Get Mystery Box with random crypto!

FastMereja.com

የቴሌግራም ቻናል አርማ fastmereja — FastMereja.com F
የቴሌግራም ቻናል አርማ fastmereja — FastMereja.com
የሰርጥ አድራሻ: @fastmereja
ምድቦች: ዜና , ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 36.80K
የሰርጥ መግለጫ

FastMereja.net

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 12

2023-05-09 16:59:07
#ተያዘች
ሁለት ህፃናትን በአሰቃቂ ሁኔታ የገደለችው ነጋሴ ከበደ በሸገር ከተማ አስተዳደር ቡራዩ ክ/ከተማ ከከታ ሳንሱሲ ጫካ ውስጥ በህብረተሰቡ ትብብር በህግ ቁጥጥር ስር ውላለች።

@fastmereja
8.1K views13:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-09 15:28:28 ፈተና ከበደኝ ያለው ተማሪ ራሱን አጠፋ ሲል ደብረማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ገለፀ!
#FastMereja
በደብረማርቆስ ዩኒቨርሲቲ የአንደኛ ዓመት የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪ የነበረው ተማሪ አበባው ስንሻው መጸዳጃ ቤት ውስጥ ገብቶ የመጸዳጃ ቤቱን በር በመቆለፍ በራሱ ቀበቶ ራሱን አጥፍቶ መገኘቱን ነው ዩኒቨርሲቲው የገለፀው።

ተማሪው እዚህ አሳዛኝ ውሳኔ ላይ እንዲደርስ ያበቁትን ጉዳዩች ብሎ ዩኒቨርሲቲው ሲገልፅ ፈተና ከበደኝ በሚል ሲጨናነቅ እንደነበር መረጃዎች ያሳያሉ ግን ተጨማሪ ማጣራት ያስፈልጋል ተብሏል።

@fastmereja
8.0K views12:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-08 12:24:17
በትግራይ ክልል በሳምሬ ወረዳ አምዲ ወያነ ክፍለ ከተማ ከ20 በላይ ሰዎች በረሃብ መሞታቸውን ተጎጂዎችና ነዋሪዎች ተናገሩ። ችግሩ ወደ ሌሎች ጣቢያዎችም እየተዛመተ መሆኑን የገለፁት ኃላፊው ለጋሾች አስቸኳይ ሰብዓዊ እርዳታ እንዲያደርጉ አስተዳደሩ ጥሪ ማቅረባቸውን DW ዘግበዋል።

@fastmereja
9.1K views09:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-07 11:28:01 በደቡብ አሪ ወረዳ አርሶ አደርና በሳላማጎ ወረዳ አርብቶ አደር መሃል በተፈጠረዉ ግጭት ምክንያት ለሞቱ 8 ሰዎች ከደቡብ አሪ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ የተሰጠ መግለጫ

በደቡብ አሪ ወረዳ አርሶ አደርና በሳላማጎ ወረዳ አርብቶ አደር መሃከል በተፈጠረዉ ግጭት ምክንያት እስካሁን 7 የደቡብ አሪ ወረዳ አርሶ አደርና 1የዳሰነች ወረዳ ጸጥታዉን ለማረጋጋት የመጣ የፓሊስ አባል በሳላማጎ ወረዳ አርብቶ አደሮች ተገድለዋል።

ግጭቱ ከጀመረበት ቀን አንስቶ ሰዎች እየሞቱና የአካባቢዉ ሰላም ጠፍቶ ዘጎች በስጋት ዉስጥ መግባታቸዉን በመገንዘብ መንግስት ለማረጋጋት እየሰራ መሆኑ ይታወቃል በዝህም መሰረት የደቡብ አሪ ወረዳ ጸጥታ ኃይል የአጎራባች ወረዳዎች የፖሊስ አባላትና የክልሉ የጸጥታ ኃይል አብሮ በመተባበር ስያረጋጉ ከቆዩት አንዱ የዳሰነች ወረዳ ፓሊስ አባል ኮንስታብል ዮሐንስ ሎቱሊያ እና 7 አርሶ አደሮች በግጭቱ ምክንያት መሞታቸዉ ተገልጿል።

በመሆኑ የወረዳዉ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ግዳልቅ አልቅሚ እስካሁን ለሞቱት የወረዳችን አርሶ አደር ቤተሰቦችና የፓሊስ አባሉ ቤተሰቦች እንድሁም ለዳሰነች ወረዳ መንግስትና አጠቃላይ የሁለቱ ወረዳ ህዝቦች መጽናናትን ይመኛል።

እንደዝህ አይነት የእርስ በርስ ግጭቶች የዜጎች ህይወት ላይ ከፍተኛ ጉዳትና የህይወት እልቅትን የሚያስከትል በመሆኑ ሰዉ ከግጭት ይልቅ ችግርን በሰላማዊ መንገድ መፍታት እንድችል በመግለጽ በድጋሚ ለሟች ወዳጅ ቤተሰቦች መጽናናትን እንመኛለን ብለዋል።

