Get Mystery Box with random crypto!

ግጻዌ

የቴሌግራም ቻናል አርማ gitsawe — ግጻዌ
የቴሌግራም ቻናል አርማ gitsawe — ግጻዌ
የሰርጥ አድራሻ: @gitsawe
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 11.19K
የሰርጥ መግለጫ

የየዕለቱን ግጻዌ የቅዳሴ ጊዜ ምንባባትና ምስባክ በዚህ ቻናል ያገኛሉ።

Ratings & Reviews

5.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2023-06-01 21:03:42 የ ምስራች ለ ተዋህዶ ልጆች በሙሉ!

መንፈሳዊ የዜማ መሳርያዎች መማር ይፈልጋሉ ?

 
የ ምስራች ለ ተዋህዶ ልጆች በሙሉ!

መንፈሳዊ የዜማ መሳርያዎች መማር ይፈልጋሉ ?

 
እምቢልታ መንፈሳዊ የዜማ መሳርያዎች  ማሰልጠኛ  ተቋም 
➜  በገ ና
➜  ክራር
➜ መሰንቆ
➜ ዋሽንት

   በሚፈልጉት ቀን እና ሰዓት  እንዲሁም በግል ቤት ለቤት  እናስተምራለን ! በተጭማሪ  ጥራት ያላቸው  የበገና , የክራር , መሰንቆ እንሸጣለን እናከፋፍላለን የክራር የበገና የመሰንቆ ቦርሳ እኛ ጋር ያገኛሉ


አድራሻችን  -  ጀሞ 1 ሩት የገበያ ማዕከል
                            
         Tel.  0995975237
                     
                     

.
1.5K views18:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-23 20:49:43 የ ምስራች ለ ተዋህዶ ልጆች በሙሉ!

መንፈሳዊ የዜማ መሳርያዎች መማር ይፈልጋሉ ?

 
የ ምስራች ለ ተዋህዶ ልጆች በሙሉ!

መንፈሳዊ የዜማ መሳርያዎች መማር ይፈልጋሉ ?

 
እምቢልታ መንፈሳዊ የዜማ መሳርያዎች  ማሰልጠኛ  ተቋም 
➜  በገ ና
➜  ክራር
➜ መሰንቆ
➜ ዋሽንት

   በሚፈልጉት ቀን እና ሰዓት  እንዲሁም በግል ቤት ለቤት  እናስተምራለን ! በተጭማሪ  ጥራት ያላቸው  የበገና , የክራር , መሰንቆ እንሸጣለን እናከፋፍላለን የክራር የበገና የመሰንቆ ቦርሳ እኛ ጋር ያገኛሉ


አድራሻችን  -  ጀሞ 1 ሩት የገበያ ማዕከል
                            
         Tel.  0995975237
                     
                     

.
2.1K views17:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-20 23:46:29 የ ምስራች ለ ተዋህዶ ልጆች በሙሉ!

መንፈሳዊ የዜማ መሳርያዎች መማር ይፈልጋሉ ?

 
የ ምስራች ለ ተዋህዶ ልጆች በሙሉ!

መንፈሳዊ የዜማ መሳርያዎች መማር ይፈልጋሉ ?

 
እምቢልታ መንፈሳዊ የዜማ መሳርያዎች  ማሰልጠኛ  ተቋም 
➜  በገ ና
➜  ክራር
➜ መሰንቆ
➜ ዋሽንት

   በሚፈልጉት ቀን እና ሰዓት  እንዲሁም በግል ቤት ለቤት  እናስተምራለን ! በተጭማሪ  ጥራት ያላቸው  የበገና , የክራር , መሰንቆ እንሸጣለን እናከፋፍላለን የክራር የበገና የመሰንቆ ቦርሳ እኛ ጋር ያገኛሉ


አድራሻችን  -  ጀሞ 1 ሩት የገበያ ማዕከል
                            
         Tel.  0995975237
                     
                     

.
237 views20:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-17 08:03:53 የ ምስራች ለ ተዋህዶ ልጆች በሙሉ!

