Get Mystery Box with random crypto!

ግጻዌ

የቴሌግራም ቻናል አርማ gitsawe — ግጻዌ
የቴሌግራም ቻናል አርማ gitsawe — ግጻዌ
የሰርጥ አድራሻ: @gitsawe
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 11.19K
የሰርጥ መግለጫ

የየዕለቱን ግጻዌ የቅዳሴ ጊዜ ምንባባትና ምስባክ በዚህ ቻናል ያገኛሉ።

Ratings & Reviews

5.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 7

2023-03-07 23:57:38 #የካቲት_29
ተዝካረ ልደቱ ለእግዚእነ ወአባ ቢላካርዮስ ሰማዕት ኤጲስ ቆጶስ ዘሀገረ አርሞኒ።
               #ዘነግህ_ምስባክ
ወኢሰምዑኒ ሕዝብየ ቃልየ
ወእስራኤልኒ ኢያጽምዑኒ
ወፈነውኩ ሎሙ በከመ ምግባሮሙ
              #ትርጉም
ሕዝቤ ግን ቃሌን አልሰሙኝም
እስራኤልም አላዳመጠኝም
እንደ ልባቸው ሥራ ተውኋቸው።
                   #መዝ_80 ፥ 11
            #ወንጌል
#ማቴዎስ_22 ፥ 1 - 5 :- "ወአንሥአ እግዚእ ኢየሱስ...."
               #ዘቅዳሴ
#ሮሜ_8 ፥ 3 - 12 :- "ወሶበ ተስእኖ ለሕገ ኦሪት..."
#1ኛ_ዮሐንስ_4 ፥ 7 - 18 :- " አኃዊነ ለንትፋቀር በበይናቲነ..."
#የሐዋ_ሥራ_9 ፥ 20 - 32 ፦ "ወሰበከ በጊዜሃ በምኵራባት..."
                  #ምስባክ
እግዚአብሔር ይቤለኒ ወልድየ አንተ
ወአነ ዮም ወለድኩከ
ሰአል እምኔየ እሁበከ አሕዛበ ለርስትከ
                 #ወንጌል
#ሉቃስ_2 ፥ 1 - 21 :- "ወኮነ በውእቱ መዋዕል ወጽአ ትእዛዝ..."
#ቅዳሴ :- ዘእግዚእነ።

@gitsawe
@gitsawe
@gitsawe
@gitsawe
1.1K views20:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-06 21:57:33 @gitsawe
@gitsawe
460 views18:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-06 21:45:07 #የካቲት_28
ተዝካረ አብርሃም ይስሐቅ ወያዕቆብ ወቴዎድሮስ ሮማዊ ዘወጽአ እምአፈ ፈረሱ መንፈሳዊ እሳት ወአጥፍዖሙ ለዐላውያን ወለጎምዎ አፉሁ ወቀነውዎ እገሪሁ
#ዘነግህ_ምስባክ
እግዚአብሔር ይረድኦ ውስተ ዐራተ ሕማሙ
ወይመይጥ ሎቱ ኵሎ ምስካቤሁ እምደዌሁ
አንሰ እቤ እግዚኦ ተሣሀለኒ።
#ትርጉም
እግዚአብሔርም በደዌው አልጋ ላይ ሳለ ይረዳዋል
መኝታውን ሁሉ በሕመሙ ጊዜ ያነጥፍለታል
አቤቱ እኔንስ ማረኝ
#መዝ_40:3
#ወንጌል
#ማቴዎስ_9፥1-9 :- "ወዐሪጎ ውስተ ሐመር....."
#ዘቅዳሴ
#ዕብራው_11፥8-22 :- "በተአምኖ ሰምእ ዘተሰምየ አብርሃም....."
#ያዕቆብ_3፥1- ፍጻሜ :- " ወኢይኩኑ እምውስቴትክሙ ብዙኃን..."
#የሐዋ_ሥራ_7፥1-17 ፦ "ወይቤሎ ሊቀ ካህናት...."
#ምስባክ
ዘሠርዓ ለአብርሃም
ወመሐለ ለይስሐቅ
ወአቀመ ስምዐ ለያዕቆብ
#ትርጉም
ለአብርሃም ያደረገውን ለይስሐቅም የማለውን
እስከ ሺህ ትውልድም ያዘዘውን ቃል
ኪዳኑን ለዘለዓለም አሰበ።
#መዝ_104፥9
#ሉቃስ_20፥37 - ፍጻሜ :- "ወከመሰ የሐይዉ ሙታን...."
#ቅዳሴ :- ዘእግዝእትነ ማርያም