@fastmereja
9.4K views08:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-07 10:16:28
በቡራዩ ሁለት ህጻናት በአሳዳጊያቸዉ በአሰቃቂ ሁኔታ ተገደሉ

በሸገር ከተማ አስተዳደር ቡራዩ ክ/ከተማ ከታ በተሰኘዉ አካባቢ እድሜያቸዉ የ 12 እና 4 አመት የሆኑ ወንድምና እህት በአሳዳጊያቸዉ በአሰቃቂ ሁኔታ መገደላቸውን ብስራት ራዲዮ ሰምቷል።

የ12 አመት ታዳጊ የሆነዉ ናኦል ጌቱ እና የ 4 አመቷ ህጻን ናኑ ጌቱ ከትናንት በስቲያ ሌሊት የቤት ሰራተኛ ሆና ወደ ቤታቸዉ በገባችና በኋላም ከሟቾቹ ህጻናት አባት ጋር የፍቅር ግንኙነት አላት በተባለችዉ "ነጋሴ ከበደ" ግድያ ተፈጽሞባቸዋል። ግለሰቧ ህጻናቱን በማረድ ከገደለች በኋላ አስክሬናቸውን በእሳት ማቃጠሏም ነዉ የተሰማዉ።

በሸገር ከተማ የቡራዩ ፖሊስ መምሪያ ሀላፊ ረዳት ኮሚሽነር ሽቱ ለኪሳ በተለይ ለብስራት ራዲዮ እንደተናገሩት ፤ ግለሰቧ ራስዋን "ትግስት" ብላ የምትጠራ ሲሆን ድርጊቱን ከፈጸመች በኋላ ከአካባቢዉ መሰወሯን ገልጸዋል።

"ነጋሴ ከበደ" አልያም ራሷን "ትግስት" የምትለዉ ግለሰብ ፤ ከሟች ህጻናቶቹ አባት ጋር ግንኙነት እንደነበራቸዉና ከሶስት ወራት በፊት ተጋጭተዉ ከቤት መዉጣቷን ረዳት ኮሚሽነር ሽቱ ተናግረዋል። በኋላም በእርሷ ቤተሰቦች አሸማጋይነት ሁለቱ ጥንዶች እርቅ አድርገዉ ወደ ቤት መመለሷን ይገልፃሉ።

ሆኖም አባት በከተማዉ ባለ የቄራዎች ድርጅት ሰራተኛ እንደመሆኑ እንደተለመደዉ ከትናንት በስቲያም በሌሊት ወደ ስራ ያቀናል። በዚህ ወቅትም ግለሰቧ ቤቱ መቃጠሉን ለአባት በስልክ ታሳዉቃለች። በኋላም አባት በቦታዉ ሲደርስ እና የህጻናቱ አስክሬን ሲገኝ ህጻናቱ ላይ ጉዳት እንደደረሰባቸዉ ይረጋገጣል።

ግለሰቧም ከአካባቢው ራሷን መሰወሯን እና ፖሊስም በፍለጋ ላይ መሆኑን በሸገር ከተማ የቡራዩ ፖሊስ መምሪያ ሀላፊ ረዳት ኮሚሽነር ሽቱ ለኪሳ ጨምረዉ በተለይ ለብስራት ራዲዮ ተናግረዋል።

Via ዳጉ_ጆርናል

@fastmereja
8.6K views07:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-06 14:45:09
የደብረታቦር ዩኒቨርሲቲ ከሃያ ሺህ ጫማ ከፍታ በላይ መጓዝ የሚችል ሮኬት አስወነጨፈ

የደብረታቦር ዩኒቨርሲቲ ዘንድሮ ለሁለተኛ ጊዜ "አፄ ቴዎድሮስ 2015" የሚል ስያሜ የተሰጣትን ሮኬት ከሃያ ሺህ ጫማ ከፍታ በላይ አስወንጭፎ ስኬታማ ሙከራ ማድረግ ችሏል፡፡

ዩኒቨርሲቲው በህዋ ምርምር ላይ ትኩረት በማድረግ ጋፋት የህዋ ምህንድስና ልማት ማዕከልንም አቋቁሞ የተለያዩ የምርምር ሥራዎችን በመስራት ላይ ይገኛል።

የማዕከሉ መሥራችና ሰብሳቢ አቶ በለጠ ጌታቸው፣ ሮኬት የማስወንጨፉ ሙከራ ከዚህ በፊት ከተሞከሩት የተሻለ ምርምር የተደረገበትና ለህዋ ሳይንስ የሚያስፈልጉ ቁሳቁሶችን ተሸክሞ መሄድ የሚያስችል ቴክኖሎጅ የተገጠመለት መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ኢትዮጵያ በህዋ ሳይንስ ዘርፍ ትኩረት ሰጥታ እየሠራች ነው ያሉት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶክተር አነጋግረኝ ጋሻው በዩኒቨርሲቲው ተማሪና ተመራማሪዎች የተሠራው ሥራ ኢትዮጵያ እንደሰለጠኑት ሀገራት በህዋ ምርምር የበኩሏን ድርሻ እንደምትይዝ ጅምሩን ያሳየ ነው ብለዋል።

በኢትዮጵያ ከሚካሄዱት የህዋ ሳይንስ ምርምሮች ውስጥ በሮኬት ሳይንስ ዘርፍ ደብረታቦር ዩኒቨርሲቲ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑንም ገልጸዋል።

የአማራ ሳይንስ እና ቴክኖሎጅ ኮሚሽን ኮሚሽነር ሳሉ አያሌው (ዶ.ር) እንደዚህ አይነት ሙከራዎች ኢትዮጵያ ወደፊት በዘርፉ ለምታደርገው ምርምር አጋዥ ናቸው ማለታቸውን አሚኮ ዘግቧል።

@fastmereja
8.9K views11:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-26 18:31:03 የኢትዮ ቴሌኮም ሽያጭ ሰራተኞች ቅሬታ እና የድርጅቱ ምላሽ
#FastMereja
ኢትዮ ቴሌኮም የሽያጭ ክፍል ሰራተኞች ከሚያዝያ 14/2015 ጀምሮ ማደያ በመገኘት ነዳጅ ለሚቀዱ ደንበኞች አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል ይሁንና አንድን ሰራተኛ ያለ ሽፍት እንዲሁም ያለ ምንም ተጨማሪ ክፍያ በአስገዳጅ ሁኔታ ከጠዋት 12:30—2:00 እየሰራን እንገኛለን" ሲሉ ቅሬታቸውን ለፋስት መረጃ ገልፀው ነበር የሰራተኞቹን ቅሬታ ይዘን የኢትዮ ቴሌኮም የሽያጭ ክፍል ከፍተኛ ኃላፊ የሆኑትን ፋስት መረጃ አነጋግሮ የሚከተለውን ምላሽ አግኝቷል

«ይህ ልዩ ፕሮግራም ህብረተሰቡን ለመደገፍ እና የመንግስትን አቅጣጫ ተግባራዊ ለማድረግ እየሰራን ያለነው፣ አዎ እውነት ነው ሁላችንም ከስራ ሰዓት ውጪ እየሰራን ነው ያሉት ኃላፊው ግን በማስገደድ ሳይሆን የትርፍ ሰአት ስራ ለሚሰሩት ማንኛውም ሰራተኛ የትርፍ ሰአት ክፍያ እንደሚከፈል ቃል ገብተናል።» የሚል ምላሽ ሰጥተውናል።

@fastmereja
3.7K views15:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-26 16:54:04
በሱዳን የተከሰተውን ግጭት በመሸሽ የተለያዩ ሀገር ዜጎች በመተማ ዮኋንስ ከተማ በኩል ወደ ኢትዮጵያ እየገቡ ነው።
#FastMereja
የተፈጠረውን አለመረጋጋት ሸሽተው የሚመጡ የተለያዩ የውጭ ሀገር ዜጎችን የምእራብ ጎንደር ዞን መተማ ዮኋንስ ከተማ በሰላም እያስተናገደች መሆኑ ተነገረ።

ሱዳን ላይ በተፈጠረው የውስጥ አለመረጋጋት ምክኒያት ጦርነቱን ሸሽተው ከካርቱም ወደ ጎረቤት ሀገር ኢትዩጵያ የሱዳን ዜጎችን ጨምሮ የ23 ሀገራት የተለያዪ ሃገራት ዜጎች እንደገቡና ወደ ሚፈልጉት አካባቢ እየሄዱ ይገኛሉ።

በዚህም የምዕራብ ጎንደሯ መተማ ዮሃንስ ከተማ እንግዶቿን እያስተናገደች ሲሆን በቀን ከ15-20 የሚሆኑ መኪናዎች ወደ ጎንደር እየሄዱ ይገኛሉ ። በዚህ የጦርነት ስጋት ሽሽትም ህፃናት፣ ሴቶች እና አቅመ ደካሞች ይገኙበታል።

የመተማ ዮሃንስ ከተማ አስተዳደር፣ የዞን ከፍተኛ አመራሮች፣ የሚመለከታቸው የፀጥታ አካላትም ዜጎች ያለምንም እንግልት ወደ ሚፈልጉት አካባቢ እንዲደርሱ ሰብአዊ ተግባራትን እያከናወኑ እንደሆነ የዞኑ ኮሙኒኬሽን ገልፇል።

@fastmereja
4.3K views13:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-26 12:35:30
ከኦሮሚያ ክልል የተውጣጡ የሀይማኖት አባቶች ከ10 ሺህ ኩንታል በላይ የምግብ ርዳታ መቐለ አደረሱ።
#FastMereja
የሀይማኖት አባቶች፣ አባገዳ፣ ሃዳ ስንቄ እና የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በህዝቦች መካከል ያለውን ግንኙነት ለማጠናከርና ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን 10 ሺህ ኩንታል ሩዝ ይዘው ነው መቐለ የሄዱት።

@fastmereja
4.8K views09:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-26 12:29:52
የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ከኦሮሚያ ክልል የተውጣጡ ልኡካንን አነጋግረዋል።

@fastmereja
4.4K views09:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