2022-09-03 22:16:22
#የደረጃ_ሰንጠረዥ_ትንተና
ክለባችን ማንችስተር ዩናይትድ ነገ ከአርሰናል ጋር በጣም አስፈላጊ የሆነ እና ሶስት ነጥብ መውሰድ ያለበት ጨዋታን በታላቋ ኦልድትራፎርድ ስታዲየም ያደርጋል።
ነገ የሚደረገውን ጨዋታ ብናሸንፍ፣ ብንሸነፍ ወይም አቻ ብንወጣ በደረጃ ሰንጠረዡ የሚኖረን ሁኔታ ይህን ይመስላል:-
የነገውን ጨዋታ ካሸነፍን የደረጃ ሰንጠረዡ እንዴት ይሆናል?
የነገውን ጨዋታ የምናሸንፍ ከሆነ ከአርሰናል 3 ነጥብ ልዩነት፣ በሲቲ እና ቶተንሃም 2 ነጥብ ልዩነት ርቀን በደረጃ ሰንጠረዡ አራተኛ ደረጃ ላይ መቀመጥ የምንችል ሲሆን ነገርግን ይህ የሚሆነው ብራይተን ነገ ከሌስተር ጋር የሚያደርገውን ጨዋታ የሚሸነፍ ከሆነ ብቻ ነው!
ብራይተን የነገውን ጨዋታ አሸንፎ ሶስት ነጥብ የሚያገኝ ከሆነ ግን በቶፕ 4 የሚቀጥል ሲሆን እኛም አሸንፈን ሶስት ነጥብ ብናገኝ እንኳን ከቶፕ 4 ክልል ወጥተን በአምስተኛ ደረጃ ላይ ነው የምንቀመጠው።
የነገውን ጨዋታ አቻ ብንወጣስ?
የነገውን ጨዋታ አቻ የምንወጣ ከሆነም ከቼልሲ ጋር እኩል ነጥብ ኖሮን በጎል ክፍያ ተበልጠን ስድስተኛ ደረጃ ላይ የምንቀመጥ ይሆናል፤ ይህ ግን ከሌሎች በደረጃ ሰንጠረዡ ተፎካካሪ ክለቦች ጋር በዝቅተኛ ነጥብ ልዩነት ነው የሚሆነው።
አቻ ከወጣን እና ብራይተን ከሌስተር ጋር የሚያደርገውን ጨዋታ የሚያሸንፍ ከሆነ ከኋላቸው ሆነን ስድስተኛ ደረጃ ላይ ነው የምንቀመጠው። ነገርግን የነገ ጨዋታቸውን የሚሸነፉ ከሆነ እና እኛ አቻ ከወጣን እኩል ነጥብ ኖሮን በጎል ክፍያ ተበልጠን ስድስተኛ ደረጃ ላይ ነው የምንቀመጠው።
የነገውን ጨዋታ ብንሸነፍስ?
የነገውን ጨዋታ ከተሸነፈን እንኳን እዛው 8ኛ ደረጃ ላይ መቀመጣችንን እንቀጥላለን።
ድል ያለ ድል ለታላቁ ማንችስተር ዩናይትድ ይሁን
አቡኪ
@man_united_ethio_fans
@man_united_ethio_fans
12.6K views𝐊𝐀𝐑𝐄𝐄𝐌 𝐀𝐁𝐔𝐊𝐈 , 19:16