@gitsawe
@gitsawe
@gitsawe
@gitsawe

#like #share
499 viewsedited  18:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-04 21:43:33 #ግጻዌ

የካቲት 26
#ምስባክ_ዘምኵራብ
እስመ ቅንዓተ ቤትከ በልዓኒ
ትእይርቶሙ ለእለ ይትዔየሩከ ወድቀ ላዕሌየ
ወቀጻዕክዋ በጾም ለነፍስየ
#ትርጉም
የቤትህ ቅንዓት በልታኛለችና
የሚሰድቡህም ስድብ በላዬ ወድቋልና
ነፍሴን በጾም አስመረርኋት።
#መዝ_68:9-10
#ወንጌል
የዮሐንስ_ወንጌል_2፥12-ፍጻሜ
#ቅዳሴ:- ዘእግዚእነ

@gitsawe
@gitsawe
@gitsawe
@gitsawe
469 viewsedited  18:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-25 21:36:40 መዝሙር ዘቅድስት

በ (፭)

ግነዩ ለእግዚአብሔር ወጸውዑ ስሞ ወንግርዎሙ ለአሕዛብ ምግባሮ ሀቡ ስብሐተ ለስሙ አክብሩ ሰንበተ ተገበሩ ጽድቀ ዝግቡ ለክሙ መዝገበ ዘበሰማያት ኀበ ፃፄ ኢያማስኖ ወኢይረክቦ ሰራቂ ድልዋኒክሙ ንበሩ ዘበላዕሉ ሀልዩ ኀበ ሀሎ ክርስቶስ።

ትርጉም፦

ለእግዚአብሔር ተገዙ ስሙንም ጥሩ ሥራውን ለአሕዛብ ንገሯቸው ለስሙ ምስጋናን ስጡ/አቅርቡ ሰንበትን አክብሩ ጽድቅን ሥሩ ሌባ በማያገኘው ብል በማያጠፋው በሰማያት መዝገብን አከማቹ ክርስቶስ ባለበት ለመሆን በላይ ያለውን እያሰባችሁ ተዘጋጅታችሁ ኑሩ።

ምስባክ፦

እግዚአብሔርሰ ሰማያተ ገብረ
አሚን ወሠናይት ቅድሜሁ
ቅድሳት ወዕበየ ስብሐት ውስተ መቅደሱ መዝ ፺፭፥፭

ትርጉም፦

እግዚአብሔር ግን ሰማያትን ፈጠረ
እምነትና በጎነት በፊቱ ናቸው
ቅድስና እና የክብር ገናንነት በመቅደሱ ውስጥ ናቸው።

ምሥጢር፦

እግዚአብሔር ሰባቱን ሰማያት ፈጠረ
ሃይማኖት ምግባር በፊቱ ነው አለ ምግባር ሃይማኖት የያዘ ሰውን ይወዳል

ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ ተብሎ መመስገን ዓቢየ ስብሐት መባል ገንዘቡ ነው

የዕለቱ ወንጌል፦

ማቴ ፮፥፲፯ - ፳፭

ቅዳሴ፦ ዘኤጲፋንዮስ
430 views18:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-18 20:59:06 #የካቲት_12
መዝሙር ዘዐቢይ ፆም ዘዘወረደ ፩ኛ መዝሙር ተቀነዩ ለእግዚአብሔር፡፡
              #ዘቅዳሴ
#ዕብራው_13:7-17፡ተዘከሩ መኳንንቲሆሙ ዘነገሩክሙ ቃለ እግዚአብሔር
#ያዕቆብ_4:6-ፍጻሜ፡ወበእንተ ዝንቱ ይቤ
#የሐዋ_ሥራ_25:13-ፍጻሜ፡ወእምድኅረ ኅዳጥ መዋዕል
             #ምስባክ
ተቀነዩ ለእግዚአብሔር በፍርሃት
ወተሐሠዩ ሎቱ በረዓድ
አጽንዕዋ ለጥበብ ከመ ኢይትመዐዕ እግዚአብሔር
  #መዝ_2:11-12
            #ወንጌል
#ዮሐንስ_3:10-25፡ወአውሥአ እግዚእ ኢየሱስ ወይቤሎ
  #ቅዳሴ፡ዘእግዚእነ፡፡(ነአኩተከ)
  @gitsawe
416 views17:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-16 12:47:05 https://t.me/+X_R4zZFqlCwzYTVk

