Get Mystery Box with random crypto!

💎ስለ ማርያም አማላጅነት እንመሰክራለን✍

የቴሌግራም ቻናል አርማ join_maryam_amalajinet_telegram — 💎ስለ ማርያም አማላጅነት እንመሰክራለን✍
የቴሌግራም ቻናል አርማ join_maryam_amalajinet_telegram — 💎ስለ ማርያም አማላጅነት እንመሰክራለን✍
የሰርጥ አድራሻ: @join_maryam_amalajinet_telegram
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 34.51K
የሰርጥ መግለጫ

የዚህ ቻናል አላማ ስለ ድንግል ማርያም,ፃድቃን,መላእክት እና ሰማእይታት አማላጅነትና ገድል ተአምራታቸውን እንዲሁም ክብራቸውን መመስከር ነው። ለህይወታችን ለሚገጥሙን ፈተናዎች አስተማሪና ጠቃሚ የሆኑ መልእክቶች ይገኙበታል።

Ratings & Reviews

2.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 5

2023-03-05 12:07:35
ስራኝ እንደገና
አይን አለኝ አላይም ጆሮ አለኝ አልሰማ፣
ህሌናዬ ቆስሎ መንፈሴ እየደማ፣
የማላመሰግን ባለኝ የማረካ፣
የብብቴን ጥዬ የቆጡን የምመኝ።
በልቸ ማልጠግብ ጠጥቸ ማረካ፣
የሰውን የምመኝ የእራሴን ሳልነካ፣
ውሉ እንደጠፋበት ልቃቂት በሆነች፣
ላይ ላይዋን አስውባ ውስጧን በመረዘች፣
በእሾሃማ ወርቋ ዙሪያየን ታጥሬ፣
በዚህች ቡትቶ አለም አለው እስከዛሬ።
ህሌናየን ሽጬ ስጋየን አርክሼ፣
በሀሰተኛ ምላስ ባሰት ቃል ተክሼ፣
ያኔ አቤት ማማሬ በንግስት ወንበሬ፣
ነፍሴ ጮቤ ስትረግጥ በወይን ሰክሬ።
ዛሬ ግን አባቴ
ቃልህን ዘንግቸ ለስጋዬ አድልቸ፣
የኖርኩበት ሂይዎት አንተን እረስቸ፣
ዛሬ ተፀፅቸ ህሌናዬ ደምቶ፣
ለበድን ስጋዬ ሳለ በቁም ሞቶ፣
መጣው ልጠይቅህ አንድ የይቅርታ ቃል፣
መቸም የእኔ ጌታ ምህረትህ መች ያልቃል።
አንተን ብቻ ላክብር ይንበርከክ ጉልበቴ ፣
ስምህን ላመስግን ቃል ያውጣ አንደበቴ፣
ትላንትን ረስቸ ቤትህ እንዲሆን ቤቴ፣
እንግዲህ አባቴ
ስራኝ እንደገና ዛሬ ይሁን ልደቴ።
3.5K views09:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-08 13:01:05
ጨለማ ሲበዛ ድንጋይ ይደበቃል፣ ከዋክብት ግን ይደምቃሉ።
መከራ ሲበዛ ቅዱሳን ይገለጣሉ፣ ኃጥአን ግን ይደበቃሉ።
ጨለማ ለኮከብ መድመቅያው ነው ለድንጋይ ግን መደበቅያ ነው።
መከራ ለክርስቲያን መድመቅያው እና መብዣው ነው።
ክርስቲያንን የሚያበዛው መከራ ነው። ክርስቲያንን የሚያሳንሰው ኃጢአት ነው።
ርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን
4.4K viewsedited  10:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-04 14:18:01
ለምን ይመስላችዋል ማህተባችንን እግራችን ላይ ያላሰርነው?
. ምክንያቱም ሰው፣እግር ቢቆረጥ ስለማይሞት ነዉ። ለምንስ እጃችን ላይ አላሰርንም?
. ምክንያቱም እጃችን ቢቆረጥ ስለማንሞት።
. ግን አንገታችን ላይ አስረናል ይህም ማለት ሰው፣አንገቱ ቢቆረት ይሞታል።
. ለክርስትናችን ህይወታችንን አስከመስጠት ድረስ፣እንታመናለን።
. ስጋን የሚገሉትን አንፈራም ይልቁን ነፍስንም ስጋንም በገሀነም ሊያጠፋ የሚቻለውን የድንግል ማርያም ልጅን እንፈራለን እንጂ።
. እናንተ ግደሉን፣እኛ እየሞትን እንበዛለን ምክንያቱም የያዝነው የቀራኒዮ አሸናፊውን የድንግል፤ማርያምን ልጅ ክርስቶስን ነው።
ብፁዕ አቡነ ናትናኤል በአንድ ወቅት ከተናገሩት
331 views11:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-04 09:17:39
መድኃኔዓለም ሆይ!
አቤቱ አቤቱ ስንልህ በከንቱ እንዳንጠፋ ጠብቀን
2.5K views06:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-03 12:57:11
ቅዱስ ሲኖዶስ ጥሪ አቀረበ!
ጥቁር ልብስ