መንፈሳዊ የዜማ መሳርያዎች መማር ይፈልጋሉ ?

 
የ ምስራች ለ ተዋህዶ ልጆች በሙሉ!

መንፈሳዊ የዜማ መሳርያዎች መማር ይፈልጋሉ ?

 
እምቢልታ መንፈሳዊ የዜማ መሳርያዎች  ማሰልጠኛ  ተቋም 
➜  በገ ና
➜  ክራር
➜ መሰንቆ
➜ ዋሽንት

   በሚፈልጉት ቀን እና ሰዓት  እንዲሁም በግል ቤት ለቤት  እናስተምራለን ! በተጭማሪ  ጥራት ያላቸው  የበገና , የክራር , መሰንቆ እንሸጣለን እናከፋፍላለን የክራር የበገና የመሰንቆ ቦርሳ እኛ ጋር ያገኛሉ


አድራሻችን  -  ጀሞ 1 ሩት የገበያ ማዕከል
                            
         Tel.  0995975237
                     
                     

.
787 views05:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-09 14:44:34 እመቤቴ ሆይ አንቺ ኑሮ የጀመርሽው ገና በሥላሴ ልቡና ውስጥ ነበር፡፡ በዛሬው ዕለት የሥላሴ ሃሳባቸው ተከናወነ፡፡ የነቢያት ትንቢታቸው የመላዕክት እህታቸው እመቤታችን ሆይ ተስፋችን በአንቺ ተፈፀመ፡፡ " ከገነት በተሰደደ ጊዜ የአዳም ተስፋው አንቺ ነሽ" እንዲል አንቺን ተስፋ አድርጎ ከገነት የወጣው አዳም ዛሬ ተስፋው ለመለመ፡፡ የቅዱሳን እናትና አባትሽን ሐና እና ኢያቄምን ልጅ በማጣት ያዘኑትን ኃዘን ብቻ ሳይሆን እኛም ገነትን በማጣት የተሰቃየነውን ስቃይ በልደትሽ አጠፋሽልን፡፡

ፀሐይን ያስገኘ አምላክ የወጣብሽ ምሥራቅ፣ እውነተኛው የሕይወት ውኃ የፈለቀብሽ ንጹሕ ምንጭ፣ ሁሉንም በቸርነቱ የሚያስጠልለው ዛፍ የበቀለብሽ ለምለም መሬት፣ ሥጋውና ደሙን ያስገኘሽ አማናዊት መቅደስ ያንቺን ልደት በምን መስለን እንናገረው? ያንቺን ልደት ስናስብ የሚሰማንን እውነተኛ ደስታስ በምን እንግለጸው?

ፍጥረት ሁሉ በደስታ የደነገጠብሽ የምሥራች ሆይ እስቲ ከወንድሞችሽ መላዕክት አንዱን ላኪና ያንቺን ልደት ያብስረን፡፡ ቅዱስ ገብርኤል እንኳን ሊያበስርሽ ተልኮ ሰላምታ ለማቅረብና ያንቺን ክብር ለመናገር ቃላት አጥሮት ሲጨናነቅ አይተነዋል፡፡ አሁንስ ስለእኔ ልደት ንገራቸው ብለሽ ብትልኪው መቶ ምን ይለን ይሆን?

እመቤቴ ሆይ የሰላም ባለቤት ሰላማዊ ኢየሱስ ክርስቶስን ያስገኘሽ አንቺ ነሽና ከአንቺ ሌላ የሰላም ሚኒስቴር አናውቅም፡፡ " ሕሙማነ ሥጋን በተአምራት፤ ሕሙማነ ነፍስን በትምህርት" የሚያክም እውነተኛው ሐኪምን ያስገኘሽ አንቺ ነሽና ከአንቺ ሌላ ጤና ሚኒስቴር አናውቅም፡፡ ዛሬ የዓለም ጤናና ሰላም ሚኒስቴር የተመሰረተችበት ቀን ነው፡፡