በጣም አጫጭር ነገር ግን በጣም ጠቃሚ ፅሁፎች የሚለቀቁበት ቻናል ነው። ቻናሉን join ያድርጉ
373 views09:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-16 12:46:54 ሰውን ብትታገልና ብትዋጋ ታሸንፈዋለህ፤ ወይም ያሸንፍሃል፤ ቤተ ክርስቲያንን ግን
ማሸነፍ አይቻልም። ቤተ ክርስቲያን ሁልጊዜ ትዋጋለች፤ ተሸንፋም አታውቅም። ዲያብሎስ
ዝናሩን አራገፈ ቀስቱን ጨረሰ ቤተ ክርስቲያንን ግን ሊያጠፋት አልቻለም።
         
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
       
348 views09:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-16 11:26:02 አባቶቻችን በኀዘን ተውጠው ስለ ቤተ ክርስቲያን ሲያለቅሱ አምነናቸው አብረን ካለቀስን ደስ ሲላቸውና ደስ ይበላችሁ ሲሉንም እንዲሁ ልናምናቸው ይገባል፡፡ ስለ ቤተ ክርስቲያን አንድነት አልቅሰን ከጾምን አንድ ሆነች ሲባል ‘አይዋጥልኝም’ ማለትም ‘ታዲያ የጸለያችሁት ምን ይሁን ብላችሁ ነው?’ ያስብላል፡፡ ሊቃነ ጳጳሳቱ ‘አምላካችን ሆይ ስማን በሉ’ ሲሉ እንደተቀበልናቸው ‘ሰምቶናል’ ሲሉንም አብረን ማመስገን የልጅነት ግዴታችን ነው፡፡ ነገሩ ምንም ያልተዋጠልን እንኳን ብንሆን አባቶቻችንን አትንኩብን ስንል በከረምንበት አፋችን ለመሳደብ ብንነሣ እንኳንስ እግዚአብሔር ሶሻል ሚድያውም ይታዘበናል፡፡ ቅዱስ ሲኖዶስን ሌላው ሲያቃልለው ከተቃወምን እኛም የማቃለል መብት የለንም፡፡ ሁሉም ሰው መሪ ሊሆን ስለማይችል ጉዳዩን በትኩረት ለያዙት አባቶች ሥራቸውን እንደ ጀመሩት እንዲፈጽሙ እየጸለይን በምንችለው ማገዝ እንቀጥል፡፡

ከዚህ በኋላ ያለው ጊዜ የተሰበረውን የምንጠግንበት ፣ ቤተሰቦቻቸውን ያጡትን የምንደግፍበት ፣ ሰማዕታቱን የምንዘክርበት ፣ በመከራዋ ቀን ለጮህንላት ቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ሁለንተናዊ ድጋፍ የምናደርግበት ነው፡፡ እስካሁን የገጠሙን ችግሮች ያልተሠሩ ሥራዎች ውጤት መሆናቸውን በማሰብ ሌላ ሰው አጀንዳ እስኪያቀብለን በመጠበቅ ሳይሆን እኛ አጀንዳ ሠጪ እየሆንን የተቀጣጠለውን ፍቅረ ቤተ ክርስቲያን ለወንጌል አገልግሎት የምናውልበት ዕድል አሁን ነው፡፡ መጪው ዐቢይ ጾም ነውና እያበጣበጠ ሲያፌዝብን የከረመውን ዲያቢሎስ በርትተን የምንቀጣበት እድልም ከፊታችን ነው::

