Get Mystery Box with random crypto!

ስብዕናችን #Humanity

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiohumanity — ስብዕናችን #Humanity
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiohumanity — ስብዕናችን #Humanity
የሰርጥ አድራሻ: @ethiohumanity
ምድቦች: ሳይኮሎጂ
ቋንቋ: አማርኛ
ሀገር: ኢትዮጵያ
ተመዝጋቢዎች: 30.61K
የሰርጥ መግለጫ

🔆እየጠየቁ መኖር መልስን፣
መልስን ፈልጎ ማግኘት ዕውቀትን፣
እውቀት ነፃነትን፣ ነፃነት ሙሉ ስብዕናን፣
ሙሉ ስብዕና ሠላምና እርካታን፣
እርካታ ደግሞ ደስተኛ ሆኖ መኖርን ያስገኛል፡፡
አብረን እንደግ !!
@EthioHumanity @Ethiohumanity
✍የተሰማቹን አጋሩን! ቤቱ ሁሌም ክፍት ነው፣ሃሳባቹን ፃፍፍ አርጉልን @EthioHumanitybot

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 32

2021-11-19 18:22:55 ከወረቀት ያልተዋደደ ብዕር ምን ምስጢር ያወራል?
ብቻውን የቆመ ግድግዳ ለማን ከለላ ይሰራል?
ተከታይ የሌለው ነብይ ምን እውነት ይናገራል?
ከሰው ያልተዋሃደ ሰው መች ከልቡ ይኖራል?
ይህ አለም ጥምረት ነው አንዱን ካንዱ ያዋቀረ
በተፈጥሮ ጉጉን ጎንጉኖ ሁሉን ያስተሳሰረ
ከዚህ የህይወት ጉንጉን እራሱን ሊያወጣ የሞከረ
የዳር ተመልካች ሆነ እንጂ መች ከልቡስ ኖረ?

ከአበባው መሃል ቆሜ ይህን እያሰብኩኝ
አንዲት ቢራቢሮ ......አበባውን ስትስም ታዘብኩኝ
ስማ......ስትቀስም
ለመላምቴ ማስረጃ ፈጣሪ እጁን ሲሰጠኝ
ከአበባው ቀና አድርጎ ከቢራቢሮ አፋጠጠኝ
እዛው እንደቆምኩኝ.....
ይህ የትስስር ኑሮ ጠልቆ ይገባኝ ጀመረ
ሰው የራበው ልቤም ፍለጋውን አመረረ!!!

ሰው ያለሰው ፤ ሰው ያለዙሪያው ህይወትን ሙሉ በሙሉ ሊኖራት አይችልም። ሰው ስንል ግዴታ በአንድ ጣሪያ ስር የሚኖርን ወዳጅ አይደለም፤ በዙሪያችን ያለውን ሁሉ እንጂ። እኛ ከአለም ውጪ አለም ከእኛ ውጪ አንደኛችም መኖራችን አይረጋገጥም ። የሰው ዘር ከእኛ ህይወት ውስጥ ፤ እኛም ከሰው ዘር ውስጥ መውጣት አንችልም። ልክ ገጣሚው እንደሚለው “አንተ የውቂያኖሱ ጠብታ ሳትሆን ውቂያኖሱ ያንተ ጠብታ ነው” እንዳለው መሆኑ ነው።

ብዙ የከበዱን ነገሮች ሊቀሉን የሚችሉት፤ እራሳችንን ከተመልካችነት ወደ ተሳታፊነት ማቅረብ ስንችል ነው። አሁን ከፊት ለፊቴ የተቀመጠችው ወጣት፤ እራቅ ብለው የቆሙት አዛውንት፤ ከአስፓልቱ ባሻገር የሚለምነው ለማኝ፤ ከለማኙ ጀርባ ባለው ፎቅ ውስጥ የተቀመጠው ባለሃብት፤ ሁላችንም የተሳሰርን ነን። እንዴት? እሱ በማስረዳት የሚመለስ አይመስለኝም፤ በመኖር ውስጥ ብቻ ሊገባን የሚችል ግላዊ እውነት እንጂ። ለብቻ የተሰራ አንድም ታሪክ የለም፤ ሁሉም የጥምረት ውጤት ነው።

የሰውን ከዙሪያው ጋር መዋሃድ አስፈላጊነቱን ስናወራ፤ በጥገኝነት መልኩ ብቻ አይደለም። ሁላችንም በራሳችን ምሉዕ ነን ብለን ልናስብ እንችላለን፤ በእርግጥም ምልዑ እንሆን ይሆናል። አንዳንድች ከሌላችን ጋር የተሳሰርንበትን ክር መበጠስ ስንሞክር ነው ችግሩ የሚፈጠረው።

