2022-08-24 21:14:55
#የሶስት_ጠቢባን_አባባሎች
“ለሶስት ችግሮች ሶስት ሃሳቦችን ትዕዛዝ አድርገን መያዝ ይገባናል፣ እነዚህም፡-ከረጅም ጊዜ በፊት በእኔ ላይ በነበረው ያ ግብ፣ በእግዚአብሔርና በእጣ ፈንታ ተማምኛለሁ፡፡
አልወድቅም እከተላለሁ፣ ቁርጠኝነቴ ቢደክም እንኳን መጓዜን እቀጥላለሁ፡፡”
#ክሊያንተስ
“የሚያስፈልገውን ብቻ የያዘ እሱ ጠቢብ ነው፤ በአማልክቱም ተባርኳል።”
#ኢዩሪፒደስ
“አማልክቱን የሚያስደስት ከሆነ፣ ይሁን፡፡ ምናልባት ይገድሉኝ ይሆናል፣ ግን ሊጎዱኝ አይችሉም፡፡”
#ፕሌቶ
እነዚህ በኤፒክቴተስ ስራ ውስጥ የተጠናቀሩ ሶስት ጥቅሶች፣ ከታሪክ ባሻገር በጥበብ ውስጥ የመቻቻል፣ እንደ ሁኔታው የመሆንና በመጨረሻም የመቀበልን ጭብጥ የሚያሳዩ ናቸው፡፡
ክሊያንተስና ኢዩሪፒደስ መድረሻና እጣ ፈንታን መቀበልን ቀላል ለማድረግ የሚረዱ ሀሳቦች አድርገው ያቀርባሉ፡፡ አንድ ሰው በእግዚአብሔርም ይሁን በአማልክት ላይ ታላቅ ወይም ከፍተኛ የሆነ እምነት ካለው፣ ከእቅዱ በተቃራኒ የሚባል ነገር የለም፡፡
በአምላክ ባታምንም እንኳን፣ በተለያዩ የዩኒቨርስ ህግጋት ወይም በሕይወት ኡደት እንኳን ጥቂት ምቾት ልታገኝ ትችላለህ፡፡ በእኛ ላይ እንደ ግለሰብ የሚከሰተው ነገር በዘፈቀደ የሚሆን ወይም የሚያናድድ ወይም ጨካኝ ወይም ሚስጥራዊ ሊመስል ይችላል፤ እይታችን በትንሹም እንኳን በሚገለጥበት ጊዜ ግን እነዚህ ሁኔታዎች እንዲያውም ፍጹም በሆነ ሁኔታ ትርጉም ያላቸውና ስሜት የሚሰጡ ሆነው እናገኛቸዋለን። መጥፎውም የሆነው ለምክንያት ነው።
#ዛሬ_ይህንን_እይታ_እንለማመድ፡፡ የተፈለገም ይሁን ያልተጠበቀ ያ ሁኔታ እንዲሆን የታቀደ ነው። በተለይ በአንተ ላይ እንዲሆን የተፈቀደ እንደ ሆነ አስመስል፡፡ እንደዚያ ከሆነ እና የሆነው ሁሉ መሆኑ ካልቀረ እጣፈንታህን አትታገለውም፣ ትታገለዋህ?
@yederasiyanbet
2.3K viewsFellyNova/ፌሊኖቫ, 18:14