አሁንም ደግመን እንላለን :-

አንድ ፓትርያርክ
አንድ ሲኖዶስ
አንዲት ቤተ ክርስቲያን

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
የካቲት 8 2015 ዓ.ም.
450 views08:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-16 11:25:23 ላለፉት ሦስት ሳምንታት የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በታሪክዋ አይታው የማታውቀው ሐዋርያዊ ሰንሰለትዋን የሚበጥስ አንዳች ዱብ ዕዳ ገጥሞአት በብዙ ጭንቀትና መከራ ውስጥ አሳልፋለች፡፡ ከልሒቅ እስከ ደቂቅ በጉዳዩ ተደናግጦ ለእናት ቤተ ክርስቲያን ሲኖዶሳዊ አንድነት የሚችለውን ሁሉ ለመክፈል ታይቶ በማይታወቅ አንድነት ተረባርቦአል፡፡

የቤተ ክርስቲያንን ሰላም እስካይ ድረስ ለዓይኖቼ ዕረፍትን ለሽፋሽፍቶቼ እንቅልፍን አልሠጥም ብላችሁ ስለ ቅድስት ቤተ ክርቲያን በምትችሉት ቆማችኋል ፣ ብርድ ላይ አድራችኋል ፣ ለመሞትም ቆርጣችኋል፡፡ አሁን በሰማያዊትዋ የድል ነሺዎች ቤተ ክርስቲያን ሆናችሁ የምታዩን ፣ ዓይናችን እያየ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን አትደፈርም ብላችሁ ሰማዕታት የሆናችሁት ልጆችዋም በረከታችሁ ይድረሰን፡፡ ቤተ ክርስቲያንን ከብባችሁ አካላችሁ የጎደለ ፣ አሁንም ድረስ በአልጋ ላይ ያላችሁ ፣ ቤተሰቦቻችሁን ያጣችሁ ፣ ከቀዬያችሁ የተፈናቀላችሁ እስከ አሁንዋ ሰዓት ድረስ በወኅኒ ቤት ሆናችሁ ከእናንተ መፈታት ይልቅ የችግሩ መፈታት ያስጨነቃችሁ ወንድምና እኅቶቻችን ሥራችሁ በልበ ሥላሴ የተጻፈ ነው፡፡

ቤተ ክርስቲያን ስለተገደሉ ልጆችዋ ስታለቅስና ማቅ ስትለብስም ከዳር ዳር ጥሪዋን ተቀብላችሁ ማቅ የለበሳችሁ ‘ቤተ ክርስቲያን ሆይ ማቅ ልልበስልሽ’ ያላችሁትን በአደባባይ በጥፊ የተመታላት የቤተ ክርስቲያን ራስዋ ክርስቶስ አይቶታል፡፡
ግራ ቀኝ የሚናፈስ ወሬ ነገሩን ሊያደፈርሰው ሲሞክርም በታሪክ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ምእመናን ‘ከሲኖዶስ ሌላ ማንንም አንሰማም’ ብላችሁ ታዝዛችኋል፡፡ ከመቼውም ጊዜ በላይ የቤተ ክርስቲያን ክብርና የቅዱስ ሲኖዶስ ምንነት ሰምተው የማያውቁ ሰዎች ሳይቀር በዚህ የተነሣ የጉዳዩ መሠረታዊነት ግልፅ ሆኖላቸው ፣ ግድ የማይሰጣቸውና ሲኖዶስን ሲሳደቡ የነበሩ እንኳን ‘እኔ ነኝ ያስደፈርኩሽ ቤተ ክርስቲያኔ ይቅር በይኝ’ ሲሉ ሰንብተዋል፡፡

የቤተ ክርስቲያኔን ነገር አደራ ብሎ ያነባው ፣ ንስሓ የገባው ሕዝበ ክርስቲያን እልፍ አእላፍ ነበረ፡፡ መተዳደሪያ ሥራቸውን ፣ ዝናቸውን ፣ ሙያቸውን አደጋ ላይ ጥለው ብዙዎች ለቤተ ክርስቲያናቸው ጮኸዋል፡፡ እምነታቸው ሌላ ሆኖ እንኳን ለቤተ ክርስቲያን የቆሙ ባለውለታዎችም ብዙዎች ናቸው፡፡ ከዚህ ሁሉ በላይ ምንም ዓይነት ማስፈራሪያና ጫና ያልበገራቸው ብፁዓን አበው ታሪክ በማይረሳው መንፈሳዊ ጥብዓትና ጽናት በአንድ ልብ ሆነው በመናገር የቤተ ክርስቲያኒቱ ጠበቆች ሆነዋል፡፡ ሁላችሁም ‘ያደረጋችሁትን ሥራ ለስሙም ያሳያችሁትን ፍቅር ይረሳ ዘንድ እግዚአብሔር አመጸኛ አይደለም’ ዕብ. 6፡10

