Get Mystery Box with random crypto!

ETV.News

የቴሌግራም ቻናል አርማ etv_news — ETV.News E
የቴሌግራም ቻናል አርማ etv_news — ETV.News
የሰርጥ አድራሻ: @etv_news
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 7.43K
የሰርጥ መግለጫ

@etv_newss (tikvah news)

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-09-02 09:19:11
የፖሊስ መልዕክት !

የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ምክትል ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ ለቢቢሲ የሰጡት ቃል ፦

" ምንም በማያውቁት ጉዳይ በህጻናቱ ላይ የተፈጸመው ይህ አሰቃቂ ወንጀል ሁሉንም በእጅጉ አሳዝኗል።

ወላጆች የሚቀጥሯቸው የቤት ሠራተኞችን ማንነት ጠንቅቀው ማወቅ ይገባቸዋል።

እንደ ቤተሰብ ሆነው የሚኖሩ የቤት ሠራተኞች እንዳሉ ሁሉ እንደዚህ አይነት አሰቃቂ ወንጀል የሚፈጽሙም ስላሉ ሕብረተሰቡ ጥንቃቄ ማድረግ አለበት። "

#ተጨማሪ_መረጃ ፦

• በአንድ ቀን በአሰቃቂ ሁኔታ ሁለት ታዳጊ ልጆቻቸውን ያጡት ወላጆች በከባድ ሐዘን ውስጥ ይገኛሉ።

• ወንጀሉ በተፈጸመበት አካባቢ ያሉ ነዋሪዎችም በእጅጉ ተረብሸው ነው የሚገኙት።

• ፖሊስ በወንጀሉ ዙሪያ ተጨማሪ ምርመራ እያደረገ ነው።

- ተጠርጣሪዋ ህጻናቱን አንቃ እና ስለት ተጠቅማ በአስቃቂ ሁኔታ መግድሏ የሚያመላክቱ መላምቶች አሉ።

- ተጠርጣሪዋ ወንጀሉን ለመፈጸም ምን እንዳነሳሳት ለማወቅ ምርመራዎች እየተካሄዱ ነው።

- በወንጀሉ የተጠርጠረችው ግለሰብ በቤት ሠራተኛነት ግድያው ለተፈጸመበት ቤተሰብ ስታገለግል ቆይታለች።

• ተጠርጣሪዋ ወንጀሉን የፈጸመችው ወላጆች የሌሉበትን ሰዓት ጠብቃ ነው።

መረጃው ም/ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ ለቢቢሲ የአማርኛ አገልግሎት ከሰጡት ቃል የተወሰደ ነው።

#AddisAbabaPolice

@tikvahethiopia
132 views06:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-02 09:19:11
#AddisAbaba

ዛሬ በአዲስ አበባ ከተማ አሰቃቂ የግድያ ወንጀል መፈፀሙን ፖሊስ ገልጿል።

በአዲስ አበባ ለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 ቦሌ አራብሳ ኮምዶሚኒየም በሁለት ህፃናት ላይ እጅግ አሰቃቂ ግድያ መፈፀሙን የአዲስ አበባ ፖሊስ አሳውቋል።

የወንጀል ድርጊቱ የተፈፀመው ከጠዋቱ አራት ሰዓት ላይ ሲሆን ፤ በቤት ሰራተኝነት ተቀጥራ የምትሰራ አንዲት ግለሰብ ክርስቲያን መላኩና ወንጌላዊት መላኩ የተባሉ የሁለት ዓመትና የሶስት አመት ህፃናትን ህይወት አጥፍታለች።

የአዲስ አበባ ፓሊስ ኮምሽን የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ም/ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ ፦

" ቦታው ለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ነው፤ ወረዳ አራት አራብሳ ኮንዶሚኒየም እዛ አካባቢ ነው።

ወንጀሉ ተፈፀመው አራት ሰዓት አካባቢ ነው። ግለሰቧ እጅግ ዘግናኝ የሆነ ወንጀል ነው የፈፀመችው።

የሁለት ዓመት እና የሶስት ዓመት (ክርስቲያን መላኩ እና ወንጌላዊት መላኩ) ህፃናትን ነፍስ ነው ያጠፋችው።

ምክንያቱ ገና እየተጣራ ነው ወንጀል ፈፃሚዋ ግን በቁጥጥር ስር ውላለች። እስካሁን ባለን መረጃ ከአሰሪዎቿ ጋር በተፈጠረ ፀብ ነው የሚባለው።