ወላዲተ አምላክ ሆይ እንዴት ነው ታድያ የሰማይ ቤት ጉድጉድ? የአንቺን ልደት ለማክበር ቅዱሳን መላዕክት ፣ ፃድቃን ሰማዕታት በሰማይ ቤት እንዴት ተጨንቀው ይሆን? ምንስ ስጦታ ሊሰጡሽ አሰቡ? ቢያስቡስ ላንቺ ያልተሰጠሽ ምን አለ? ግን ደግሞ ልጅሽ በልደትሽ ቀን " ምን ላድርግልሽ?" ብሎ መጠየቁ አይቀርም፡፡ ታድያ የመስቀል ስር ስጦታዬ እመቤቴ ሆይ ልጅሽ ክርስቶስ " እነሆ ልጅሽ" ብሎ በመስቀል ስር እኔንም ላንቺ አደራ እንደሰጠ እንዳትረሺ፡፡

እመቤቴ ሆይ አንቺ በፍጹም ንጽሕና ተወልደሽ እንደ ልጅሽ አርገሻል፡፡ እኔ ግን በኃጢአት ታስሬ በልጅሽ ሥጋና ደም መወለድ አቅቶኛል፡፡ እናቴ ሆይ አንቺስ ከወለድሽ በፊትም በኋላም በፍጹም ድንግልና ኖረሸል፡፡ እኔ ግን ዘወትር በኃጢአት እየረከስኩ " አመንዝራውን ድንግል" የሚያደርገውን ቁርባን ተቀብዬ ድንግል መሆን አቅቶኛል፡፡ ወላዲተ አምላክ እባክሽን እኔም ልደቴን ከአንቺ ጋር አከብር ዘንድ ልጅሽ ከኃጢአት አንጽቶ ዳግም በቅዱስ ሥጋውና ደሙ እንዲወልደኝ ለምኝልኝ፡፡

እንኳን ለእመቤታችን፣ ለእናታችን፣ ለአማላጃችን፣ ለወዳጃችን፣ ለስጦታችን፣ ለምርኩዛችን፣ ለመመኪያችን፣ ለአጽናኛችን፣ ለደስታችን፣ ቅድስት ብጽዕት ክብርት ድንግል ማርያም ልደት በሰላምና በጤና አደረሳችሁ፡፡
ዓዲ
እንኳን ለልደታችን አደረሰን፡፡ ልደቷ ልደታችን ነውና፡፡

ዲያቆን ዮሐንስ ደረጀ
ግንቦት 01/2013 ዓ.ም
አዲስ አበባ
https://t.me/dnJohannes
632 views11:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-09 00:48:53 እንኳን ልጅሽ ማረችሽ
............................................................

በሰው ልጅ ከንፈር ላይ በጣም የሚያምር ቃል "እናት" የሚለው ቃል ሲሆን በጣም የሚያምር ጥሪ ደግሞ "እናቴ" የሚለው ነው። "እናቴ" በተስፋ እና በፍቅር የተሞላ፣ ከልብ ጥልቅ የሆነ ጣፋጭነት ያለው ከማር ይልቅ የሚጣፍጥ ቃል ነው።

ከሁሉ ይልቅ ግን አምላክ "እናቴ" ሲል በጣም ይደንቃል። እኛም የወለደችንን "እናቴ" እንላለን አምላክም የወለደችውን "እናቴ" ይላል እንዲያው ሌላ ቃል በኖረ እና ከፍ ከፍ አድርገን ለእርሷ ሌላ የእናትነት ስም ባወጣንላት፤ ለነገሩ እርሱ አማላኳ እና ልጇ ከፍ ከፍ ያደረጋት እኛ ምን ልንጨምርላት? ግን ቢሆንም እሷን ከፍ ከፍ ከማድረግ አንቦዝንም ያሉንን ቃላት ሁሉ እንጠቀማለን ምክንያቱም እናት ሁሉም ነገር ነች። እሷ በሀዘን መጽናኛችን ናት ፣ በመከራ ውስጥ ያለችን ተስፋ እና ጥንካሬያችን ናት፣ እሷ የፍቅር፣ የምህረት፣ የህይወት እና የይቅርታ ምንጭ ነች።