በዚህ አለም ውስጥ የገለልተኝነት ስሜት ሊሰማን አይገባም፤ በቅርብ የምናወራው ሰው ባይኖረን፤ አብሮን ሌሊቱን የሚያሳልፍ ወዳጅ ባያድለን፤ ለቡናና ለሻይ የሚሆን ጓድ ቢጠርብን እንኳን፤ ከዚህ የህይወት ትስስር ውስጥ ክራችን እንደተቆረጠ ሊሰማን ፈጽሞ አይገባም። ለብቻ መሆን አይደለም የብቸኝነት መንስዔው፤ የብቸኝነት መንስዔው መንፈሳችንን ከዙሪያችን መነጠል ነው። ሁሉም ነገር የእኛ አካል ነው፤ እኛም የሁሉም ነገር አካል ነን፤ ይህ ተፈጥሮ የቆጣጠረው በእኛ ሃይል የማይፈታ ቋጠሮ ነው። ዙሪያችንን ወደእኛ በማቅረብ እኛም ወደዙሪያችን በመቅረብ ይህችንን ህይወት ትንሽ ትርጉም እንስጣት።

A wall standing alone is useless
But put three or four walls together And they will support a roof and keep The grain dry and safe.”

ሚስጥረ አደራው

ውብ አሁን
@EthioHumanity
@EthioHumanity
8.2K views15:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-11-19 18:22:42
6.6K views15:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-03 15:29:20
"If you don’t have peace within yourself, it is very difficult to work for peace. [During the Vietnam war] our thinking was, the other person is not our enemy. Our enemies are misunderstanding, discrimination, violence, hatred, and anger. With that kind of insight, we conducted the peace movement.

If you are filled with anger, you create more suffering for yourself than for the other person. When you are inhabited by the energy of anger, you want to punish, you want to destroy. That is why those who are wise do not want to say anything or do anything while the anger is still in them.

So you try to bring peace into yourself first. When you are calm, when you are lucid, you will see that the other person is a victim of confusion, of hate, of violence transmitted by society, by parents, by friends, by the environment. When you are able to see that, your anger is no longer there...”

~Thich Nhat Hanh~

@EthioHumanity
@EthioHumanity
164 views12:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-03 11:36:04 ጉዞ ወደ ሀሳብ..........

በጣም በተደጋጋሚ ከብዙ ሰዎች የምሰማው አባባል አለ "የኢትዮጵያ አምላክ አይተኛም ኢትዮጵያን ይጠብቃታል" የሚባለው አባባል
"

አድዋን ተዋግተን ያሸነፍነው
ጊዮርጊስ በፈረስ ላይ ሆኖ በጎራዴው የጣሊያኖችን አንገት እየቀላልን ነው ብላቹ ታምናላቹ..? እንደዛ ከሆነ ሌሎች ሀገራቶችን በጣሊያን ሲገዙ ፣ እንደ እቃ ሲሸጡ እና ሲለወጡ ፣ ሲገደሉ አምላክ እንዴት ዝም ይላል ? ኢትዮጵያ በተለየ የሚያይ አምላክ አለ..? ካለስ የአምላክነቱ ባህሪ (ፍትሃዊነት) ጥያቄ ውስጥ አይገባም ወይ...?


በሚኒሊክ ግዜ በፈረስ መጥቶ
የጣሊያኖችን አንገት የቀላልን ጊዮርጊስ በሃይለስላሴ ግዜ ለምን አልመጣም..?

ጣሊያኖች ተመልሰው መጥተው በመርዝ ጋዝ እንደ በረሮ ሲረፈርፉን ያ አድዋ ላይ የዘመተው መልአክ የት ሄደ? በ'3 ቀን 33 ሺ ኢትዮጵያዊያን በአካፋ በዶማ በድንጋይ ተወግረው እንደ ዶሮ አንገታቸው ተበጥሶ በየ መንገዱ ሲጣሉ አዲሳባ የደም ባህር ስቶን አድዋ ላይ የጣሊያኖችን አንገት የቀነጠሰው ጊዮርጊስ ምነው ለአዲስ
አበባ ግዜ ሲሆን ፀጥ አለ? ..

#አምላክ ኢትዮጵያን በተለየ መልኩ ይመለከታታል ? ማሳያዎችስ አሉት?


