Get Mystery Box with random crypto!

أبو سعيد

የቴሌግራም ቻናል አርማ abuseidibnuhussen — أبو سعيد أ
የቴሌግራም ቻናል አርማ abuseidibnuhussen — أبو سعيد
የሰርጥ አድራሻ: @abuseidibnuhussen
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 320
የሰርጥ መግለጫ

በዚህ ቴሌግራም ቻናል የተለያዩ ኢስላማዊ አስተምህሮቶች ቁርኣን እና ሐዲሥን እንዲሁም የደጋግ ቀደምቶችን ፈለግ መሰረት ባደረገ በፅሁፍ ለሙስሊሙ ማህበረሰብ ይቀርብበታል።
📝አቡ ሰዒድ (ዐብዱረሒም ሑሴን)

Ratings & Reviews

1.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-07-08 20:11:01 تقبل الله منا ومنكم صالح الأعمال
103 viewsأبو سعيد, 17:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-04 15:20:44 በአስርቱ ከዱንያ በላጭ በሆኑት ቀናት ውስጥ እንገኛለን። በእነዚህም ቀናት ውስጥ የሚፈፀም ማንኛውም ኸይር ሥራ በየትኛውም ጊዜ ከሚተገበር ኸይር ሥራ እንደሚልቅ ማስረጃዎች ይጠቁማሉ። ታዲያስ እንዴት እያሳለፍናቸው ይሆን?!

አቡ ሰዒድ (ዐብዱረሒም ሑሴን)
https://t.me/abuseidibnuhussen
235 viewsأبو سعيد, 12:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-03 14:35:20 በጁሙዓ እለት አንዲት ሰዓት አለች ዱዓ ተቀባይነት የሚያገኝባት። ከዐስር ሰሏት በኋላ እንደሆነች ብዙዎች ይናገራሉና ባንሳነፍ ባይ ነኝ።

አቡ ሰዒድ (ዐብዱረሒም ሑሴን)
https://t.me/abuseidibnuhussen
350 viewsأبو سعيد, edited  11:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-19 15:44:19 ☞ የሌላውን እምነት የማንሰድብበትና የማናቋሽሽበት መርኁም ምክንያቱም ይኸው፦

«እነዚያንም ከአላህ ሌላ የሚገዙዋቸውን (ጣዖታትን) አትስደቡ። ድንበርን በማለፍ ያለዕውቀት አላህን ይሰድባሉና።»
[አል-አንዓም፥108]

አልሐምዱሊሏህ ሙስሊም ላደረገኝ

አቡ ሰዒድ (ዐብዱረሒም ሑሴን)
https://t.me/abuseidibnuhussen
425 viewsأبو سعيد, edited  12:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-17 15:21:14
376 viewsأبو سعيد, 12:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-01 18:49:25 تقبل الله منا ومنكم صالح الأعمال
650 viewsأبو سعيد, 15:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-01 10:31:33 ☞ የረመዷን ስንብት……!!
~
ከቀናት በፊት የረመዷንን መምጣት በጉጉት ስንጠባበቅ የነበርን ሰዎች ዛሬ ከመቅፅበት የመጨረሻ ቀን ላይ እንገኛለን። «የተቆጠሩ ቀናቶች…» የሚለው የጌታችን ቃል ምንኛ ያማረ አገላለፅ ነው! አዚህ ገር ቆም ብለን እራሳችንን መጠየቅ ይጠበቅብናል። ባሳለፍናቸው ቀናት ምን ያህል ጊዜ ቁርኣንን አኸተምን?፣ ዚክር ላይ እንዴት ነበርን?፣ የሌሊት ሰሏትሳ?፣ የፆመኛ ዱዓእ ተቀባይነት አለው። ታዲያ ችግራችንን ለአሏህ አድርሰናል?፣ ፆመኛን አስፈጥረናል?፣ የታረዘን አልብሰናል?፣ የተራበን መግበናል?… ሌላም ሌላም መልካም ሥራ ላይ ተሰማርተናል? ለእነዚህ ጥያቄዎች መልሳችን "አዎ" ከሆነ አሏህን እናመስግን። "አይ" ከሆነ ግን ነፍሳችንን አርመን ዛሬን እንጠቀም። ካልሆነ ግን የተቀሩት ጥቂት ሰዓታት ያልፉናል። ምክንያቱም በረመዷን አንድ ቀን ማግኘት ታላቅ ዕድል ነውና እንጠቀምበት። በነገራችን ላይ ቀናቶች እየነጎዱ እድሜያችን እየተገባደደ እለተ-ቂያማ ከፊታችን በፍጥነት ወደኛ እየገሰገሰ መሆኑን ማስተዋል ያሻናል።