በ1ኛ ቆሮንጦስ መልዕክቱ ቅዱስ ጳውሎስ እንደተናገረው "ተፈጥሮ እንኳ አያስተምራችሁምን?" እናትነትን ተፈጥሮም ውስጥ እናየዋለን ፀሐይ ልክ እናት ልጇን እንደምትመግብ ምድርን በብርሃን ትመግባታለች ለህልውናዋ የሚሆኑትን ንጥረ ነገሮችም ትለግሳታላች። የባሕርን ዝማሬና የወፎችንና የወንዞችን መዝሙር ምድርን ሲሞላ ልክ ልጇ እንደሚቦርቅ ህፃን ፍዝዝ ብላ ታያታለች።

ይህች ምድርም ብትሆን የዛፎች እና የአበባዎች እናት ናት። በውስርጧ ያለውን ጥረነገር ያለ ስስት ትለግሳቸዋለች፣ ፍሬ ያፈሩ ዘንድ፣ አበባን ያፈኩ ዘንድ፣ እናታቸውን በልምላሜ ካባ ያስዉቡ ዘንድ ትንባከባቸዋለች የእነሱ መለምለም እና መፍካት ለእናታቸው ውበትን ያላብሳታል። ከአምላክ በሚሰጣት ጠል እና በላዩአም በመላት ወንዞች እና ምንጮች ልጆቿን ጡት ታጠባለች ታረሰርሳቸዋለች። ዛፎቹ እና አበቦቹም ቢሆኑ ለታላቅ ፍሬዎቻቸው እና ዘሮቻቸው ደግ እናቶች ናቸው።

እናትነት በውበት እና በፍቅር የተሞላ ዘላለማዊ መንፈስ ነው። እና እኚህ ሁሉ እናቶች አምላካችን የሚሉትን እርሷ ልጄ ብላ የምታየው እናት፣ እርሱ አለማትን የሚመግበውን የመገበች እናት፣ እርሱ ሁሉን ፈጥሮ ሲያበቃ ለሰውነቱ እድገት የሚሆነውን ወተት የመገበችው ድንግል እናት፣ እርሱ ፍጥረትን እንደ ሰጎን ዐይኑን ሳይነቅል በስስት የሚመለከተንን እኛን በስስት አይኗን ሳትነቅል በምድር ለይ በቆየበት ጊዜያት በሙሉ የተመለከተች እናት፣ ገና አይኑን ሲገልጥም ነፍሱን ከሥጋው በፈቃዱ ሲለይም የተመለከታት እናት፣ እኛ አምላካችን፣ አባታችን እያልን አንገታችንን ወደ ሰማይ አንጋጠን የምንለምን እርሷ ግን አለምን በመዳፉ የጠቀለለውን በጨርቅ ጠቅልላ በእቅፏ ይዛ ልጄ ብላ አይን አይኑን በፍቅር እየተመለከተች የምታናግረው እናት። ከቶ ለዚህች እናት ምን የሚል ስም እናወጣ ይሆን?

ሊቁ ቅዱስ ኤፍሬም "ጌታ ሆይ እናትህን ማን ብለን እንጥራት? እናት ብቻ እንዳንላት ድንግል ሆና አገኘናት ፣ ድንግል እንዳንላት ልጅ ታቅፋ አየናት። ጌታ ሆይ እናትህን ለመጥራት እንዲህ የሚያስቸግር ከሆነ አንተን ከቶ ምን ብለን እንጠራሃለን?"በማለት በምን ስም እንደሚጠራት እንዲህ ከተጨነቀ እኛ ከቶ ማን ብለን ልንጠራት እንችላለን?

