Get Mystery Box with random crypto!

ETV.News

የቴሌግራም ቻናል አርማ etv_news — ETV.News E
የቴሌግራም ቻናል አርማ etv_news — ETV.News
የሰርጥ አድራሻ: @etv_news
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 7.43K
የሰርጥ መግለጫ

@etv_newss (tikvah news)

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2022-08-27 19:58:01
" ድርጊቱን በፅኑ እናወግዛለን "  - የአልቾ ውሪሮ ወረዳ አስተዳደር

በስልጤ ዞን የአልቾ ውሪሮ ወረዳ አስተዳደር ፤ በቀን 19/2014 ምሽት ላይ በኦሮሚያ ክልል ሌሙ ከተማ አቅራቢያ በሰላማዊ ዜጎችና ንብረት ላይ ጥቃት መፈፀሙን አሳወቀ።

ወረዳው ጥቃቱን አጥብቆ እንደሚያወግዝ ገልጿል።

ጥቃቱ ሌሙ መግቢያ አቅራቢያ በሚገኝ ስፍራ ላይ መነሻቸውን አልቾ ውሪሮ ወረዳ በማድረግ ወደ አዲስ አበባ በመጓዝ ላይ በነበሩ አሸክርካሪዎች እና ተሽከርካሪዎች የተፈፀመ መሆኑ ተመላክቷል።

ጥቃት አድራሾቹ ለግዜው ማንነታቸው በውል እንደማይታወቅ ነገር ግን የታጠቀ ቡድን እንደሆነ ወረዳው ገልጿል።

ታጣቂ ቡድኑ ከአልቾ ውሪሮ ወረዳ ጎመንና ቅመማ ቅመም በጫኑ 2  የደረቅ ጭነት መኪናዎች (አይሱዙ) እና ለግዜው መነሻቸው ከሌላ ቦታ በሆኑ የጭነትና የህዝብ ማመላለሻ መኪኖች ላይ ጥቃቱን እንደረሰ የተገለፀ ሲሆን በጥቃቱ ምክንያት በሰው ህይወት እና በንብረት ላይ ከባድና ቀላል ጉዳት መድረሱን ተገልጿል።

የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ አማን ከድር " በወረዳችን በተለያዩ ከተሞች በአትክልትና ፍራፍሬ ንግድ ላይ በማህበር ተደራጅተው ምርቱን ከወረዳው ማዕከል በመሰብሰብ ለማዕከላዊ ገበያ በሚያቀርቡ ነጋዴዎች ምርትና ምርቱን በጫኑ አሽከርካሪዎችና የጭነት አይሱዚ ተሽከርካሪዎች ላይ ጥቃት ደርሷል " ሲሉ የነበረውን ሁኔታ ገልፀዋል።

ወረዳው ይህን ተግባር በጽኑ እንደሚየወግዘው ገልፀው በአደጋው የተጎዱ ነጋዴዎችንና አሽከርካሪዎች ፈጥነው ወደ መደበኛ ስራቸው እንዲመለሱ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚደረግ አሳውቀዋል።

@tikvahethiopia
419 views16:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 19:58:01
#EU

የትግራይ ባለስልጣናት የተዘረፈውን ነዳጅ በአስቸኳይ ይመልሱ ሲሉ የአውሮፓ ኅብረት የቀውስ ጉዳዮች ኮሚሽነር ጃኔዝ ሌናርቺክ ጠይቀዋል።

ሌናርቺክ ፤ ያለ ነዳጅ በትግራይ ውስጥ ምግብ የማድረስ ስራ ሊሰራ አይችልም ብለዋል።

የሚሊዮች ህይወት በዚህ ላይ የተመሰረተ ነው ሲሉ አስገንዝበዋል።

@tikvahethiopia
348 views16:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 19:58:01
" የሰላም ንግግር አሁንም ይቻላል " - አምባሳደር ዘነበ ከበደ

በጄኔቫ የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛና ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ዘነበ ከበደ በኢትዮጵያ መንግስት እና በህወሓት መካከል የሰላም ንግግር አሁንም ይቻላል ብለዋል።