በእነዚህ ሀሳቦች ላይ የምታምኑበትን በጨዋ ደንብ ሀሳባቹን ወርውሩልን

@balmbaras
691 viewsedited  08:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-02 21:13:21 • ዛሬ ዕለተ ማግሰኞ የካቲት ፳፫-፳፻፲፫ ለዐዉዳችን እንዲስማማ ኾኖ የቀረ ተንቀሳቃሽ ምስል ነዉ። ቦታዉ ብሔራዊ ሙዚየም ዉስጥ ነዉ ፥ በወፍ በረር የዓድዋ ጦርነትን ለማዉሳት ሙዚየም ዉስጥ ባሉ ጥንታዊ ቅርሶች እና የኅብር የስነ ስዕል ልኺቃን ለሦስተኛ ያበጃጁትን አዉደ-ርዕይ ዋቢ አድርጎ የተቃኘ ነዉ። በነገራችኹ ላይ ይኽ የስነ-ስዕል አዉደ ርዕይ ከየካቲት ፲፱ እስከ መጋቢት ፲፱|፳፻፲፫ ድረስ እነደሚሠነብት ከደጋሾቹ ተነግሮኛል። •

ከ@Mykeyonthestreet የተሰረቀ
221 views18:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-02 21:13:21
229 views18:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-02 13:57:58
,#አድዋ

እንኳን ለ125ኛው የአድዋ ድል በዓል አደረሳችሁ አደረሰን

መልካም በአል ለሁላችን
169 views10:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-28 21:52:04 ሰዓት እላፊ!


# መፅሐፍ በዞረበት ከዞርኩኝ ሁለት ወር አልፎኝ ነበር (ለምንም ነገር ስሜት አጥታቹ ታውቃላቹ..?)እንደዛ ነገር! .....አስታወሳችሁት ከዚህ ቀደም ስለዚህ መፅሐፍ አውርቻቹ ነበር #በመሀል ለምን አልደግመውም በሚል መፅሐፉን ደገምኩት በቃ የተለየ ስሜት ነው የተሰማኝ በድጋሚም.......

#ተከተሉኝ
.
.
.


የጊዜ ዑደት የማይለውጠው ነገር አይኖረውም የማይችለው ነገር ቢኖር መሆን ያለብንን እና መሄዳችንን ብቻ ይመስለኛል ከዛ ውጭ ጊዜ ሁሉን እየወለወለ፣ እየከለሰ እያደሰም ሆነ እያፈረሰ እሳቤን፣ማንነትን ያሳየናል።ከጊዜ ጋር የማይበስል፣ በጊዜ እሳት ተጥዶም እንጭጭ የሚሆን አይጠፋም... ላውራላችሁ ያሰብኩት ስለ ጊዜ ሳይሆን ስለ አንድ መፅሀፍ ነው መቼቱን የወያኔ እንቅስቃሴ በተማሪዎች ላይ ሰርፆ በገባበት ወቅት ያረገው ይህ መፅሀፍ ከሀርቡ ተነስቶ በሀሳብ እና በፍልስፍና እየጎለበተ አዲስ አበባ ዩንቨርስቲ የተማሪዎች እንቅስቃሴን ያስቃኘናል....ልጅ ሳለሁ የአንባቢ ጣሪያ የሰብለን እና የበዛብህን ታሪክ ፍቅር እስከ መቃብር ላይ አንቦ መጨረስ ይመስለኝ ነበር(ያኔ ይህ መፅሀፍ ሊነግረን የሚፈልገው ፍቅራቸውን ብቻ ይመስለኝ ነበር) በቃ ፍቅር እስከ መቃብርን ያነበበ ካለ እሱ ለኔ የአንባቢ ጥግ ነበር....ለአሁኖቹ አንባቢያን ደግሞ አደፍርስ ይመስለኛል ገልጦ የጨረሰም አብጠርጥሮ የጨረሰም እኩል የምትወደው መፅሀፍ ሲባል አደፍርስ ይላል ይህን ሊል የሚችለው ግን ንባብን አዘውታሪ ከሆነ ብቻ ነው። ዛሬ ላይ ብዙ በገለጥን ቁጥር ብዙ እንደምናውቅ፤ ብዙ ባሰስን ቁጥር ብዙ እንደምናገኝ አውቃለሁ....አሁን ላወራላችሁ ያሰብኩት ስለ ሚክሎል ነው። ይህን መፅሀፍ ከገዛሁት ከወራቶች ቀደም ብሎም ያህል ቢሆነኝም ሁለቴ ገለጥኩት ሰሞኑን ነው ግን ውስጤን ሰቅዞ ስለያዘው እና ካተረፍኩት ደስታ ብትቃርሙ ብዬ ወደ እናንተ ያሳለፍኩት።


