Get Mystery Box with random crypto!

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiobooks — ከስነ-ፅሁፍ ዓለም
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiobooks — ከስነ-ፅሁፍ ዓለም
የሰርጥ አድራሻ: @ethiobooks
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 12.79K
የሰርጥ መግለጫ

የስነ-ፅሁፍ ቻናላችንን
👉 https://t.me/Ethiobooks ተቀላቀሉ።
ለማንኛውም አስተያየት እና ማስታወቂያ
👉 @firaolbm
@tekletsadikK
እናመሰግናለን።
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 6

2023-04-24 10:00:05 ጭንቅላትህ በፈጠረው ነገር አትጨነቅ፤
          የሆነውን ግን ተቀበል
═════ ❖ ═════
>>>
ዝናዋ በዓለም የታወቀ አንዲት የመድረክ ሴት ነበረች። ለአምሳ ዓመታት ያህል የመድረክ ንግሥት፣ የመድረክ እመቤት በመባል ታወቀች። በሰው ዘንድ ተወዳጅነትን አተረፈች። ግን በሰባ አንድ ዓመቷ አደጋ ደረሰባት።

ውቅያኖስን አቋርጣ በመርከብ ስትሄድ ወድቃ ተሰበረች፤ እግሯ ተሸማቀቀ። ከበሽታዋ ትድን ዘንድ ያላትን ገንዘብ በሙሉ ለሕክምና አወጣችው። ከብዙ ጥረት በኋላ ያክማት የነበረው ሐኪም እግሯ ካልተቆረጠ ልትድን እንደማትችል ተገነዘበ። «እግርሽ ሊቆረጥ ነው» ብሎ ለመንገር ፈራ። ሐኪሙ እውነቱን የነገራት እንደሆነ የምታብድ መሰለው።

እርሷ ግን እንዳይነግራት ፈርቶ ሲርበተበት ባየች ጊዜ ጉዷን አወቀች። በዚህ ጊዜ በሽተኛዋ የሐኪሟን ዓይን እያየች «ማድረግ ያለብህን ሁሉ መፈጸም አለብህ» አለችው። ከዚያም እግሯ ተቆረጠ።

እግሯ ሊቆረጥ ወደ ቀዶ ጥገና ክፍል ሲወስዷት ልጇ ቆሞ ሲያለቅስ አየችው። እሷ ግን እጇን ወደ ልጇ በማውለብለብ በፈገግታ «አትሂድ ቶሎ እመለሳለሁ» አለችው። ከቀዶ ጥገና ክፍል ልትደርስ ስትል ጤነኛ በነበረች ጊዜ ትዘምራቸው ከነበሩት ዜማዎች አንዱን ታንጎራጉር ጀመር። ለምን እንደምታንጎራጉር ብትጠየቅ «ሐኪሞችንና አስታማሚዎችን ለማስደሰት ነው» ስትል መለሰች።

ይህች ሴት በመጨረሻ እግሯ ቢቆረጥም ከዚያ በኋላ ለሰባት ዓመት ዓለምን እየዞረች ብዙ ሕዝብ ከተሰበሰበበት ለመዝፈን ችላለች። ስንቶቻችን ነን እስቲ እግራችን ሊቆረጥ ሲል የሴትዮዋን መንፈስ ሊኖረንና ለመዝፈን የምንችለው?

በዘፈን ፈንታ በማልቀስ ምንም ስለማይገኝ በትንሹም፣ በትልቁም እያለቀስክ ሕይወትህን አታበላሸው። ቆራጥ ሁን። የደረሰብህን እንደ ሴትዮዋ ተቀበለው እንጂ አልቃሻ አትሁን። ብዙ ብታለቅስና ብትማረር ሰው ይሸሽሃል እንጂ የምታተርፈው ነገር እንደሌለ እወቅ።

ኑሯችን የዛፍ ኑሮ ዓይነት መሆን አለበት። አንድ ዛፍ በክረምት ወራት ብዙ ቅጠሎችን ያወጣል። በበጋ ወራት ግን ፀሐይ ስለሚበዛበት ያን ሁሉ ቅጠል ያራግፋል። ዛፍ በበጋ ወራት ቅጠሉን የሚያራግፈው ለዘዴው ነው። በበጋ ወራት መሬቱ ስለሚደርቅ የዛፉ ሥሮች እንደልባቸው የሚመጡት በቂ ውሃ አያገኙም።