«...ﻭَﻣَﺂ ﺃَﻣْﺮُ ﭐﻟﺴَّﺎﻋَﺔِ ﺇِﻟَّﺎ ﻛَﻠَﻤْﺢِ ﭐﻟْﺒَﺼَﺮِ ﺃَﻭْ ﻫُﻮَ ﺃَﻗْﺮَﺏ...»
[النحل؛ ،٧٧]
«የሰዓቲቱ (መምጣት) እንደ ዓይን ቅፅበት እንጂ አይደለም። ወይ እርሱ ይበልጥ የቀረበ ነው።…» [አንነሕል ፥77]

አዎ ያለፈ ነገር እንጂ መጪ ነገር ሁሉ ቅርብ ነው። ከረመዷን ሂደት ይህንን መረዳት ይቻላል። ያለፉት የረመዷን ቀናት ላይመለሱ አምልጠዋል። የተጠቀመባቸው አሏህን ያመስግን፤ የተሳነፈባቸው ነፍሱን እንጂ ማንንም መውቀስ አይችልም። ባይሆን የዛሬውን ቀን ከልብ መጠቀም ብልህነት ነው። የዛሬው ቀን ከብዙ እይታ አንፃር ካለፉት ይበልጥ ውድ ነው።

~ አንደኛ፦ የረመዷን ማብቂያና ማጠናቀቂያ በመሆኑ በዚህ ቀን ሥራን ማሳመር ፍፃሜን እንደማሳመር ይታሰባል። የሥራ ማማር የሚመዘነውም አጨራረሱ ላይ ነው። መልዕክተኛችንምﷺ እንደሚከተለው ገልፀዋል፦
«ﺇﻧَّﻤﺎ ﺍﻷﻋﻤﺎﻝُ ﺑﺎﻟﺨﻮﺍﺗﻴﻢِ‏»
«ሥራ (የሚለካው) በፍፃሜው ነው።» ስለሆነም በዛሬው ቀናችን አጨራረሳችንን ለማሳመር መትጋት አማራጭ የሌለው መፍትሔ ነው።

~ ወንጀሉ የሚማረው በመጨረሻው ሌሊት ነው።
«… ﻭﻳﻐﻔﺮ ﻟﻬﻢ ﻓﻲ ﺁﺧﺮ ﻟﻴﻠﺔ ‏» ﻗﻴﻞ: ﺃﻫﻲ ﻟﻴﻠﺔ ﺍﻟﻘﺪﺭ؟ ﻗﺎﻝ: ‏« ﻻ، ﻭﻟﻜﻦ ﺍﻟﻌﺎﻣﻞ ﺇﻧﻤﺎ ﻳﻮﻓﻰ ﺃﺟﺮﻩ ﺇﺫﺍ ﻗﻀﻰ ﻋﻤﻠﻪ‏»
ረሱል ﷺ «…(ለፆመኞች) በመጨረሻው ሌሊት (ወንጀላቸውን) ይምርላቸዋል» አሉ። "ይህ የሚሆነው በውሳኔይቷ ሌሊት ነውን?" ተብለው ተጠየቁ። እሳቸውም፦ «አይደለም። ይልቅ ሠራተኛ ሥራውን ሲጨርስ ነው ሙሉ ክፍያውን የሚሰጠው።» አሉ።

