2022-09-03 18:20:55
MATCH DAY PRESS CONFRENCE !
በተወዳጁ የእንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ ስድስተኛ ሳምንት መርሃግብር ምሽት 12:30 በውቧ ኦልትራፎርድ ማንችስተር ዩናይትድ አርሰናልን ያስተናግዳል እንደተለመደውም ኤሪክ ቴን ሀግ ከእዚህ ተጠባቂ ፍልሚያ በፊት ጋዜጣዊ መግለጫን ሰጥተዋል።
ኤሪክ ስለ ተጫዋቾች ጉዳት እና ከጉዳት መመለስ ሁኔታ
"ስለ ሉክ ሾው እና አሮን ሳወራ ለመናገር አስቸጋሪ ነው። ነገር ግን አንቶኒ ማርሻል ከአርሰናል ጋር በሚኖረው ጨዋታ አይሳተፍም።
“አንቶኒ መቼ እንደሚመለስ በአሁኑ ጊዜ መናገር አልችልም።
ኤሪክ ስለ ተጋጣሚያችን አርሰናል
"እኔ አርሰናልን አይቻለሁ እናም ጠንካራ ተጋጣሚያችን ነው የውድድር አመቱን ሁላችንም እንደምናውቀው በጥሩ ሁኔታ እነሱ ጀምረዋል እናም አብረው ረጅም ጊዜ የቆየ ቡድን የእሱን ፍልስፍና የሚተገብር አሰልጣኝ ነው ያላቸው።
"ስለዚህ ይህ ጥሩ ፈተና ነው ከአርሰናል ጋር የሚኖር ጨዋታ እናም በጉጉት እጠብቀዋለን ለጨዋታውም ትክክለኛውን ቋሚ 11 እንመርጣለን ግን እንደምታዩት ተጫዋቾች ብቻ ሳይሆን ሙሉ ቡድን አለን እንዲሁም ዛሬ ሀሙስ የገቡት ተጫዋቾች ጥሩ አድርገዋል።
ኤሪክ ስለ ቡድኑ ጥሩ እንቅስቃሴ
"ስለ መስርቶ መጫወት ፣ መስመሮችን ስለማግኘት እና እድሎችን ስለመፍጠር እና ከዚያም ትክክለኛ ውሳኔዎችን ስለ ማድረግ ይመስለኛል። በተጨማሪም በኳስ ጋር የሚኖሩ እንቅስቃሴዎች ትንሽ ይቀሩናል ነገር ግን ከኳስ ውጭ ጥሩ እርምጃ እየወሰድን ነው ፣ መሠረት አለን ግን አሁንም ብዙ መሻሻሎች የሚያስፈልጋቸው ነገሮች አሉ።
ኤሪክ ስለ ተከላካይ መስመሩ
“በአጠቃላይ ቡድኑን በሙሉ ሲከላከል ነው የማየው ይህም ለተከላካዮቻችን ነገሮችን ቀላል ያደርገዋል። እኔ ግን ጥሩ የሚሠሩት ተባብረው አብረው በመስራታቸው እና እርስ በእርስ በመደጋገፋቸው ጥሩ አፈጻጸም ያላቸው ይመስለኛል።
"አሁን በሜዳው ላይ የምንመለከተው ለተፋላሚያችን የግብ እድሎችን መፍጠር ከባድ ማድረግን ነው አሁን የምናየው ያን ነው።
ኤሪክ ቴን ሀግ ስለ አንቶኒ
“ሀሙስ ዕለት የመጀመሪያ ልምምዱን ሰርቷል ይህም ልምምድ ለብቻው ያደረገው ነው አርብ እና ቅዳሜ የቡድን ስልጠና አለን በእዚህ ላይ ይሳተፋል ከእዚህ በኃላ በአርሰናሉ ጨዋታ በመሳተፉ ዙሪያ ውሳኔ የምንወስን ይሆናል።
ኤሪክ ከጨዋታው አስቀድሞ የሰጡት ሙሉ ጋዜጣዊ መግለጫ ይህንን ይመስላል አና እንዲህ አቀረብኩላቹሁ መልካም ምሽት ዩናይትዳዊያን።
@Starboyana
@man_united_ethio_fans
30.7K views Błąçķ ÃŇĀ, 15:20