ጠቢቡ ሰሎሞንም “፤ርግቤ መደምደሚያዬም አንዲት ናት ፤ለእናትዋ አንዲት ናት ለወለደቻትም የተመረጠች ናት። ቈነጃጅትም አይተው አሞገሱአት፥ ንግሥታትና ቍባቶችም አመሰገኑአት። ፤ይህች እንደ ማለዳ ብርሃን የምትጐበኝ፥ እንደ ጨረቃ የተዋበች እንደ ፀሐይም የጠራች፥ ዓላማ ይዞ እንደ ተሰለፈ ሠራዊት የምታስፈራ ማን ናት?” እያለ በትንቢት መነጽር ተመልክቷት በመደነቅ የዘመረላትን ብላቴና ከቶ እኛ ማን ብለን ስም እናውጣላት?

"እግዚአብሔር መረጠሸ፥ ልቶኚው እናቱ
ይኸው ሊፈፀመ፥ የአዳም ትንቢቱ
የሔዋን ተስፋዋ፥ የአዳም ዘር ህይወት
የእያቄምወ ሀና፥ የፍሬ በረከት
ኪዳነምህረት የድህነታችን ምክንያት
ድንግል ተወለደች፥ የክርስቶስ እናት"
እናም ለእርሷ "የአምላክ እናት" ከመባል ሌላ ምንም ክብርን ይሚያላብስ ስም አላገኘንምና በአምላክ ስሞች ለይ ሁሉ "እመ" እየጨመርን እንጠራታለን፡

እመ አምላክ

እመ ፍቅር

እመ ብርሃን

እነሆ ስለዚህች ብላቴና የተነገረላት ነገር ይገለጥልን ዘንድ እናትና አባቷ ማን ብለው ይጠሯት እንደሆነም እንሰማ ዘንድ ኑ ወደተቀደሰዉ ተራራ እንሂድ።

ኢትዮጵያውያን ሊቃውንት አባ ጽጌ ድንግልና አባ ገብረ ማርያም ዘደብረ ሐንታ በማሕሌተ ጽጌ የነገረ ማርያም መጽሐፋቸው "ትንቢት ከተነገረለት ከአንበሳ ጉድጓድ፤ ድንግል ሙሽራ በተገኘሽ ጊዜ የንጉሦች ንጉሥ የሰሎሞን ልቡ እንደተደሰተ፤ ደስ ባላቸው በመላእክት አንድነት ፊት ታምርሽን እየተናገርኊ የሐና አበባ ማርያም እዘምርሻለኊ፤ ወተትን ጠብቶ እንደሚዘልል እንቦሳም ዝለል ዝለል ይለኛል" በማለት ሰሎሞን ስለ ቅድስት ድንግል ማርያም ልደት የተናገረው ትንቢት ፍጻሜውን አግኝቶ ታላቅ ደስታን ለኹላችን እንደሰጠን አብራርተው እንደገለጡ፤

እነሆ ለሕዝቡ ሁሉ የሚሆን ታላቅ ደስታ የምሥራች፤ ዛሬ በሊባኖስ ተራራ የመድኃኒት እናት እርሷም እመ አምላክ የሆነች ተወልዳልናለችና። ይህም ምልክት ይሆንልናል ሕፃኗን ተጠቅልላ በተራራው ጫፍ ተኝታ እናገኛታለን፤ ፍጠኑ ወደ ተራራው እንውጣ።

እነዚያን ደጋግ ቅዱሳን ባልና ሚስት ሃና እና እያቄምን እናይ ዘንድ፣ እነሆ መካኒቱ ቅድስት ሃና ሰባቱ ሰማያትን ሰንጥቃ መጥታ በማሕፀኗ ስታድር ያየችትን ፀዓዳ ርግብ የሆነችውን ሕፃን እናይ ዘንድ ወደ ተቀደሰው ድንኳን እንሂድ። እነሆ ቅዱሱ እያቄም ከሰባተኛው ሰማይ ወርዶ በራሱ ላይ ሲቀመጥ ያየውን ነጭ ዖፍ ምስጢር ይገለጥልን ዘንድ ፍጠኑ እንሂድ ወደ ተራራው እንውጣ። ከመላእክቱ ጋር እናመሰግን፥ እናደንቅም።