የአገዳደል ሁኔታው እየተጣራ ነው። በምንድነው የገደለችው እንዴት ነው የገደለችው የሚለው ነገር ... ግማሹ አርዳነው ያላል ግማሹ አንቃ ነው ይላል እየተጣራ ነው ዞሮ ዞሮ ግን የህፃናቱ ህይወት አልፏል ይሄ ነው አሁን ላይ በተጨባጭ ሊገለፅ የሚገባው።

ወንጀሉ እጅግ ዘግናኝ ስለሆነ ፖሊስ መስራት የሚገባውን ሰርቶ ለሚመለከተው የፍትህ አካል ያቀርባል ህብረተሰቡ መረጋጋት አለበት። "

#ኢትዮኤፍኤም

@tikvahethiopia
123 views06:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-02 09:19:10
#ATTENTION

ሰንበቴ !

የሰንበቴ ከተማ አስተዳደር ወቅታዊ የጸጥታ ሁኔታ መነሻ በማድረግ ከነሐሴ 26/ 2014 ዓ/ም ጀምሮ ላልተወሰነ ጊዜ የሰዓት እላፊ ገደብ አውጇል።

በዚህም መሰረት ፦

- የከተማ ባለ 3 እግር ተሽከርካሪዎች (ባጃጆች) ከምሽቱ 12 ሰአት ጀምሮ በከተማው ውስጥ ማሽከርከር ተከልክለዋል።

- ከተመደበው የጸጥታ ኃይል በስተቀር ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ እስከ ንጋቱ 12:00 ሰዓት ድረስ #ማንኛውም_ሰው መንቀሳቀስ ተከልክሏል።

የተጠቀሰው የሰአት እላፊ ገደብ ጥሶ የተገኘ ግለሰብ ላይ አስፈላጊው የህግ እርምጃ እንዲወሰድ ታዟል ሲል የከተማ አስተዳደሩ አስጠንቅቋል።

@tikvahethiopia
72 views06:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-02 09:19:10
"ጦርነት ቆሞ የሰላም ሂደቱ ይቀጥል"

በሰሜን ኢትዮጵያ ክፍል ዳግም ያገረሸው ግጭት ተባብሶና ሰፍቶ እየቀጠለ ባለበት በዚህ ወቅት መሳሪያ ወርዶ ወደ ንግግር እንዲገባ እና ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን የሚቀርቡ የሰላም ጥሪዎች ቀጥለዋል።

በዛሬው ዕለት የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ" ጦርነት ቆሞ የሰላም ሂደቱ ይቀጥል" ሲል የሰላም ጥሪ አቅርቧል።

ጉኤው ምን አለ?

- ዳግም የተቀሰቀሰው ጦርነት ሊቆምና የሰላም ሂደቱ ሊቀጥል ይገባል።

- የሰላም ቅድመ ሁኔታው ሰላም ብቻ በመሆኑ ጦርነቱን በማቆም ሰላማዊ ንግግሮች መቀጠል አለባቸው።

- ከዚህ ቀደም የጉባኤው የበላይ ጠባቂ አባቶች ተደጋጋሚ የሰላም ጥሪ ሲያደርጉ ቆይተዋል፤አሁንም የሰላም ጥሪ እናቀርባለን።

- የፌደራሉ መንግሥት ለሰላማዊ ንግግሮች ዝግጁ መሆኑን በተደጋጋሚ እንደገለጸው ሌሎችም ወገኖች ለዚህ ተግባር ዝግጁ ሊሆኑ ይገባል።

- የሕዝብ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት፣ የሃይማኖት ተቋማትና ንጹኃን ዜጎች ጥበቃ ሊደረግላቸው ይገባል።