ጾመ ነነዌን ምክንያት በማድረግ ከ ሰኞ እስከ እረቡ (ከጥር 29 እስከ የካቲት 1) ጥቁር ልብስ ብቻ በመልበስ በጾምና በጸሎት ምሕላ በመያዝ ከቤተ ክርስቲያን ዓውደ ምህረት በመገኘት ወደ እግዚአብሔር ጾም፣ ጸሎትና ምሕላ እንድታቀርቡ ሲል ቅዱስ ሲኖዶስ ጥሪ አስተላለፈ።
ሼር በማድረግ ላልሰሙት የተዋህዶ ልጆች አሰሙ
3.8K viewsedited  09:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-02 11:19:43
<<ቆማችሁ ነፃነታችሁ ከሚረክስ
ሙታችሁ ስማችሁ ይቀደስ>>
ኢትዮጵያዊ ሰማዕት ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ።
3.4K viewsedited  08:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-29 11:17:05 ጥር 21 ድንግል ማርያም በ 64 አመቷ ያረፈችበት እለት
የጥንት ቅዱሳን አባቶቻችን ስለ እመቤታችን ዕረፍትና ትንሳኤ በዓይናቸው ያዩትንና የተማሩትን እንዲህ ይመሰክራሉ!
....................
1. # ኢቮድየስ_ዘአንጾኪያ (የሐዋርያው የቅዱስ ጴጥሮስ ደቀመዝሙር) :- ይህ ታላቅ አባት ከጴጥሮስ ጋር አብሮ የነበረ፣ የድንግል ዕረፍትዋ በዓይኑ የተመለከተ፣ የትንሳኤዋም ሕያው ምስክር የሆነ ነው! ያየውምን ነገር በሙሉ "Homily on the Dormition of the falling asleep of Mary" በተባለው ክታቡ እንዲህ ይተርካናል!
...........
(ነሐሴ) ወር በአስራ ስድስተኛው ቀን ጠዋት በተመሳሳይ ምሽት በብርሃን ሰዓት፣ ጌታችን በታላቅ ክብር ወደኛ መጣ! ሰግደንም አመለክነው! ጌታም "ለምን ታዝናላችሁ?" ሲለን፣ አባቴ ጴጥሮስም "በእናትህና በሁላችን እመቤት ሞት፣ ከሞተችም ብኋላ ስጋዋን ስላላሳየሀን ነው" አለው! ጌታም ወደ መቃብሩ በመጣራት የድንግል እናቱን ስጋ በማስነሳት፣ ነፍስዋንም እንደገና ወደ ስጋዋ በማስገባት ልክ ቀድሞ በስጋ እንደምናውቃት በስጋ አየናት። መድኃኒታችንም ለስለስ ባለ ድምፅ "እነኋት ውድ እናቴን" አለን። ይህ የሁላችን እመቤት እና የወላዲተ አምላክ የሕይወትዋ መጨረሻው ይህ ነው በጦቢ(ጥር) ወር 21ኛ ቀን። ትንሳኤዋ ደግሞ በሜሶሪ (ነሐሴ) ወር በ16ኛው ቀን ነው> በማለት ከቀብሯ ተገኝቶ ትንሳኤዋን አይቶ ይመክረናል።
.............
2.ቅዱስ # ቴዎዶስዮስ_ዘእስክንድርያ (535 ዓ.ም)
አባታችን ቴዎዶስዮስ ስለ ትንሳኤዋ ሲንፕግረን <የነበሩበት ቦታ በእሳት ተሞላ። ጌታም በኪሩቤል ላይ ሆኖ የድንግልንም ነፍስ በእቅፉ በሰማያዊ ልብስ አጊጣ ይዟት ተገለጠ። ሐዋርያትም በፍርሐት ተሞልተው መሬት ላይ እንደ ሞቱ ሆኑ። እርሱ ፍርሐታቸውን አጥፍቶ እንዲህ አላቸው "እናንተ ደቀመዛሙርቴና ደናግል ሆይ፥ የእናቴን ክብር ታዩ ዘንድ ተነሱ።" እንዲህ ብሎም ወደመቃብሩ ጮሀ "ለእኔ መቅደስ የሆነሽኝ አንቺ ቅድስት ስጋ ሆይ፣ የእኔ የዘላለም ድንኳን የሆነችኝን ይህቺን ነፍስ ውሰጂ" ... ጌታ እነዚህን ቃላት ሲናገር መቃብሩ በዚያ ቅፅበት ተከፈተ... ከዚያም ብኋላ የከበረው የድንግል ስጋ ተነሳ፤ ነፍስዋንም አከበረቻት። ሁለት ወንድማማች ከተለያየ ሀገር እንድሚመጡ እንዲሁ ተባበሩ አንድም ሆኑ> ብሎ ወደ ትንሳኤዋ ይወስደናል።
.............
3.ቅዱስ # ዮሐንስ_ዘደማስቆ (675-749)
ይህ ቅዱስ አባትም <እርስዋ ልጅን ስትወልድ ድንግልናዋ እንደተጠበቀ እንዲሁ ስጋዋ ከሞትም ብኋላ ከመበስበስ የተጠበቀ ይሆን ዘንድ የተገባ ሆነ። ፈጣሪን በሕፃንነቱ በደረቷ እንዳቀፈችው እንዲሁ በመለኮታዊው ድንኳን (ሰማያዊ መቅደስ) ትኖር ዘንድ ተገባት! የእግዚአብሔር እናት የልጇ የሆነውን ነገር (ትንሳኤ) ታገኝ ዘንድ በፍጥረት ሁሉም የእግዚአብሔር እናትና አገልጋይ ተብላ ትመሰገን ዘንድ ሆነች> ይለናል።
.............
4.ቅዱስ # ጌርማነስ_ዘቁስጥንጥንያ (8ኛ ክ.ዘ)
ይህ አባት ደግሞ <አንቺኮ እንደ ተፃፈው በውበት የተገለጥሽ፣ ድንግል የሆነ ስጋሽም ቅዱስና ንጹሕ፣ መላውም የእግዚአብሔር ማደርያ ነው። ስለዚህም ጠቅልሎ አፈር ሆኖ ከመቅረት ነጻ ሆነ (ቀረ) ምንም እንኳን አሁንም ሰው ብትሆኚ ሥጋሽ ወደ ማይበሰብስ ሰማያዊ ሕይወት (አካል) ተቀየረ! አሁንም ስጋሽ በሕይወትና በክብር፣ ሳይጎድፍና ሳይጎድል በፍፁም ኑባሬ አለ!> እያለ ከእናቱ ከእናታችን ጋር ያወጋል። በአባቶቻችን እምነት ያፅናን!
.... የትንሳኤዋ በረከት ከወደቅንበት ኃጢኣት ያንሳን!
9.3K views08:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-26 06:40:36
ጥር 18
የቅዱስ ጊዮርጊስ አመታዊ ክብረ በዓል ነው
አጥንቱ የተበተነበት ደሙ የፈሰሰበት
70 ነገስታት ያፈሩበት እለት ነው
ጥር 18 " ዝርወተ ዓጽሙ " ቅዱስ ጊዮርጊስ ሊቀ ሰማዕታት ይህቺ ዕለት ለሰማዕቱ 'ዝርወተ አጽሙ' ትባላለች:: በቁሙ 'አጥንቱ የተበተነበት' እንደ ማለት ነው:: ቅዱስ ጊዮርጊስን ለዘመናት በብዙ ስቃያት ሲያስጨንቁት ኖረው በጽናቱ አሸነፋቸው:: 70 ነገሥታትን ከነ ሠራዊታቸው ከማሳፈሩ ባሻገርም በርካታ (በመቶ ሺ የሚቆጠሩ) አሕዛብን ማርኮ ለሰማዕትነት አበቃ:: በዚህ የተበሳጨ ዱድያኖስም ኮከበ ፋርስ ቅዱስ ጊዮርጊስን እንዲቆራርጡት አዘዘ:: ወታደሮቹም ቅዱሱን ቆራርጠው: በብረት ምጣድ ላይ ጠበሱት:: ያለ ርሕራሔም አካሉን አሳረሩት:: ቀጥለውም ፈጭተው አመድ አደረጉት:: በአካባቢው ወደ ነበረው ትልቅ ተራራ ጫፍ (ደብረ ይድራስ) ወጥተውም በነፋስ በተኑት:: "ሐረድዎ ወገመድዎ: ወዘረዉ ሥጋሁ ከመ ዓመድ "እንዲል:: እነርሱ ይህንን ፈጽመው ዘወር ሲሉ ግን የቅዱሱ ዓጽም ባረፈባቸው ዛፎች: ቅጠሎችና ድንጋዮች ሁሉ "ቅዱስ ጊዮርጊስ ሊቀ ሰማዕታት" የሚል ጽሑፍ ተገኘ:: ስለዚህም ይሕቺ ዕለት ቅዱሱ አለቅነትን የተሾመባት ናት ማለት ነው:: ወዲያው ግን ኃያል ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስ ከተበተነበት ተነስቶ ወታደሮችን አገኛቸውና "በክርስቶስ እመኑ" ብሎ: አስደንቆ ወደ ሕይወት መራቸው:: 70ው ነገሥታት ግን አፈሩ:: የሊቀ ሰማዕታት ቅ/ጊዮርጊስ በረከቱ ይደርብን ሼር በማድረግ ላላወቁት አሳውቁ
ቅዱስ ጊዮርጊስ ፈጥኖ ደራሹ በመከራ ግዜ ፈጥኖ ይድረስልን
አጥንታችንን ለመፍጨት ደማችንን ለማፍሰስ የተነሱትን ቅዱስ ጊዮርጊስ ያፍዝዝልን ሀገራችንን ሰላም ያርግልን
13.8K views03:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-20 09:06:02
እንኳን ለቃና ዘገሊላ አደረሳችሁ
ቃና ዘገሊላ