ህጻኗንም በእናቷ እቅፍ ከአባቷ ጋር ባገኘናት ጊዜ ልክ እንደ ሊቃውንቱ እጅ ነስተን "እነሆ ውዲቷ ሐና አንቺን የፀነሰችባት የደስታ ቀን ምን ያኽል የተባረከች የተቀደሰች ናት፤ አረጋዊው ኢያቄምም ለሕይወት አንቺን ያፈራባት ቀን ምን ያኽል የተባረከች የተቀደሰች ናት፤ አንዲቱ ርግቤ ማርያም አንቺ የዓለሙ ኹሉ መድኀኒት ኾነሻልና ታምርሽን አመሰግናለኊ" በማለት ምስጋናን እናቅርብ።

፤እነሆ ከዕሴይ ሥር የወጣችውን በትር ከርሷም ያበበውን አበባ እናይ ዘንድ ኑ ፍጠኑ እንሂድ ወደ ተራራው እንውጣ። ክብር ለእግዚአብሔር በአርያም ይሁን ሰላምም በምድር ለሰውም በጎ ፈቃድ እያልን ከመላእክቱ ጋር እንዘምር። የእናታችንን የልደቷን ቀን ከእናቷ እና አባቷ ጋር በመሆን እናክብር።

አያታችንን እንኳን ልጅሽ ማረችሽ እንበላት።
"ዮም ፍሥሐ ኮነ በእንተ ልደታ ለማርያም፤ በማርያም ልደት ምክንያት ዛሬ ደስታ ሆነ!" (ቅዱስ ያሬድ)
"ይህች ዕለት ትልቅ ሕንፃ የታነጸበትና ፍጡር የፈጣሪ ማደሪያ ለመሆን የተዘጋጀባት ዕለት ናት" (ቅዱስ እንድርያስ)
ዮርዳኖስ.21

ግንቦት 01, 2015 ዓ.ም

አዲስ አበባ
873 views21:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-08 07:04:15 ከበዓል በኃላ ለሰርጎ , ለልጆቾ ክርስትና የዲኮር ስራ ማሰራት ይፈልጋሉ ?



ለ ሰርግ                            ለ ክርስትና
ለ ልደት                            ለ ቀለበት
ለ ገዓት                             ለ ሽምግልና
ለ ተማሪዎች ምረቃ           ለ ልጆች ልደት
ለ ቤት ምርቃት                   ለ ሆቴል ምረቃ
ለ ስብሰባ አዳራሾች          ለ ቤተሰብ ኘሮግራሞች
ለ ሰርግ ለመኪና ዲኮር
በ ቤተክርስቲያን ስርዓት ለሚፈፀሙ ሰርጎች እና ኘሮግራሞች

ለተለያዮ ዝግጅቶችም ጭምር የተለያዮ የዲኮሪሽን ስራዎችን እንሰራለን እንዲሁም የተለያዮ የዲኮር እቃዎችን እናቀርባለን !
       

     
              ይህን ይጫኑት  ...  ይህን ይጫኑት

█▓▒░        ►𝗢𝗽𝗲𝗻◄░►𝗢𝗽𝗲𝗻       ▒▓█
█▓▒░         ►𝗢𝗽𝗲𝗻◄░►𝗢𝗽𝗲𝗻      ▒▓█
█▓▒░         ►𝗢𝗽𝗲𝗻◄░►𝗢𝗽𝗲𝗻      ▒▓█
█▓▒░        ►𝗢𝗽𝗲𝗻◄░►𝗢𝗽𝗲𝗻       ▒▓█


Tel .   +251961064953
                 +251703504953
.
819 views04:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-07 20:20:51
ብዙዎቻችን በምንወዳቸው ሰዎች የልደት ቀን ፍቅራችንን በውብ ቃላት ሰድረን ጽፈን እንልክላቸዋለን፥ መልካም ምኞታችንን እናዥጎደጉድላቸዋለን። ታዲያ የመወለዷ ደስታ ለወላጆቿ እና ለወዳጆቿ ብቻ ሳይሆን ለአዳም ዘር በሙሉ ለሆነው ለእመቤታችን ልደት ምን ልትጽፉላት አሰባችሁ? ምን ልትሏትስ ትወዳላችሁ? ልደቷ ልደታችን ለሆነው ንጽሕት ምኞታችሁ ምንድነው? እኔ ውለታዋ የከበደኝ ልጇ የተወለደችውን ወላዲተ አምላክ በልደቷ ስዕል ፊት ቆሜ እያየኋት ይህንን ጻፍኩላት:

"የተወለድሽ እናት ሆይ ለእኛ የተሾሙልን ብጹዓን ሊቃነ-ጳጳሳት በሥዕልሽ ፊት ቆሙ፥ ለመኑሽም አላፈሩም፤

ቅድስት ሆይ አባቶቻችን ካህናት በሥዕልሽ ፊት መልካም መአዛ ያለውን ዕጣን አጠኑ ፥ ነግህ ሰርክ ሳይሉ ለምሥጋናሽ ተፋጠኑ አላፈሩም፤

ድንግል ሆይ ከእኛ ፊት ሐዘናቸውን እየደበቁ አባቶቻችን በደጀ ሰላምሽ በሥዕልሽ ፊት አነቡ አንቺም አጽናናሻቸው፤

ማርያም ሆይ በእንብርክክ እየዳሁ እጃቸውን ዘርግተው እናቶቻችን በደጃፍሽ ተማጸኑሽ፥ የእናት ሆድ አያስችል ነውና ብሒሉ የለመኑትን ከሆድሽ ፍሬ ዘንድ አሰጠሻቸው፤

እኔም ይኸው በመቅደስሽ በሥዕልሽ ፊት ቆምኩ። የጳጳሳቱ የረቀቀ ክህነት፣ የካህናቱም ትጋት፣ የአባቶቼ ፍቅር፥ የእናቶቼም የዋሃት የለኝም፥ አንቺን ግን ተስፋ አደርጋለሁ።

ሕጻን እና ሽማግሌ፥ ድሃና ሀብታም ብሎ የማይለይ የተአምርሽን በረከት ለእኔም ለባርያሽ ታደርጊልኝ ዘንድ በሊቃውንቱ ውብ ዜማ "በሥዕልሽ ፊት መቆምን አላፍርም" ብዬ ዘወትር በመቅደስሽ አውጃለሁ።"

ንጽሕት ሆይ ልደት የለንም እኛ፥ ልደትሽ ነው ልደታችን!!

ዲያቆን እስጢፋኖስ ግርማ
850 views17:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-06 04:06:38 ከዓመት እስከ ዓመት ግርግር በማያጣትና ሁሌም በሰውና በገበያተኛ በተጨናነቀችው ኢየሩሳሌም ውስጥ እየተጓዝን ነው:: ጥንታዊትዋ የኢየሩሳሌም ከተማ በአሁኑ ሰዓት በአራት ሩቦች ተካፍላ ትተዳደራለች:: የክርስቲያን እርቦ ፣ የሙስሊሞች እርቦ ፣ የአርመኖች እርቦ እና የአይሁድ እርቦ ይባላሉ::

ለሦስቱ አብርሃማውያን እምነቶች (Abrahamic religions) ለአይሁዳዊነት ለክርስትናና ለእስልምና ትልቅ ፋይዳ ባላት ኢየሩሳሌም "አርብ አርብ" ብቻ ሳይሆን ሁሌም ሽብርና ግርግር አለ:: በሁሉም ሩቦች ተሳላሚዎች ፣ ጎብኚዎች ፣ ሻጮች ፣ ገዢዎሽ እስከ እኩለ ሌሊት ይርመሰመሳሉ::

ዘንድሮ እግር ጥሎኝ ከአንድ ወዳጄ ጋር በአይሁድ እርቦ (Jewish quarter) በኩል ሳልፍ አንድ ልብ የሚነካ ሥዕል ዓይኔ ውስጥ ገባ:: ሥዕሉን ሳይ ዕንባ በዓይኔ ሞላ:: የኢሳይያስ 53ቱን የሕማም ሰው ፣ የማይናገረውን በግ በአንገቱ የእሾህ አክሊል ጌጥ አድርገውለት እንዲህ ሆኖ ሳየው ችዬ የማላነበውን ኢሳይያስ 53 በሥዕል ሲያመጣብኝ ከማልቀስ ውጪ ምንም አቅም አልነበረኝም::