ነገር ግን ፤ ይህ የሚወሰነው የሰላም ንግግርን ውድቅ አድርጎ ወደ ጦርነት ባመራው ህወሓት /TPLF/ አቋም ነው ሲሉ ገልፀዋል።

የኢትዮጵያ መንግስት ለሰላም ያለውን አቋም በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ዘንድ ግልፅ አድርጓል ብለዋል።

በሌላ በኩል ፤ ዛሬ ከሰዓት የፌዴራል መንግስት ባወጣው መግለጫ ህወሓት የከፈተውን ወታደራዊ ጥቃት አሁንም አብብሶ ቀጥሏል ብሏል።

ቡድኑ ለሰላም የተዘረጋውን መንገድ ትቶ በሙሉ አቅሙ ለጦርነት ሲዘጋጅ ቆይታል ሲል አስታውሷል።

አሁን ላይ በተለያዩ ግንባሮች የከፈተውን ጥቃት አድማሱን በማስፋት ለፍቶ አዳሪ ንፁሃንን ኢላማ እያደረገ ነው ብሏል።

ህወሓት የሰው ማዕበል የጦርነት ስልት በመከተል በሺዎች የሚቆጠሩ ታዳጊዎችንና ወጣቶችን በገፍ እየማገደ ነው ያለው የፌዴራሉ መንግስት ቡድኑ ኃሉን አሰባስቦ በአፋር እና አማራ አዋሳኝ ቦታዎች እየተንቀሳቀሰ ነው ብሏል።

የሰላም አማራጩ እንዳለ ሆኖ ሀገር መከላከያ ሰራዊት የተከፈተውን መጠነ ሰፊ ጥቃት በተሟላ ሁኔታ እየመከተ ነው ሲል አሳውቋል።

በሰሜን ኢትዮጵያ ዳግም ግጭት ካገረሸ ወዲህ ከቀን ወደ ቀን ሁኔታዎች ከመርገብ ይልቅ የመባባስ ምልክት እያሳዩ ሲሆን እስከዛሬ በዜጎች ላይ ከደረሰው ጉዳት የበለጠ እንዳይደርስ ከየአቅጣጫው የሰላም ጥሪዎች እየቀረቡ ናቸው።

@tikvahethiopia
321 views16:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 19:58:01
#Update

- የተመድ ዋና ፀሀፊ ቃል አቀባይ ስቴፋን ዱጃሪች ምንም እንኳን UN ይሄን ለማረጋገጥ (የአየር ጥቃቱ) የሚያስችል ሁኔታ ላይ ባይሆንም በመቐለ የአየር ጥቃት መፈፀሙን የሚገልፁ ሪፖርቶች "እጅግ በጣም አሳሳቢ ናቸው" ብለዋል። በመቐለ ያሉት የተመድ አባላት ደህና ናቸው ፤ ነገር ግን ግንኙነቱ እና ሰራተኞችም ለመንቀሳቀስ ያላቸው አቅም ውስብስብ ነው ብለዋል።

- የተመድ የህፃናት መርጃ ድርጅት (UNICEF) በበኩሉ በመቐለ የአየር ጥቃት መፈፀሙን እና በዚህም ህፃናት መሞታቸውን ሌሎች ትልልቅ ሰዎች ማጎዳታቸውን በማመልክተ ድርጊቱ በፅኑ እንደሚያወግዝ ገልጿል። ሁሉም ወገኖች በፍጥነት ግጭት ይቆም ዘንድ ወደ ስምምነት እንዲመጡም ጠይቋል። አሁንም በሰሜን ኢትዮጵያ እየተባባሰ የመጣው ግጭት ህፃናት ከፍተኛ ዋጋ እንዲከፍሉ እያደረገ ነው ያለው UNICEF በክልሉ የሚኖሩ ልጆችና ቤተሰቦቻቸው ላለፉት 2 ዓመታት ግጭቱ ያመጣውን ስቃይ ተቋቁመዋል አሁን ግን ማብቃት አለበር ብሏል።

- የዩናይትድ ኪንግደም የአፍሪካ ጉዳዮች ሚኒስትር ቪኪ ፎርድ በትግራይ የተፈፀመ የአየር ድብደባን ተከትሎ በሰላማዊ ዜጎች ላይ ጉዳት መድረሱን የሚገልፁ ሪፖርቶች አስደንጋጭ ናቸው ብለዋል። ሁሉም ወገኖች ዓለም አቀፍ የሰብዓዊነት ህግን ማክበር እና ለሲቪሎች ጥበቃ ቅድሚያ መስጠት አለባቸው ብለዋል።