ስለዚህ በመጠኑ የሚያገኘውን ውሃ በቅጠሎቹ አማካይነት በብዛት እንዲወጣ አይፈልግም። ከዚህ በተለየ ዘዴም በመጠቀም ሕይወታቸውን የሚያቆዩ ዛፎች እንዳሉም እንወቅ። ቅጠሎቹ እንዳሉ ከቆዩ ውሃ በብዛት ከዛፉ ስለሚወጣ ዛፉ ሊደርቅ ይችላል። ይህ እንዳይደርስበትና ሕይወቱ እንዳይጠፋ ቅጠሎቹን መስዋዕት በማድረግ የመከራንና የድርቅ ዘመንን በትዕግሥት ያሳልፋል። ከቅጠሎቹ ጋር ግን አብሮ አይሞትም። ግን አልፎ አልፎ የሚሞት አይታጣም።

ስንቶቻችን ነን በሚገጥሙን ችግሮች ድል የምንሆነውና የምንሞተው? ስንቶቻችንስ ነን እንደ ዛፉ ዘዴ ፈጥረን ከክፉና ከጅል ቀን የምናመልጠው? የችግር ብዛት ትምህርት መስጠት አለበት እንጂ ብስጭትን አስከትሎ ፀጉር ማስነጨት የለበትም። አንድ ሰው ትንሽ እክል ሲያጋጥመው ያንን ካሳለፈ፣ ትልቁም በመጣ ጊዜ ማሳለፍ አያዳግተውም።
>>>
━━━━━━━━
ኑሮ በዘዴ - የጭንቀትህ ቁልፍ
ከዮሐንስ ገብረጻድቅ
ገፅ 66 - 68

https://t.me/Ethiobooks
337 views07:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-22 12:02:46 አቡ በክር አል-ሰዲቅ - 2 የመጨረሻው!
788 views09:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-22 11:00:12 አቡ በክር አል-ሰዲቅ - 1
806 views08:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-22 10:57:21
   አቡ በክር አል-ሰዲቅ
        ━━━━━━━
«የ መ ጀ መ ሪ ያ ው  ከ ሊ ፋ»
         @ethiobooks
809 views07:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-21 08:13:09
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታይ  ቤተሰቦቻችን!
እንኳን ለ1444ኛው የኢድ-አል ፈጥር (ረመዳን) በአል አደረሳችሁ!

በአሉ
የሰላም፣
        የደስታና
                የጤና
እንዲሆንላችሁ ልባዊ ምኞታችንን እንገልፃለን።
  
ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

https://t.me/Ethiobooks
393 views05:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-19 09:20:07 ጥላሁን ገሠሠ እኔ እንደማውቀው
    ════•✦•════
መስፍን ሀብተማርያም
'
>>>
ጥላሁን በጣም ውድ መኪኖችን ባልያዘበት ጊዜ በ70ዎቹ መጀመሪያ እየተበላሸች ታበሳጨው በነበረችው ሬኖ መኪናው እኔንና ብዙ ግጥሞች የገጠመለትን ክፍለ ኢየሱስ አበበን ይዞ ከወደ ለገሀር ስንመጣ ቸርችል ጎዳና ላይ መብራት አቆመን። መኪና ሲነዳ "ጎራው"ን፣ "ጉብልዬ"ን፣ "መላመላ"ን ለራሱ ማንጎራጎር ይወድ ነበር።

ከእነዚህ አንዱን ይመስለኛል ሲያንጎራጉር አረንጓዴ ሜርሰዲስ መሪ የጨበጠች አንዲት ቆንጆ ልጅ ፍዝዝ ብላ ስታዳምጥ አየን። ወዲያው ቀዩ ጠፍቶ አረንጓዴው በራ። መኪኖቹ ጉዞ ሲቀጥሉ ወጣቷ «ጥላሁን እንጉርጉሮህን ቀጥል፣ አትንቀሳቀስ። የትራፊክ እኔ እቀጣለሁ» ስትል ተነስተን ሄድን። ጓደኛዬ «ህ! ያንተ ድምጽ መኪናም ውስጥ ይፈለጋል፣ ቀይ መብራት ላይ እንኳ። አይ መታደል!» አለ። ...
-
አርቲስት ጥላሁን ገሠሠ በማኅበራዊ ሕይወት ውስጥ መሳተፍ ብቻ ሳይሆን መረዳጃ ማኅበር በመሳሰሉት ጉዳዮች ላይ አነሳሽ መሆንም ደስታው ነው። አንድ ጊዜ አሥር የምንሆን ሰዎች የመረዳጃ ማኅበር መሥርተን በነበረበት ወቅት እኔ የማኅበሩ ፀሐፊ ሆኜ ሕጉን ባረቅም በጠቅላላው ማኅበሩ ይንቀሳቀስ የነበረው በጥላሁን የቃል ሕግ ነበር።