ነቢዩ ኢሳይያስ ሳይናገር በፊት የሚቀበለው እንደሌለ አውቆ "የሰማነውን ነገር ማን አምኖአል?" ብሎ የተጨነቀበትን ይህን አስጨናቂ ራእይ እንዴት እንረሳዋለን? ከኢትዮጵያዊው ጃንደረባስ በቀር ኢሳይያስ 53 ን አንብቦ "ማን አምኖአል?" (ሐዋ. 8:26) የእግዚአብሔር ክንዱ የተባለ ክርስቶስስ ለማን ተገልጦአል?

በግርፋቱ ብዛት ፊቱ በደም ተለውሶ "ባየነው ጊዜ እንወደው ዘንድ ደም ግባት የለውም" የተባለበትን ውበቱ ስለ እኛ የጠፋው የሕማም ሰው እንዴት ከሕሊናችን ተሰወረ?

"እርሱ ግን ስለ መተላለፋችን ቈሰለ፥ ስለ በደላችንም ደቀቀ፤ የደኅንነታችንም ተግሣጽ በእርሱ ላይ ነበረ፥ በእርሱም ቍስል እኛ ተፈወስን።ተጨነቀ ተሠቃየም በሸላቾቹ ፊት ዝም እንደሚል በግ እንዲሁ አፉን አልከፈተም" የሚለው ቃል ምንኛ ያስጨንቃል? ቆስሎ የሚፈውስ ታምሞ የሚያድን ታስሮ ነፃ የሚያወጣውን የእግዚአብሔር በግ ለመግለፅ ቃላት አቅም ቢያጥራቸው እንዲህ በብሩሽ ኃይል ተሥለው ሳያቸው ሁሉን ነገር ዘነጋሁት::

አንድ ልብሱ በቀለም ያደፈ ሰው በሥዕል ጋለሪው ደጃፍ ቁጭ ብሎ ይፈርማል:: እንደ መታደል ሆኖ ሰውዬው የሥዕሉ ባለቤት UDI MERIOZ ነበረ:: ቀርቤ ስለ ሥዕሉ የተሰማኝን ስነግረው እሱም ስሜቱ ተነካ:: "ይሄንን ሥዕል እኔ ብሥለውም የእኔ ፈጠራ አይደለም:: ሸራውን ወጥሬ በቀለም ላይ የሠራሁት እኔ ነኝ:: ነገር ግን ከመሣሌ በፊት በተደጋጋሚ በሕልሜ አየው ነበር:: የሣልሁትም ያየሁትን ነው" አለኝ:: ሥዕሉንም ፈርሞ ለእኔና ለወዳጄ ሠጠን::

ቅዱስ ኤፍሬም "ጌታ ሆይ ረዥሙን ሥቃይህን ማን ሊገልጸው ይችላል?" እንዳለው የጌታን መከራ የሚገልፅ አንደበት የሚሥለው ብሩሽ ባይኖርም ለአፍታ ግን እንዲህ በየሰዉ ላይ ባሳረፈው ጸጋ ሕማሙን ያስታውሰናል::

ይህ የበገና መዝሙር ግጥም ግን ከሕሊናዬ መጣ

"ያ ሁሉ መከራ እንዴት ይግባ ልቤ
አልበጠስ አለኝ የኃጢአት መረቤ

ተው ልቤን ስበረው ልመንህ አጥብቄ
መቼ ሕይወት ሆነኝ ቃልህን ማወቄ
ቃሉን ተናጋሪ ምግባር የሌለኝ
ተገርፎአል ተሰቅሎአል የምል ብቻ ሆንኩኝ" (ዘማሪት አዳነች አስፋው)

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ሚያዝያ 2015 ዓ.ም.
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
1.2K views01:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-30 12:41:28

2.2K views09:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