2022-08-30 21:49:57
#ATTENTION
ደብረ ብርሃን !
የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር የፀጥታ ምክር ቤት ወቅታዊ የፀጥታ ስጋትን አስመልክቶ የሚከተሉትን ውሳኔዎች አሳልፏል።
- በከተማው አስተዳደር በተፈናቃይ መጠለያ ጣቢያ ውስጥ የሚኖር ተፈናቃይ ከምሽቱ 12:00 ሰዓት በኋላ ወደ መጠለያ ጣቢያውም ሆነ ወደ ከተማው መግባት ተከልክሏል።
- ሁሉም አይነት ተሽከርካሪዎች ከምሽቱ 2፡00 ሰዓት በኋላ መንቀሳቀስ ተከልክሏል።
- መጠጥ ቤቶች ፣ ምግብ ቤቶች ምሽት ጭፈራ ቤት እስከ ምሸት 2:00 ሰአት ብቻ አገልግሎት እንዲሰጡ ተወስኗል።
- የንግድ ቤቶች የምርት የዋጋ ጭማሪ ማድረግ በጥብቅ ተከልክሏል።
- ከተፈቀደላቸው የፀጥታ ሀይሎች ውጭ የጦር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ ፈፅሞ ተከልክሏል።
- ከመንግስት ዕውቅና ውጭ ማናቸውም አይነት ውይይቶችና ስብሰባ ማድረግ ተከልክሏል።
- አዳር የሚሰሩ በከተማው ያሉ ፋብሪካዎችና ድርጅቶች ድርጁቱ በሚሰጣቸው ህጋዊ መረጃ እና በፀጥታ መዋቅሩ የተረጋገጠ የይለፍ ከያዛ ብቻ መንቀሳቀስ ይችላሉ።
- ህብረተሰቡን ለማሸብር አሉባልታ መንዛት፣ ወሬ ማሰራጨት በጥብቅ የተከለከለ ነው ፤ መላው ማህበረሰብም አካባቢውን ቀንና ሌሊት በንቃት መጠበቅ አለበት።
- የሆቴል አልጋ አከራዮች ማንነቱ ያልታወቀ የታጠቀ ገለሰብ በድርጅታቸው ውስጥ ሲያጋጥም ለህግ አካላት እንዲያሳውቁ ፤ በሌላ በኩል ፤ የቤት አከራዮች የሚያከራዩትን ግለሰብ መታወቂያ በመጠየቅ፣ ፎርምም በመሙላት ሰላም እና ፀጥታ መምሪያ እንዲያሳውቁ ተብሏል።
(ተጨማሪ ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
507 views18:49