እሱ ያለው ይፀድቃል! እሱ ያወገዘው ይሰረዛል። የሚያቀርባቸው ሃሳቦች የምናምንባቸው ቢሆኑም በአብዛኛው የሚገዛን ድምፁ ነበር። ከተጨቃጨቅን ሲያንጎራጉርልን ዝም እንላለን። ስብሰባ አቋርጦ መሄድ የሚፈልግም ካለ እሱ ሲያንጎራጉር ቁጭ ይላል።

ሦስት ዓመት ከቆየንበት የማኅበሩ ግንኙነታችን ገንዘብ ለማሰባሰብ የጥላሁን ዜማ ትልቅ ሚና ተጫውቷል። በኋላ «አንድ ዘፈን ስትጠይቁ ለማኅበሩ ሁለት ብር አስቀምጡ፣ ድጋሚ ስትጠየቁ አንድ ብር ያስጨምራል» የሚል ደንብ አወጣና የብር ዓይነት ጠረጴዛው ላይ ይከመር ጀመር። የደሞዝ ሰሞን ቢያንስ ብር 30 የማያወጣ አልነበረም። በአንድ ቀን ብር 70 ያስቀመጠም ከመካከላችን ነበር።

ጥላሁን ብዙ ብር እንድናዋጣ ሆን ብሎ ዘፈኑን ያሳጥረዋል። ያኔ ድጋሚ እንጠይቃለን። ካፒታላችን ትንሽ ቢሆንም የመረዳዳት ጅምራችን የሚያበረታታ ነበር። በኋላ ግን በቀይ ሽብር ምክንያት መሰባሰብ አደገኛ እየሆነ ስለመጣ ለጊዜው ተበታተንና የማኅበራችን ነገር አከተመለት።
-
በመጨረሻም የጥላሁን ዜማ በአንድ ምሽት ያመጣውን ውጤት ልገልፅላችሁ እወዳለሁ። ካዛንቺስ ያለ ጓደኛችን ቤት ሆነን ስናወጋ በድንገት አንድ ሴት ከጎረቤት ሮጣ መጥታ ሳሎኑን አቋርጣ መኝታ ቤት ስትገባና በሩን ስትዘጋ ባልዬው ተከትሎ መጣ። ጥላሁን «የጠላሽ ይጠላ» የሚለውን ዘፈን ያንጎራጉር ነበር። በስሜት ተውጠን እርጭ ብለን እያዳመጥነው ያንቆረቁረዋል። ባልዬው ልክ ተንደርድሮ ሲገባና ገላጋዮች ሲይዙት ሰውዬውን እያየ ጥላሁን ገና በካሴት ያላስቀረፀውን ዜማ ጣራው እስኪሰነጠቅ ይለቀዋል።

ሰውዬውም «ጥላሁን አለ እንዴ?» አለና እንደ መደንገጥ ብሎ ፊቱን ወደ እኛ አዞረ። አርቲስቱ ግን ቀጠለ። ሰውዬው ቁጭ አለ። ጥላሁን በዚህ ጊዜ (ሰውዬው ቁጭ ሲል) ዘፈኑን አቋረጠ። በሚያሳዝን አስተያየት መሬት መሬት እያየ «ወይ ቅዱስ ገብርኤል የጥልዬን ድምፅ ልስማበት ወይስ የእሷን ለከፋ» አለ። አንድ ጊዜ ሳቃችንን ለቀቅነው።
>>>
━━━━━━━━
የቡና ቤት ስዕሎችና ሌሎችም