- ህፃናትን ለወታደራዊ ዘመቻ ማሰለፍ በዓለም አቀፉ የጦር ወንጀል የሚያስጠይቅና በሁሉም መመዘኛ ተገቢ ባለመሆኑ ሊቆም ይገባል።

- በወቅታዊ ጉዳይ ኃላፊነት በጎደለው መልኩ ሐሰተኛ መረጃ የሚያሰራጩ አካላት ከድርጊታቸው ሊታቀቡ ይገባል።

- ትግራይ ክልል የሚገኙ የሃይማኖት አባቶች መሪዎች የትግራይ ክልል ወደ ሰላማዊ ድርድሩ እንዲመለስ በመምከር አባታዊና መንፈሳዊ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጥሪ እናቀርባለን።

- የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰቡና የውጭ ሀገራት መንግሥታት፣አፍሪካ ሕብረት፣ ተመድና ሌሎች አካላት ሁሉ የሰላም ጥረቱ አጋዥ እንዲሆኑ ጥሪ እናቀርባለን።

- የጳጉሜን 5ቱን ቀናት ምእመናን በፆምና ፀሎት እንዲያሳልፉ ጥሪ እናቀርባለን።

(የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ)

#ENA

@tikvahethiopia
66 views06:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-02 09:19:10
#Update

#ሰቆጣ

መላው የሰቆጣ ነዋሪዎች በአሉባልት እና ሀሰተኛ መረጃዎችን ሳይደናገሩ አካባቢያቸውን በንቃት እንዲጠብቁ ጥሪ ቀርቧል።

#ኮምቦልቻ

ዛሬ በኮምቦልቻ ከከተማው የሀይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች ፣ በከተማው ከሚታወቁ ታዋቂ ግለሰቦች ጋር ወቅታዊ ጉዳይ ላይ ውይይት ተደርጎ ነበር።

በዚህም መድረክ ፤ የተለያዩ ሀሰተኛ አሉባልታዎች በመንዛት ህዝቡን ለማሸበር የሚደረጉ ጥረቶች መኖራቸው ተገልጾ መላው ነዋሪ ተረጋግቶ በንቃት አካባቢውን በመጠበቅ ከፀጥታ ኃይሎች ጋር በጋራ ሊሰራ ይገባል ተብሏል።

በሌላ በኩል ፤ በከተማዋ እስከሁን ባለው ከ400 በላይ ባጃጆች እና 80 ሞተሮች በህግ ቁጥጥር ስር ገብተው ማጣራት ተደርጎ ወደየመጡበት እንዲመለሱ መደረጉ ተገልጿል።

የመድረኩ ተሳታፊዎች ሁሉም ነዋሪ በቀበሌና ቀጠና ብሎክ ተደራጅቶ አካባቢውን መጠበቅ እንዳለበትና በእቃ ዋጋ ላይ ጭማሪ በሚያደርጉ ነጋዴዎች ላይ ጠበቅ ያለ ቁጥጥር ይደረግ ሲሉ ጠይቀዋል።

#ደሴ

ዛሬ በደሴ ከአምስቱም ክ/ከተሞች ከተውጣጡ ወጣቶች ጋር በወቅታዊ ጉዳይ ውይይት ተደርጎ የነበረ ሲሆን በዚሁ መድረክ ሀሰተኛ ፕሮፖጋንዳዎችን በማሰራጨት ህዝቡ ላይ የስነልቦና ጫና ለማሳደር ጥረት እየተደረገ መሆኑ ተገልጿል።

በዚህም የከተማው ወጣት በሙሉ በሀሰተኛ ወሬ እና በሀሰተኛ ፕሮፖጋንዳ ሳይረበሽ ከመላው የከተማው ነዋሪ ጋር በመሆን አካባቢውን እና የከተማውን ሰላም ሊያረጋግጥ ይገባል ተብሏል።

በከተማው የፀጥታ ኮማንድ ፖስት መቋቋሙ ተነግሯል።

#ወልድያ

ወልዲያ ከተማ አዳሯ ሰላም የነበረ ሲሆን የዛሬ ውሎዋም ሰላም ነው። አሁንም ቢሆን መላው ነዋሪ ተረጋግቶ አካባቢውን በመጠብቅ የከተማዋን ሰላም ሊያረጋግጥ ይገባል ተብሏል።

@tikvahethiopia
63 views06:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-02 09:19:10
#Update