~ ሁለተኛ፦ የዛሬው ቀን ከመጨረሻዎቹ አስርት ቀናት አንዱ ነው። ስለዚህ ባለፉት ቀናት ሰንፈንም ከነበረ ዛሬን እንኳ አንበርታ። አጠቃቀሙን እንቻልበት። ብልህ ሰው ካለፈው ይማራል፣ ለቀጣዩ ቀበቶውን ጠበቅ ያደርጋል።

~ ለማንኛውም አሏህን በብዛት ማምለክ፣ ቁርኣን በብዛት መቅራት፣ ሌሎችም መልካም ተግባራቶች መተግበር ረመዷን ውስጥ ምንዳቸው እጥፍ ድርብ ይሁን እንጂ በሁሉም ወራትና ቀናት ታላላቅ ምንዳዎችን ያሰጣሉ። እንዲያውም እውነቱን ለመናገር ረመዷን ውስጥ ዒባዳ ላይ በብዛት በርትቶ ሲያበቃ ረመዷን ሲወጣ ግዴታዎችን እንኳን እርግፍ አድርጎ ከሚተው አካል ረመዷን ውስጥም ሆነ ውጪ ግዴታዎች ላይ የሚፀና አካል በእጅጉ የተሻለ ነው። በል አይነፃፀሩም! ስለዚህ ጽና! የ2014 ረመዷን አንተ ላይ የለውጥ አሻራውን አኑሮብህ "እኔ ዲኔ ላይ ለውጥ ያመጣሁት፣ የሰላትና መስጂድ ሰው የሆንኩት 2014 ረመዷን ላይ ነበር።" ብለህ የምትተርከው ታሪክ እንዲፈጠር አድርግ

~ ከረመዷን ጋር አብረህ ከመስጂድ እንዳትወጣ። እባክህ የሚጠቅምህን ምክር ሰምተህ ተግባራዊ አድርግ። ለፅናትህ ወሳኝነት አለው። አሏህ ይህንን በቁርኣን በአጽንኦት ገልፆታል፦
"... ﻭَﻟَﻮْ ﺃَﻧَّﻬُﻢْ ﻓَﻌَﻠُﻮﺍ ﻣَﺎ ﻳُﻮﻋَﻈُﻮﻥَ ﺑِﻪِ ﻟَﻜَﺎﻥَ ﺧَﻴْﺮًﺍ ﻟَﻬُﻢْ
ﻭَﺃَﺷَﺪَّ ﺗَﺜْﺒِﻴﺘًﺎ" [النساء؛ ٦٦]
«…እነርሱም በእርሱ የሚገሰጹበትን ነገር በሠሩ ኖሮ ለነሱ መልካምና (በእምነታቸው ላይ) ለመርጋትም በጣም የበረታ በኾነ ነበር።» [አኒ፞ሳእ፥66]

☞ አንባቢ ሆይ! አንብበህ መተግበርን ልመድ። የማንበብህ ዓላማና ዒላማ ተግባር እንጂ የማንበብ ልምድ ማዳበር ብቻ አይሁን። አሏህ እኛንም እናንተንም ፆማችንን ይቀበለን! ከረመዷንም በኋላ ፅናትን ይስጠን!
ወሏሁ አዕለም!

አቡ ሰዒድ (ዐብዱረሒም ሑሴን)
https://t.me/abuseidibnuhussen
661 viewsأبو سعيد, 07:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-28 04:53:02 ~ ዘካቱል ፊጥር ~
ክፍል አራት/ የመጨረሻው ክፍል
① ዘካቱል ፊጥር የእህሉን ዋጋ መስጠት ይቻላል???