‘ይህ ሁሉ ለምን ሆነ?’ አንድ ፓትርያርክ ፣ አንድ ሲኖዶስ ፣ አንዲት ቤተ ክርስቲያን በሚል መርሕ የቅዱስ ሲኖዶስን ልዕልና ለማስከበርና የቅዱስ ፓትርያርኩን አባትነት ለማጽናት ፣ በዚህም በሺህ ለሚቆጠሩ ዘመናት የተሻገረችውን ቤተ ክርስቲያን ሳትፈርስ እንድትቀጥል ለማድረግ ነው፡፡ ያ ሁሉ ዕንባና ልቅሶ ፣ ያ ሁሉ ሰማዕትነት አንድ ፓትርያርክ ፣ አንድ ሲኖዶስ ፣ አንዲት ቤተ ክርስቲያን የሚለውን ቀኖናዊ ዶግማ (Canonical Doctrine) ለማስከበር ነበር፡፡ በዛሬው ዕለት ከቅዱስ ሲኖዶስ እንደሰማነው በእግዚአብሔር ቸርነት ለሳምንታት ቤተ ክርስቲያንን እስከ ሰማዕትነት ድረስ ብዙ ዋጋ ያስከፈለው ችግር ተፈትቶ ‘አንድ ፓትርያርክ ፣ አንድ ሲኖዶስ ፣ አንዲት ቤተ ክርስቲያን’ የሚለው የቤተ ክርስቲያኒቱ መርሕ ተከብሮአል፡፡ ፓትርያርካችን ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፤ ሲኖዶሳችን አንድ ፣ ቤተ ክርስቲያናችንም አንዲት ናት የሚለው ጸንቶአል፡፡

ይህ እንዳለ ሆኖ ስለ ክብሩ መደፈር ተቆርቁረን ብዙ የጮኽንለት ቅዱስ ሲኖዶስን የእውነት ማክበራችንና መውደዳችን በተግባር የሚፈተነው አሁን ነው፡፡ ከአባቶቻችን ጎን እንደነበርን ከዚህ በኋላ በሚመጣው ነገር ሁሉም አብረናቸው እንሆን ይሆን? የሚለው ወሳኝ ጥያቄ ነው፡፡ ዛሬ በሰማናቸው መግለጫዎች ላይ የቅዱስ ሲኖዶስ ልዕልና ተከብሯል ፣ ከሕገ ቤተ ክርስቲያን ውጪ የነበረው ሹመትም መሻሩን ሿሚዎቹ ተቀብለዋል፡፡ ቅዱስ ሲኖዶስ ያቀረበውን የመመለስ ጥሪ ተቀብለው ይቅርታ ጠይቀውም የተወገዙት ሊቃነ ጳጳሳት ተመልሰዋል፡፡ ልባችንን ያደማው የቤተ ክርስቲያን መከፈል ጉዳይ ባልተጠበቀ ፍጥነት ተፈትቶ እግዚአብሔር ጸሎታችንን እንደሰማ አይተናል፡፡