- የአውሮፓ ኅብረት የቀውስ ጉዳዮች ኮሚሽነር ጃኔዝ ሌናርቺክ ትላንት በመቐለ የሲቪል ሰዎችን ሞት ያስከተለ የአየር ጥቃት ተፈፅሞ እንደነበር ገልፀው ጥቃቱን እንደሚያወግዙ ገልፀዋል። ዓለምአቀፍ የሰብዓዊነት ህጎች ሊከበሩ ይገባል ሲቪሎች ዒላማ ሊሆኑ አይገባም ብለዋል። ሌናርቺክ ፤ ሁሉም ወገኖች የሰላም ድርድር እንዲያደርጉና ለተቸገሩ ሰዎች ሰብዓዊ እርዳታ እንዲደርስ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።

@tikvahethiopia
324 views16:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 15:50:13
#Update

የሲዳማ ክልል የዞን አደረጃጀት ፀደቀ።

የሲዳማ ክልል ምክር ቤት የዞን አስተዳደር እና አደረጃጀትን ለማቋቋም የወጣ አዋጅ ተቀብሎ ክልሉ በ4 ዞኖች እና በ1 ከተማ አስተዳደር እንዲደራጅ ውሳኔ አሳልፏል።

የክልሉ ምክር ቤት ውሳኔውን ያሳለፈው እያካሄደ ባለው መደበኛ ጉባኤ ነው።

የዞኖቹ ስያሜዎች ሰሜን ሲዳማ ዞን፣ ማዕከላዊ ሲዳማ ዞን፣ ደቡብ ሲዳማ ዞን እና ምስራቅ ሲዳማ ዞን በሚል እንደሚጠራ ተገልጿል።

@tikvahethiopia
476 views12:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 15:50:13
" እኛ ለጎንደር ከተማ እና ለህዝቡ ክብር አለን "  - አቶ ኢሳያስ ጅራ

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በዛሬው ዕለት የምርጫ የጠቅላላ ጉባኤውን በአዲስ አበባ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስብሰባ አዳራሽ በማካሄድ ላይ ይገኛል ።

ምርጫው ከጎንደር ወደ አዲስ አበባ ለምን ተቀየረ ?

" ይሄ አስተዳደራዊ ጉዳይ ነው " ያሉት የወቅቱ የፌዴሬሽኑ ፕሬዝዳንት አቶ ኢሳያስ ጅራ " ጣልቃ ገብነቶች እና ሂደቶችን ስላየን ቦታውን ቀይረናል ፣ ውሳኔውን አስተላልፈን ለስራ አስፈፃሚ አቀረብን ሂደቱን ጠብቀን ነው ያደረግነው " ብለዋል ።

" ሂደቱ የነበረው ይህ ነው ፣ ራስን መፈተሽ አስፈላጊ ነው ፣ ይሄንን ጉባኤ በዚህ መልኩ ነው ማስኬድ ያለብህ ብሎ የመንግስት አካል ትዕዛዝ መስጠት አይችልም።

ቦታ ተቀየረ ተብሎ ጥቃቅን ጉዳይ አንስቶ አጀንዳ ማድረግ አግባብ አይደለም ፣ ደግሞም ቦታ ስንሰጥ የሰጠነው ለክልሉ ሳይሆን ለከተማው ነው።

እኛ ለጎንደር ከተማ ለህዝቡ ክብር አለን ፣ የጦርነት ወላፈን ከነካቸው ቦታዎች አንዱ ነው ሁለት ወር ለኢኮኖሚውም እገዛ ውድድር ሁሉ አድርገን የቆየነው እንጂ የሁለት ቀን ከለከሉ መባል የለብንም " በማለት አቶ ኢሳያስ ጅራ ተናግረዋል።

በዛሬው ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ከፊፋ እና ካፍ ተወክለው የመጡ ታዛቢዎችን ጨምሮ ከፍተኛ የስፖርቱ ባለስልጣናት ታድመዋል ።

ቲክቫህ ስፖርት : https://t.me/+VvwzStMNcNHmhK0x

@tikvahethsport    
414 views12:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