ዘካቱል ፊጥር የእህሉን ዋጋ መስጠትን አስመልክቶ በዑለሞች መካከል ይቻላል እና አይቻልም የሚሉ አቋሞች ተንፀባርቀዋል።ነገር ግን የአብዛሃኛዎቹ ዑለሞች( የኢማሙ ማሊክ፣ሻፊዒይ፣አሕመድ....) አቋምና መረጃም የሚደግፈው አስገዳጅ ነገር እስካልተከሰተ ድረስ ዘካተል ፊጥር የእህሉን ዋጋ መስጠት አይቻልም የሚለው የዑለሞች አቋም ነው።በዚህ መሰረት ዘካችንን መስጠት ያለብን ከዚህ በፊት ያሉት ክፍሎች እንዳየነው ገንዘቡን ሳይሆን እህሉን ነው።ዘካውን የምንሰጠው ሰው ብሩን ከፈለገ ሽጦ መጠቀም ይችላል።
② ዘካውን እንዲሰጥልን ሰውን መወከል ይቻላልን???
አንድ ሰው ዘካተል ፊጥሩን መስጠት ሳይመቸው ቀርቶ ዘካውን እንዲሰጥለት ሌላ ሰውን ቢወክል ምንም ችግር የለውም።እንዲሁም ከሰዎች ዘካተል ፊጥራቸውን ተቀብለው ለሚስኪኖች የሚያከፋፍሉ ተቋሞች ወይም ማህበራት ካሉ፤እንዲሁም ታማኝና ዘካውን ለሚስኪኖች ከሶላት በፊት የሚያከፋፍሉ ከሆኑ ዘካችንን ለነሱ መስጠት እንችላለን።በተጨማሪም እነዚህ ተቋማት ወይም ማህበራት እህሉን ገዝተው የሚሰጡልን ከሆነ ለነሱ እህሉን የሚገዙበት ገንዘብ መስጠት እንችላለን።ከላይ ዋጋውን መስጠት አይቻልም የተባለው ቀጥታ ለሚስኪኑ ገንዘቡን መስጠት ነው።አሁን ግን የተፈቀደ ነው ያልነው እኛ ለተቋማቱ ገንዘቡን እንሰጣለን፤ ተቋማቱ ደሞ እህል ገዝተው ለመሳኪኖች ማከፋፈላቸውን ነው።
③ ዘካቱል ፊጥራችንን የት ነው ማውጣት ያለብን???
ዘካችንን ማውጣት ያለብን የፆምንበት ቦታ(ሀገር) ላይ ነው።ነገር ግን ይህንን ማድረግ ካልቻልን ሌላ ቦታ ላይ ያለን አካል ዘካችንን እንዲሰጥልን መወከል እንችላለን።ለምሳሌ ከቤተሰብ እርቀው የሚማሩ ተማሪዎች ከቻሉ እዛው የፆሙበት ቦታ ላይ ዘካቸውን ያወጣሉ፤ይህን ማድረግ ካልቻሉ ግን ቤተሰባቸው ቢያወጣላቸው ምንም ችግር የለውም።
④የብዙ ሰዎችን ዘካ ሰብስበን ለ አንድ ሚስኪን መስጠት እንዴት ነው????
ከአንድ በላይ የሆኑ ሰዎች ፦ ለምሳሌ የአንድ ቤተሰብን ዘካ ሰብስበን ለአንድ ሚስኪን መስጠት ምንም ችግር እንደሌለው ዑለሞች አስቀምጠዋል።ስለዚህ 3 የቤተሰብ አባላት ቢኖሩን የግድ ለተለያዩ ሶስት ሚስኪኖች መሰጠት አለበት አይባልም።

አልሓምዱሊላህ ፅሁፌን እዚህ ላይ ጨረስኩ


★ "ዘካቱል ፊጥር "~~ በሚለው ፅሁፌ
ሸርሑ አልሙምቲዕ( በሰፊው)
ተማሙ አልሚና(በተወሰነ)
አል ሙጝኒ(በስሱ)
እንደ ምንጭነት ተጠቅሚያለው የበለጠ ማጥናት የፈለገ እነዚህንና ሌሎችን ኩቱቦች በደንብ ማየት ይችላል፤በአሏህ ፍቃድ በርዕሱም ላይ ሰፋ ያለ ግንዛቤንም ይሸምታል።
~ ወሏሁ ኣዕለም ~~~
ኢንሻአሏህ የረሳሁት ነገር ካለ እመለሳለሁ
337 viewsأبو سعيد, 01:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-28 04:52:47 ~ ዘካቱል ፊጥር ~
ክፍል ሦስት
①ዘካቱል ፊጥር የሚሰጥበት ጊዜ መች ነው??
ዘካቱል ፊጥር የሚሰጥበትን ጊዜ አስመልክቶ በዑለሞች መካከል በርካታ አቋሞች ቢስተዋሉም ከመረጃ አንፃር ጠንካራው አቋም እንደሚከተለው ነው