https://t.me/Ethiobooks
267 viewsተስፋዬ መብራቱ, edited  06:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-17 09:08:46 ያ ገ ር ባ ህ ል
══ ❁ ══
ከፍቅሩ ኪዳኔ
'
ጥንት ልጆች ሆነን ባገራችን ባህል መሠረት የሚከበሩትን በዓሎች በሙሉ በደንብ እናከብር ነበር። ዋናው የወንዶች ልጆች በዓል በነሐሴ ወር የሚከበረው ቡሄ ነው። ለቡሄ ሳምንት ሲቀረው እያንዳንዳችን ጅራፍ ገምደን ስናጮህ እንውላለን እንጂ አንጋረፍም። በቅርብ የሚተዋወቁ የሠፈር ልጆች የራሳቸውን ቡድን አቋቁመው በቡሄ ማግስት ፀሐይ ሲጠልቅ ጀምረው ዱላቸውን ይዘው እየጨፈሩ ወደ ቤተሰብ ዘንድ እየሄዱ የቡሄ ዳቦና ፍራንክ በመሰብሰብ ያገኙትን ሁሉ ያለ ጭቅጭቅ ይካፈላሉ።

የኛ ሕዝብ ደግነቱንና ቸርነቱን የሚገልፀው በብዙ መንገድ በመሆኑ፣ በድሃም ሆነ በሀብታም ቤት፣ ልጆች ኖሩ አልኖሩ፣ እናቶች የቡሄ ዳቦን መጋገር እንደ ግዴታ በመውሰድ ወጣቱን ያስደስታሉ። የሚሰበሰበው ዳቦ ስለሚበዛ ለተቸገረ ማካፈል የተለመደ ነው። የቡሄ ጭፈራና ዘፈኖች ሆያ ሆዬና አሲዮ ቤሌማ ወግና ሥርዓት አላቸው። ሆያ ሆዬ ጉዴ፣ ጨዋታ ነው ልማዴ በማለት እውነት መናገር ነው።

የሴቶች ልጆች በዓል ደግሞ ከዕንቁጣጣሽ በዓል ጋር የተያያዘ ነው። ከሜዳ የሚቀጥፉትን አደይ አበባ ይዘው እየዘፈኑ አበባ መስጠት ገንዘብ ያስገኛል። ወንዶቹም የተለያዩ የአበባ ሥዕሎችን በቀለም በመሳል ለቅርብ ቤተሰብና ለዘመዶቻቸው በማበርከት ሣንቲም ያጠራቅማሉ።

ለመጀመሪያ ጊዜ ሸራ ጫማ የገዛሁት በዕንቁጣጣሽ ባገኘሁት ብር ነው። ፒያሳ የነበረው (አሁን የፈረሰው) ኪንግ ጆርጅ ቡና ቤት ገብቼ ኬክና አረንቻታ ገዝቼ የቀመስኩት በዚያን ወቅት መሆኑን አውቃለሁ። በመስቀል በዓል ሁሉም ችቦውን አዘጋጅቶ ወይም ገዝቶ እያንዳንዱ ሰው በአጥር ግቢው ውስጥ ከማቀጣጠሉ በፊት በየሠፈሩ ልክ እንደ ቡሄ ይጨፈራል። ያኔ ጉለሌ ጫካ ስለነበረው የአበባ፣ ዱላ፣ ጅራፍና ችቦ ችግር አልነበረም።

ገናን ሁሉም ከቤተሰቡ ጋር የሚያከብር ሲሆን፣ በጥምቀት ሁላችንም የሠፈራችንን ታቦት (ዮሐንስን) ተከትለን ወደ ጃንሆይ ሜዳ በመሄድ ብርድ እየፈደፈደን እናድራለን። በዚያን ጊዜ ሰዓት እላፊ ስለነበረ ከእኩለ ሌሊት በኋላ መነቃነቅ አይቻልም። ከቤታችን ውጭ የማደር ነፃነት የምናገኘው በጥምቀት በዓል ምክንያት ነው። በየሠፈራችን ከሚገኘው ዓረብ ሱቅ ዕቃ ለመግዛት ስንላክ ዓረቡ "ምራቂ" ብሎ ከሚሰጠን ብትን ስኳር በስተቀር ከረሜላ፣ ሸንኮራ አገዳ፣ ቴምር፣ ስኳር ድንች፣ ጉልባን፣ ተልባና እርጎ እንደልብ የምናገኘው በበዓላት ወቅት ነው።

በፋሲካ ትላልቆቹ ስለሚጾሙ እኛም በግድ እንