ኦርቶዶክሳውያን መብት ይጠበቅ፤ የቤተ ክርስቲያኒቱ ሀብትና ንብረት በሀገሪቱ ሕግ መሠረት ንብረቷ ይጠበቅ፤ እነዚህ ካልሆኑ ወደ ሰላማዊ ሰልፍ እንሄዳለን ማለታችን ይታወሳል፡፡ በዚህም በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ መሪነት በፍፁም መንፈሳዊ መሪነትና ክብር ሄደናል ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር በነበረን ቆይታ በደንብ ተወያይተንበት ለጥያቄዎቻችንም መልስ ተሰጥቶናል ብለዋል ብፁዕነታቸው፡፡ እንዲሁም ዝርዝር መግለጫውን ነገ የምንሰጥ ይሆናል ብለዋል፡፡
12.1K views16:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-10 15:15:55
አባቶቻችን
1.3K viewsedited  12:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-10 14:07:58
#ሰበር_መረጃ

ቅዱስ ፓትርያርኩን ጨምሮ ብፁዓን አባቶች ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር ውይይት እያካሔዱ ይገኛሉ።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጠቅላይ ቤተ ክህነት ሕዝብ ግንኙነት አስቸኳይ ሰበር መግለጫ ሰጥቷል።

በመግለጫው ፤ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በየካቲት 2 ቀን 2015 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ መሠረት ቤተ ክርስቲያኒቱ መግለጫውን ባወጣች 72 ሰዓታት ውስጥ የቤተ ክርስቲያኒቱን ሃይማኖት ፤ ቀኖናና አስተዳደራዊ ሕግጋትን ባልጣሰ መልኩ ከመንግሥት ጋር በጉዳዩ ላይ ለመወያየት መንፈሳዊ በሯ ክፍት መሆኑን በመግለጽ ይፋዊ ጥሪ ማስተላለፏን አስታውሷል።

ከዚህ ጋር በተያያዘ የኢፌዳሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ይህንን የቤተ ክርስቲያን ጥሪ መሠረት በማድረግ ለውይይት ጥሪ ማቅረባቸውን ገልጿል።

ውይይቱ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ግቢ ሊሆን የሚገባ ነው በሚል በተነሳው ሐሳብ በጉዳዩ ላይ ከሽማግሌዎች ጋር ጥልቅ ውይይት በማድረግ የደህንነት ተሽከርካሪዎች እና የጸጥታ አካላት ብዛት ሲታይ ምእመናንን ስጋት ላይ እንዳይወድቁ እና ላልተጋባ ጉዳት እንዳይዳረጉ በማሰብ የሰላም ጥሪውን መንግሥት ከተቀበለ እና በቤተ መንግሥት መገኘቱ ለሕዝቡ የሚያመጣው መፍትሔ የሚኖር እንደሆነ በማሰብ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርካችንን ጨምሮ አበው ሊቃነ ጳጳሳትን ያካተተ ልኡክ በቤተ መንግሥት የሚገኝ መሆኑን ጠቅላይ ቤተ ክህነት አሳውቋል።

ሕዝበ ክርስቲያኑም አባቶች የደረሱበትን ውጤት እስኪያሳውቁ ድረስ በትእግስት እንዲጠባበቁ መልእክት አስተላልፏል።
5.3K viewsedited  11:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-10 12:14:29
"የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕመም ሕመማችን ክብሯ ክብራችን ነው::" የሮም ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን

የሮም ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን የአጋርነት ደብዳቤ በፖፑ የክርስቲያን አንድነት ፕሬዝደንት በኩል ላከች::

ብፁዕ ካርዲናል ኩርት ኮህ የፖፕ ፍራንሲስ የክርስቲያኖች አንድነት ፕሬዝዳንት (President Pontifical Council for Prompting Christian Unity) እንደገለጹት "በተፈጠረው ችግር እና ሁኔታ ጥልቅ ሐዘን የተሰማን ሲሆን ለቅዱስ ሲኖዶስ ያለንን አጋርነት በመግለጽ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን አንድነት ለመጠበቅ የሚደረግ ጥረትን በሙሉ እንደግፋለን" ብለዋል::