አንደኛ:—ዘካቱል ፊጥር መስጠት ፍቁድ የሚሆንበት ጊዜ ነው።ይህም ጊዜ ከኢዱ አንድ ቀን ወይም ሁለት ቀን ቀደም ብሎ ያለው ጊዜ ነው።በዚህ መሰረት አንድ ሰው ዘካውን ከኢዱ አንድ ቀን ወይም ሁለት ቀን አስቀድሞ መስጠት ይችላል ማለት ነው።ይህም ተግባር ከሶሓቦች ተገኝቷል።ይህን አስመልክቶ የሚከተለው ዘገባ መጥቷል
عن ابن عمر قال " كانوا يعطونها قبل الفطر بيوم أو يومين" (رواه البخاري)
"(ሶሓቦች) ከፊጥር ( ከኢድ) በአንድ ወይም በሁለት ቀን አስቀድመው ( ዘካተል ፊጥርን) ይሰጡ ነበር " ( ቡኻሪ ዘግበውታል)

ሁለተኛ:—ዘካቱል ፊጥር መስጠት ግዴታ የሚሆንበት ጊዜ።
ዘካቱል ፊጥር መስጠት ግዴታ የሚሆንበትን ጊዜ አስመልክቶ በኢስላም ሊቃውንቶች መካከል ሁለት አቋሞች የተንፀባረቁ ሲሆን ፤ የአብዛሃኛው ሊቃውንቶች አቋም ዘካቱል ፊጥር መስጠት ግዴታ የሚሆነው የረመዷን የመጨረሻው ቀን ፀሐይ ከጠለቀችበት ወቅት አንስቶ ነው የሚለው ነው።በዚህ አቋም መሰረት የረመዷን የመጨረሻው ቀን ፀሐይ ከመጥለቋ በፊት የተወለደ ልጅ ፤ ፀሐይ ከጠለቀች በኋላ የሞተ ሰው እና ፀሐይ ከመጥለቋ በፊት የሰለመ ሰው ላይ ዘካቱል ፊጥርን ማውጣት ግዴታ ይሆናል ማለት ነው።

ሦስተኛ: —ዘካቱል ፊጥርን ለመስጠት በላጩ ጊዜ ነው።
ዘካቱል ፊጥርን ለመስጠት በላጩ ጊዜ የሚባለው የኢዱ ዕለት ከኢድ ሶላት በፊት መስጠት ነው።ይህም የሆነው እንዲህ የሚል ሐዲስ ከመልዕተኛው ﷺ ስለተዘገበ ነው :—
عن اين عمر أن النبي " أمر أن تؤدى قبل خروج الناس إلى الصلاة "(رواه البخاري ومسلم)
ነብዩ ﷺ " (ዘካቱል ፊጥር) ሰዎች ወደ ሶላት ከመውጣታቸው በፊት እንድትሰጥ አዘዋል"
( ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል)

በዚህ ሐዲስ መሰረት በላጩ ጊዜ መልዕክተኛው ﷺ እንዲሰጥ ያዘዙበት ወቅት ነውና የምንችል ሰዎች ዘካችንን በዚህ ወቅት ብንሰጥ የተሻለ ይሆንልናል።