ቃና ዘገሊላ /2/ በዛ በሠርግ ቤት
ተገኝተሻል ድንግል ከልጅሽ ጋራ
ተገኝተሃል ጌታ ከእናትህ ጋራ
.........................................
እድምተኞች ሞልተው የተጋበዙበት
ሲበሉ ሲጠጡ ወይኑ አልቆበት
ድንግል እናታችን ቤዛዊት ዓለም
አንቺ ደረሽለት ሆንሽው አማላጅ
.......................................
አንተ እያለህስ ማፈር የለባቸው
ሁሉ ይቻልሃል ወይኑን ሙላላቸው
ማድጋው ባዶ ነው ብለሽ የተናገርሽ
ጌታን ያሳሰብሽው አመቤታችን ነሽ
.............................................
የጌታ አምላክነት የተገለጠበት
ምንኛ ታደለ የነዶኪማስ ቤት
ዛሬም የኔ ህይወት ወይኑ ጎድሏልና
ድረሺ እመቤቴ ርህሪተ ህሊና
.......................................
ውሃው ተለውጦ የወይን ጠጅ ሲሆን
በቃና ገሊላ ሁላችን አየን
እግዚአብሔር ከኖረ በመካከላችን
ሁሌ ይሰጠናል ይህን መሰል ወይን።