#ደቡብ_ወሎ

በደቡብ ወሎ ከታች ቀበሌ እስከ ዞን ድረስ ከፀጥታ ኃይሎች ጋር በመሆን ህዝቡን እንዲረጋጋ የማድረግ ስራ እየተሰራ ነው ተብሏል።

በዞኑ ባሉ ወረዳዎች ውስጥ የሀገር መከላከያን ልብስ በመልበስ መከላከያ በመምሰል በአቋራጭ መንገዶች ሲጓዙ የነበሩ አካላት በቁጥጥር ስር መዋላቸው ተገልጿል።

በአሉባልታ ከሰሜን ወሎ ዞን የተፈናቀሉ በርካታ ሰዎች ወደ ዞኑ እየገቡ መሆኑን የገለፀው የደቡብ ወሎ ዞን ከሰሜን ወሎ ዞን ጋር በመሆን መመለስ ያለባቸውን ተፈናቃዮች እና ሰሌዳ አልባ ተሽከርካሪዎችን የመመለስ ስራ እየተሰራ ነው ብሏል።

#አምባሰል_ወረዳ

በአምባሳል ወረዳ ሀሰተኛ አሉባልታ ሲነዙ እና ህብረተሰቡን በማወክ ዘረፋ ሊፈፅሙ ተዘጋጅተው የነበሩ 9 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን አሳውቋል።

መላው ነዋሪ በሀሰተኛ ወሬና አሉባልታ ሳይደናገጥ በፍፁም መረጋጋት አካባቢውን በንቃት እንዲጠብቅ ጥሪ ቀርቦለታል።

#ሐይቅ

በሐይቅ ከተማ " ከዚህ ቀደም ህወሓት ቀብሮት የነበረ ከባድ እና ቀላል መሳሪያ ተገኘ " እየተባለ በማህበራዊ ሚዲያ የሚሰራጨው መረጃ ሀሰተኛ መሆኑን የከተማው ፖሊስ አሳውቋል።

የህብረተሰቡን ሰላም ለማወክና አካባቢው እንዳይረጋጋ እንዲሁም ተከታይ ለማብዛት ሲሉ ሀሰተኛ መረጃ የሚያሰራጩ አካላት ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷል።

" ምንም ባላያችሁበትና ባላረጋገጣችሁበት አዲስ አበባ ቁጭ ብላችሁ በሀሰተኛ መረጃ ህዝብ የምትረብሹ ኃላፊነት የጎደላችሁ የማህበራዊ አንቂ ነን የምትሉ ግለሰቦች፣ ዩትዩበሮች ከድርጊታችሁ ታቀቡ " ያለው የሐይቅ ፖሊስ ይህን የፈፀሙት ላይ በህግ እንዲጠየቁ እየሰራው ነው ብሏል።

ነዋሪዎች በሀሰተኛ መረጃ ይስደናገጡ በተረጋጋ ሁኔታ የአካባቢውን ሰላም በንቃት እንዲጠብቁ ፖሊስ መልዕክት አስተላልፏል።

@tikvahethiopia
69 views06:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-02 09:19:10
#ScholarshipProgram

ካስ ኢትዮጵያ/አፍሪካ ሕብረት ቢሮ የነፃ ትምሕርት ዕድል ለኢትዮጵያዊያን የማስተርስ እና የዶክትሬት ዲግሪ ተማሪዎችና ምሩቃን ማዘጋጀቱን ለቲክቫህ ቤተሰቦች በላከው መረጃ ገልጿል።

የማስተርስ ትምህርታችሁን በሀገር ውስጥ የጀመራችሁ እንዲሁም ለመጀመር እቅድ ያላችሁ የዚህ ስኮላርሽፕ ተጠቃሚ መሆን ትችላላችሁ።

በተጨማሪም የማስተርስ ድግሪ ወይም PHD ኖሯችሁ ተጨማሪ ኮርሶችን መማር ለምትፈልጉ በተመሳሳይ እድሉን እንድትጠቀሙ ጥሪ ቀርቧል።

የማመልከቻ ቀን ከነሐሴ 26/2014  - መስከረም 20/2015 ዓ/ም ነው።

ዝርዝር መስፈርቶችንና የማመልከቻ መንገዶችን https://www.kas.de/en/web/aethiopien/sur-place-scholarship-program መመልከት ይቻላል።

መልካም ዕድል!