አራተኛ: —ከኢዱ ሶላት በኋላ ያለው ወቅት ነው።
ዘካውን ሆን ብሎ ከሶላት በኋላ መስጠት ሐራም የሆነ ተግባር ነው።እንዲሁም ዘካው እንደ ዘካተል ፊጥር እንደማይቆጠር ፍንትው ባለ ገለፃ ሐዲስ ላይ ተቀምጧል።ይህም :—
عن ابن عباس " فمن أداها قبل الصلاة فهي زكاة مقبولة، ومن أداها بعد الصلاة فهي صدقة من الصدقات"( أخرجه أبو داود وابن ماجاه)

" (ዘካተል ፊጥርን) ከሶላት በፊት የሰጠ እርሷ( ዘካዋ) ተቀባይነት ያላት ዘካ ናት፤ ከሶላት በኋላ የሰጠ እርሷ ከሶደቃዎች አንዷ ሶደቃ ናት "
( አቡ ዳዉድ እና ኢብኑ ማጃህ ዘግበውታል)

ስለዚህ ዘካችንን ከሶላት በኋላ የምንሰጥ ከሆነ ተራ ሶደቃ እንጂ ዘካተል ፊጥር አይሆንም ማለት ነው።
ማሳሰቢያ
✘አንድ ሰው በዑዝር ምክንያት ከሶላት በኋላ ቢሰጥ፤ ለምሳሌ መንገድ ላይ እያለ ነገ ኢድ መሆኑን ቢሰማና በራሱ ወይም በሰው አማካኝነት ዘካቱል ፊጥርን ማስተካከል እና ከሶላት በፊት መስጠት ባይችል ምንም ችግር የለውም።ከሰገደ በኃላ አስተካክሎ መስጠት ይችላል፤ ዘካውም እንደ ዘካተል ፊጥር ይቆጠርለታል።
✘የረመዷን የመጨረሻው ቀን ፀሐይ ከመጥለቋ በፊት ለተወለደ ልጅ ዘካ ማውጣት ግዴታ ነው ያልነው ከመወለዱ በፊት ለሱ ዘካ ማውጠት ተወዳጅ እንጂ ግዴታ አይደለም ብለን ከዚህ በፊት ስላየን ነው።
~ ወሏሁ ኣዕለም ~
ኢንሻአሏህ ይቀጥላል
227 viewsأبو سعيد, 01:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-27 20:41:52 السلام عليكم ورحمة الله وبركاته
ያ ጀማዓተል ኸይር! ከዚህ ቀደም ጀምረነው የነበረው የኑር መስጂድ ግንባታ ገቢ ማሰባሰብ ሂደት ከነገ ዛሬ እንቀጥላለን እያልን ብሎም እናንተም እንዳትሰለቹብን እየሰጋን እሰከ ዛሬ ደርሰናል። የሆነው ሆኖ ይህ የቸርነት ወር የሆነውን ረመዷን ግን በጭራሽ እድሉን ልንነፍጋችሁ እንደማይገባ ወስነናል። ስለሆነም ነገ ማለትም ረመዷን 27ተኛው ሌሊት ከተራዊሕ ሰሏት በኋላ 4:30pm እዚሁ ግሩፕ ላይ እንገናኝ። ኢንሻ አሏህ!

በሰላት፣ በዚክር፣ በቂርኣትና ዱዓእ ለይለተል ቀድርን እንደምንጠባበቀው ሁሉ ቀጣይነት ባለው ሰደቃ ሌሊቱን ህያው በማድረግም እንጠባበቀዋለን!! አሏህ የነገ ሰው ይበለን!

#ማስታወሻ
ሁላችሁም የምታውቋቸውን በቴክስትም ይሁን ደውል ለቀጠሯችን ጋብዙልን። ምንዳችሁ ከአሏህ ነው።

NUR MESJID BUILDING PROJECT ( METTU )
ለፕሮጀክቱ ድጋፍ በነዚህ አካውንት ይጠቀሙ
ኑር መስጂድ ( መቱ )
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
1000258886937

Gargaarsa projeektichaaf akkawunti kanatti fayyadamaa.
Masjiida Nuur ( Mattu )
Baanki daldala Ethiopia
1000258886937
https://t.me/Nurmesjid1
254 viewsأبو سعيد, 17:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