ድንግል ማርያም ዛሬም በህይወታችን የጎደለውን ትሙላልን
539 views06:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-18 07:13:19
ጥር 10 #ከተራ
እንኳን ለጌታችን ለመድሃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀት በዓል በሰላም አደረሳችሁ!!! #መልካም_በአል!
#ከተራ ምንድን ነው?
ከተራ 'ከበበ' ካለው የግእዝ ግሥ የወጣ ነው፡፡ ፍችው ውኃ መከተር፣ መገደብ ማለት ነው፡፡
በጥምቀት ዋዜማ ታቦተ ሕጉ ከቤተ መቅደስ ወጥቶ ውኃ ባለበት አካባቢ ስለሚያድር የየአጥቢያው ሕዝብ እየተሰበሰቡ በወንዝ ዳር ወይም በምንጭ አካባቢ ድንኳን ይተከላሉ፡፡ ድንኳንም ከሌለ ዳስ ሲጥሉ ይውላሉ፡፡ የምንጮች ውኃ እንዲጠራቀም ይከተራሉ (ይገድባሉ) ጉድጓድ እየተቆፈረ ውኃው እንዳይሄድ በመገደብ ለመጠመቂያ (ለጥር 11) ዝግጁ የሚያደርጉበት ዕለት ነው፡፡
በተጨማሪ በአቅራቢያ የሚገኙት ቤተክርስቲያናት ተሰብስበው ከዚሁ ከተቆፈረው ገንዳ ወይም ከተገደበው ጅረት አጠገብ ባለው ዳስ ወይም ድንኳን ታቦቶቻቸውን ያሳድራሉ ሊቃውንቱም በዚያው እግዚአብሔርን በማህሌት ሲያመሰግኑ ያድራሉ።
በበዓለ ጥምቀት የታቦታቱ ወደ ወንዝ መውረድ መድኃኔ ዓለም ክርስቶስ በእደ ዮሐንስ ለመጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ በዋዜማው የመሄዱ ምሳሌ ነው፡፡ ታቦቱ የጌታችን፣ ምሳሌ ሲሆኑ ካህናቱ የመጥምቁ ዮሐንስ ምሳሌ ናቸው፡፡ መዘምራኑና ሕዝቡ ደግሞ ዮሐንስ ያጠመቃቸው ሕዝቦች ምሳሌዎች ናቸው፡፡
@ orthodox tewahido
3.2K viewsedited  04:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