በመልእክታቸው ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ለቆሮንጦስ በላከው የመጀመሪያ መልእክት “አንድም ብልት ቢሰቃይ ብልቶች ሁሉ ከእርሱ ጋር ይሣቀያሉ፤ አንድ ብልትም ቢከበር ብልቶች ሁሉ ከእርሱ ጋር ደስ ይላቸዋል።” 1ኛ ቆሮንጦስ 12፥26 ያለውን ጠቅሰው ሕመሟ ሕመማችን ክብሯ ክብራችን ነው ሲሉ በአጽንዖት ገልጸዋል።

በመጨረሻም እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ወላዲተ አምላክ እና የቤተ ክርስቲያን አንድነት እናት በምልጃዋ እጅግ የተከበረች የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አንድነቷና ደህንነቷ እንዲጠበቅ ታድርግልን ብለዋል።
7.6K views09:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-10 12:14:13
የእሥር ዜና!

የኢትዮጽያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ወጣቶችና ጎልማሶች ማኅበራት ኅብረት ዋና ሰብሳቢ ወ/ሪት ፌቨን ዘሪሁን እንዲሁም ዋና ፀሐፊዋ ወጣት ብሩክታዊት ታሥረዋል።

ምንጭ፡ ተሚማ
6.9K views09:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-10 10:24:46
ዛሬ ጠዋት የማኅበረ ቅዱሳን ደቡብ ማእከላት ማስተባበሪያ አስተባባሪ የሆነውን ዲ/ን መልካሙ ጸጋዬ ማንነታቸው ባልታወቁ አካላት ታፍነው ተወስደዋል።
9.0K views07:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-10 10:07:16
የአርባ ምንጭ ከተማ አስተዳደርና የከተማው የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ጎን መሆናቸውን አሳወቁ።

የጋሞ ዞንና የአርባ ምንጭ ከተማ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ በወቅታዊ ጉዳዮችና የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔን  የሚደግፍ ምክክር አካሒደዋል።

የጋሞ ዞንና የአርባ ምንጭ ከተማ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ በወቅታዊ ጉዳዮችና የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔን አስመልክቶ በትናንትናው ዕለት ባደረጉት ምክክር  በከተማው የሚገኙ የእስልምና እምነት ተከታዮችና  የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ኅብረት የሃይማኖት ተወካዮች በኢትዮጵያ  ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ በደረሰው ክስተት ማዘናቸውን ገልጸዋል።

ቤተ ክርስቲያን ወደ ቀድሞው ሰላም እስክትመለስ ድረስ ሁሉም ቤተ እምነቶችና ምእመናን  በጾምና በጸሎት ከኢትዮጵያ  ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጎን እንደሚሆኑ  አሳውቀዋል።

ከተማ አስተዳደሩም ቅዱስ ሲኖዶሱ በሚያስቀምጠው አቅጣጫ መሠረት የሚጠይቁት ጥያቄ  እስኪመለስ ድረስ በማንኛውም ነገር  ከኢትዮጵያ  ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጎን መሆኑን አሳውቋል።

በመሆኑም ኅብረተሰቡ እንደ ከዚህ ቀደሙ የሰላም ማስከበር ሥራውን አጠናክሮ በማስቀጠል  እንግዳ እና አጠራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥሙት ጥቆማ በመስጠት ከጸጥታ አካላት ጎን በመሆን የተለመደ ተግባሩን ሊያከናውን እንደሚገባም ተገልጿል። ዘገባው የአርባ ምንጭ ከተማ ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው።
8.7K views07:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-10 09:29:41 የተወደዳችሁ የዝማሬ ዳዊት ተከታታዮች።

የእሑዱ ሠላማዊ ሰልፍ የማይቀርበት ነው ስለዚህ ሁላችሁም ሀሞታችሁን ዋጥ አድርጋችሁ አንድ ላይ እንውጣ እና ለቤተክርስቲያን የከበርን ሙሽሪቶች እንሁን።

ግን ጥልቅ ማሳሰቢያ ንስሐ ያልገባን ካለን እባካችሁ ዛሬ እና ነገ ወደ ንስሐ አባቶቻችን በመሄድ ንስሐ እንግባ።

የንስሐ አባትም ያልያዝን ወደ ቤተክርስቲያን ሄደን አባት እንያዝ እና ንስሐ እንግባ።


ሰማዕትም ብንሆን ንስሐ ገብተን ነው መሆን ያለበት። የሰማይ ቤታችንን በክብር እንድንገባበት
9.5K views06:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