በሒደቱ ላይ ነገሮች በጣም በፍጥነት ከመለዋወጣቸው የተነሣ ብዙ ጥያቄ የሚፈጥሩ ዝርዝሮችና ከልባችን ገና ያልወጡ ሥጋቶች መኖራቸው ግን የማይካድ ነው፡፡ ክስተቱ ተመለሱ የተባሉ ሰዎች ሲወላወሉ ባየንበት ማግሥት የሆነ ነገር እንደመሆኑም ለማመን የቸገረንና በሙሉ ልብ ለመደሰት የፈራን ብዙዎች ነን፡፡ ቤተ ክርስቲያን በውግዘት የለየቻቸውን አበው መልሳ የምትቀበልበት አካሔድ እንዴት ነው? ፣ ከዚህ በኋላስ ምን ይፈጠር ይሆን? ፣ ወደነበርንበት ለመመለስ የከረምንበት ሁኔታ ይፈቅድልን ይሆን? መንግሥት በቃሉ ባይገኝስ? በፍርድ ቤት የታዩ ጉዳዮችስ? ይቅርታ የሚጠይቁ ሰዎች እያታለሉን ቢሆንስ ወዘተ የሚሉ ጥያቄዎች የቤተ ክርስቲያኑ ነገር እንደ እግር እሳት ሲያንገበግበው ከሰነበተ ምእመን የሚጠበቅ ውስጣዊ ጥያቄ ነው፡፡ ቅዱስ ሲኖዶስም ተግባራዊ ምላሽ እንደሚሠጥበት እንጠብቃለን::

መንግሥትን እንዴት ማመን እንችላለን? ለሚለው እኛ ሁልጊዜም የምናምነው እግዚአብሔርን ብቻ ነው፡፡ እርሱ ደግሞ አምነነው አሳፍሮን አያውቅም፡፡ በእርግጠኝነት መናገር የሚቻለው ስለ እግዚአብሔር ብቻ ነው:: በእግዚአብሔር መንፈስ ይመራሉ ብለን የምናምንባቸው አባቶቻችንንም እስከ አሁን ያዘዙንን ስናደርግ ሰንብተን ከዚህ በኋላ አባትነታቸውን ብንጠራጠርና በስሜታዊነት ብንሳደብ ‘ለሦስት ሳምንታት ቅዱስ ሲኖዶስ ክብርና ልዕልና ተነካ ብለን የጮኽነው ለምን ነበረ? ያስብላል፡፡

በእርግጠኝነት መናገር የምንችለው ከመንግሥት ጋር በከፍተኛ ውጥረት ውስጥ ሆነው ‘ቤተ ክህነቱ ሊወረር ነው ፣ አባቶች ሊታፈኑ ነው’ የሚል የሚያሸብር ዜና እየሰሙ በዚያ የጭንቅ ሰዓት ሕይወታቸውን አደጋ ላይ ጥለው የሰነበቱ አባቶች ፣ ጠባቂዎች ቢነሡባቸው እግዚአብሔርን ጠባቂያችን ብለው ስለ ሕገ ቤተ ክርስቲያን መጠበቅ በድፍረት የቆሙ ሊቃነ ጳጳሳት ዋናው ችግር ከተፈታ በኋላ በሚኖረው ሒደት ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን አሳልፈው ይሠጣሉ ብሎ መደምደም የሚያሳዝን ነው፡፡

አባቶችን ላታልላቸው ብሎ እንደ ሀናና ሰጲራ መንፈስ ቅዱስን ሊያታልል የሚሞክር ሰው የሚያታልለው ራሱን ነውና ይቀሰፋል፡፡ አርዮስ አባቶችን አታለልኩ ብሎ ሳያምን አምኛለሁ ብሎ የደረሰበትን ስንማር ኖረናልና ቤተ ክርስቲያንን ሊያታልል የሚሞክር ሁሉ በእርሱ እንደሚብስበት እናምናለን፡፡ ስለዚህ ተመለሱ በሚል ዜና እንደጠፋው ልጅ ወንድም አኩራፊ ፣ እንደ ሀናንያ ተጸያፊ ሳንሆን የእውነት ያድርገው ብለን በመጸለይ እንበርታ:: የነነዌ ለቅሶ መልስ ሲያገኝ ካኮረፍን ኩርፊያችን የዮናስ ኩርፊያ ይሆንብንና ትርፉ ቅላችንን ማድረቅና በፀሐይ መለብለብ ይሆናል:: (ዮና. 4:1-11) ልጅ ጠፍቶ ሲገኝ ደስ የሚል ከሆነ አባት ጠፍቶ ሲገኝ እንዴት ደስ አይልም? እንደ ልጅነታችን ዳግም አባት አልባ እንዳንሆን መለመን ነው እንጂ::
430 views08:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