በፍቅር እስከ መቃብር ፣ በአደፍርስ እና አሁን ላወራላችሁ በፈለኩት ሚክሎል ውስጥ አንድ ከማህበረሰቡ በፍልስፍናቸው በእይታቸው እና በክዋኔያቸው አፈንጋጮች የተባሉ ግለሰቦች አሉ....ጉዱ ካሳ፣አደፍርስ እና ጉግሳ ነገር ግን ሁለቱ ከጉዱ ካሳ ጋር ሊያማስላቸው የሚችለው ነገር ማፈንገጣቸው ብቻ ሲሆን ሁለቱን ገፀ-ባህሪያት ግን አንዳንድ ተምሳሎት ስላላቸው ጥቂት ልበልላቸው። ሁለቱም ወጣት ናቸው የተገኙበትን ማህበረሰብ ማንቃት የሚሹ ፤ ሁለቱም ጥያቄ የሚጭሩ ሀሳቦችን የሚያነሱ ፤ ነገር ግን የሚክሎሉ ጉግሳ የማውቀው በቃኝ አይልም ሰው ይሰማል፣ የሚያጋጥሙትን ክስተቶች ችላ አይላቸውም ይማርባቸዋል ፤ በሚያወራው አደፍርስ ሲያደንቁት ሲያሞካሹት ይወዳል ጉግሳ ግን ለሙገሳ ቦታም የለው ፤ አንዳንዴ የአደፍርስ ሀሳቦች ከማህበረሰቡ ሲወርድ(ሲቀል) ይታያል ፤ አደፍርስ መስጠትን እንጂ መቀበልን የህይወቱ ኡደት ውስጥ አልከተታቸውም ምን አልባት ሀሳቦችን ተቀባይ እንዲሆን በጉግሳ የህይወት እንቅስቃሴ ላይ የተሳሉት ይህን ባህሪ ስላደሉት ይሆናል መሬት ወርዶ ከመሀይሙ፣ ከእብዱ፤ ከሴተኛ አዳሪው ይስማማል ይማራል....የልጅነት ፍልስፍናውን በአባቱ ቅኝት ምንም የሚያቅትህ ነገር የለም፣ ሁሌም ቢሆን ከቀልብህ ምከር እያሉ የቃኙት ወጣት የዩንቨርስቲ ተማሪ በንባብ ያካበተውን ወደ ውስጥ ተመልካችነት ክህሎት አንድ እብድ ጋር ያደርሰው እና ያለምክንያት መኖር ክልክል ነው የሚል ፍልስፍና ይቸረዋል....ምርጥ ስነ-ፅሁፍ፣ ቆንጆ የሀሳብ ፍሰት እና የህይወት ፍልስፍና በአንድ ጥራዝ ታትመው ቀርበዋል!!!


አስቸኳይ የንባብ እርምጃ ይወሰድበት!!!!! እውነት አንብቡት ትወዱታላቹ!!


@Ethiohumanity
@Ethiohumanity
@Nagayta
430 viewsedited  18:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-28 21:42:40
660 views18:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-28 19:29:48
በሰላም ቤትህ ገብተህና ተኝነተህ በነጋታው ጠዋት በሰላም መነሳትህን በፍጹም አትልመደው (Never take it for granted)፤ ይህንን እድል ያላገኙ ብዙ ሰዎች አሉና!

ይህንን ከፈጣሪ ብቻ ልታገኝ የምትችለውን የየቀን ተአምር እንዳልረሳኸው ለራስህ ለማስታወስ ከፈለክ ነገ ጠዋት በጥሩ አእምሮ ስትነቃ አንድን ነገር ለማድረግ አስበህ መተኛት ትችላለህ፡፡ ነገ የአንድን ሰው ችግር የሚያቃልል አንዲትን ተግባር ማከናወን ትችላለህ፡፡

ዋጋ ከፍለህ ብታደርገው የአንተን ህልውና የማይነካ፣ ለሌላው ለጨነቀው ሰው ግን የህልውና ጉዳይ የሚሆን አቅም በእጅህ ካለ የፈቃደኝነት ጉዳይ ነው እንጂ ያንን ከማድረግ ምንም ነገር እንደማይከለክልህ አትዘንጋ፡፡ አንድ ቀን የተጨመረልን አንድን ነገር በሰዎች ሕይወት እንድንጨምር እንደሆነ አትዘንጋ፡፡


ውብ እንቅልፍ

ደ/ር እዮብ ማሞ

@EthioHumanity
@EthioHumanity

@EthioHumanitybot
73 viewsedited  16:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