Via @tikvahethmagazine
70 views06:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-02 09:19:10
ወቅታዊ ጉዳዮች ፦

- የአሜሪካ ህዝብ ተራድኦ ድርጅት አስተዳዳሪ ሳማንታ ፓወር በኢትዮጵያ አፋር፣አማራ እና ትግራይ ክልሎች የሰብአዊ እርዳታ ሰጪዎች እስር፣ የነዳጅ ዘረፋና ተሸከርካሪ በኃይል የመውሰድ ጨምሮ ተቀባይነት የሌለው ጣልቃ ገብነት እየደረሰባቸው ነው ብለዋል። ዕርዳታ ለተቸገሩት ይደርስ ዘንድ ሁሉም ወገኖች የሰብአዊ ተግባራትን እንዲያከብሩ ጥሪ እናቀርባለን ብለዋል። ፓወር በዚህ መልዕክታቸው የድርጊቶቹ ፈፃሚዎችን በግልፅ አልተናግሩም። ፓወር ከዚህ ቀደም ህወሓት 150 ሺህ ጋሎን ነዳጅ ከመቐለ WFP መጋዘን መዝረፉንና ሰራተኞችን ማንገላታቱን በመግለፅ ነዳጁን እንዲመልስ ጥሪ ማቅረባቸው የሚታወስ ሲሆን በዚህ መልዕክታቸው በአማራ እና አፋር ክልሎች ውስጥ ስለተፈፀሙ ድርጊቶችና ፈፃሚዎች በግልፅ ሳያብራሩ አልፈዋል።

- አሜሪካ በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሯ አንቶኒ ብሊንከን በኩል የኢትዮጵያ መንግስት እና ህወሓት ወታደራዊ ኦፕሬሽኖችን በአስቸኳይ እንዲያቆሙና ግጭቱን በዘላቂነት ለማስቆም የሚደረገውን ጥረት በእጥፍ እንዲያጠናክሩ ጠይቃለች። ጦርነቱ እንደገና መቀስቀሱ ​ና በዚህ ሳቢያ አደጋ ላይ የሚወድቀው ህይወት ያሳስበናል ብላለች።

- የዩናይትድ ኪንግደም መንግስት የትግራይ ኃይሎች በአስቸኳይ ከአማራ ክልል ግጭት አቁመው ወደ ትግራይ እንዲመለሱ የኤርትራ ኃይሎችም ከትግራይ እንዲወጡ ጠይቋል። ንግግር ቢጀመር ሰላማዊ መፍትሄ ለማምጣት እንደሚቻል ገልጿል። የኢትዮጵያ መንግስት በትግራይ መሰረታዊ አገልግሎት እንዲጀምር እንዲያደርግ ህወሓት ከWFP የወሰደውን ነዳጅ ለሰብዓዊ ስራ እንዲውል እንዲያደርግ ጠይቋል። ይህን ግጭት ለማስቆም ብቸኛው መንገድ ግጭት በማቆም ወደፖለቲካ ድርድር ማምራት ነው ብሏል ለዚህም የUK መንግስት የአፍሪካ ህብረትን የማሸማገል ጥረት እንደሚደግፍ አረጋግጧል።

@tikvahethiopia
70 views06:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-02 09:19:10
ወቅታዊ ጉዳዮች ፦

1. ዛሬ ህወሓት የኤርትራና የኢትዮጵያ መንግስት በጋራ ሆነው በ4 አቅጣጫ ጥቃት ከፍተዋል ሲል ከሷል። ጥቃቱ ከፍቅያ ገብረ እስከ አደመይቲ፣ ከሰላሞ - ሽራሮ፣ ከጎቦ ፅንዓት ወደ እርዲ ማቲዎስና አዲ አሰር እና አዲ ጎሹ በከባድ መሳሪያ ጥቃት እየተፈጸመባቸው ነው ብሏል። እስካሁን ከኢትዮጵያ መንግስት ሆነ ከኤርትራ በኩል ለዚህ ክስ ቀጥተኛ ምላሽ አልተሰጠም።

2. የኢፌዴሪ መንግስት መግለጫ፦

• ሕወሐት ወረራውን እያስፋፋ መጮኹን ቀጥሏል ብሏል። ህወሓት ተደጋጋሚ የሰላም ጥሪዎችን ገፍቶ በየአቅጣጫው በለኮሰውና ዛሬም እያስፋፋ ባለው እሳት ንጹሐን እየተገደሉ፣ ሕዝብ እየተፈናቀለ፣ ንብረትም እየወደመ ነው ብሏል። ሕወሓት ከሀገር አጥፊነት ተግባሩ የማስቆም ግዴታ ደግሞ በኢትዮጵያ መንግሥትና ሕዝብ ላይ መውደቁን ገልጿል።

• በሕወሓት ቡድን እየደረሱ የሚገኙ ጥፋቶችን ለማስቆም ለሰላማዊ  አማራጭ እየተደረጉ ያሉ ጥረቶች ሁሉ እየመከኑ ባቡለበት ሁኔታ ሕወሓትን መጫን ሲገባቸው "ሁለቱም ወገኖች" በሚል የሚወጡ መግለጫዎች ከእውነታው ያፈነገጡ ስለሆነ ተቀባይነት የላቸውም ብሏል።

• ሕወሓት ተደጋጋሚ የሰላም አማራጮችን በመግፋት የከፈተው ጥቃት ሃገርን እንዳይበትን፣ የመከላከያ ኃይል በሁሉም አቅጣጫ የተከፈተበትን ወረራ ከሰላም ወዳዱ ደጀን ሕዝብ ጋር በመሆን በጽኑ ጀግንነት በመከላከል ላይ ይገኛል ብሏል።

3. የኢትዮጵያ ምክትል ጠ/ሚና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን መንግስት የሀገሪቱን ሉአላዊነት ለማስከበር በሕወሓት ላይ የትኛውንም አይነት እርምጃ ለመውሰድ እንደሚገደድ ዛሬ ለአምባሳደሮች፣ የሚሲዮን መሪዎችና የዓለም አቀፍ ተቋማት መሪዎች በሰጡት ማብራሪያ ገልጽዋል። ከሚወሰደው እርምጃ ጎን ለጎን አሁንም #የሰላም በሮች ክፍት መሆናቸውን አሳውቀዋል።

@tikvahethiopia
73 views06:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 12:36:59
#Update

የኢፌዴሪ መንግስት ህወሓት በዋግ፣ በወልቃይት አቅጣጫና በሱዳን ድንበር (አማራ ክልል) አካባቢ ወረራ ከፍቷል ሲል አሳወቀ።

ከደቂቃዎች በፊት መግለጫ ያወጣው የኢፌዴሪ መንግስት ፤  " ሕወሐት በምሥራቅ አማራ በኩል በቆቦና አካባቢው የከፈተው ወረራ በጀግናው የመከላከያ ሠራዊትና በደጀኑ ሕዝብ ጠንካራ የመከላከል ብቃት የተነሣ ባሰበው ልክ አልሄደለትም " ብሏል።

በዚህ ምክንያት ወረራውን ወደ ሌሎች አካባቢዎች እያስፋፋ ነው ብሏል።

ህወሓት በዋግ፣ በወልቃይት አቅጣጫና በሱዳን ድንበር አካባቢ ወረራ መክፈቱን የገለፀው የኢፌዴሪ መንግስት ወራራውን የሀገር መከላከያ ሠራዊት በተሟላ ዝግጅትና በጽኑ ቁመና እየተከላከለ ይገኛል ብሏል።

ዛሬም ድረስ ለሰላም አማራጮች የተዘረጉ እጆች አልታጠፉም ያለው የኢፌዴሪ መንግስት ይህ ለሰላም የተዘረጋው እጅ በሕወሐት ዕብሪታዊ ወረራ ምክንያት እንዳይታጠፍ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ የሚቻለውን ያድርግ ሲል አሳስቧል።

" ወገን የሆነው የትግራይ ሕዝብም ይሄንን የዕብሪት ወረራ በማውገዝ ሕወሓት ከሚያስከትልበት መከራ ራሱን ነጻ ያውጣ " ሲል ጥሪ አቅርቧል።

(የኢፌዴሪ መንግስት መግለጫ ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
317 views09:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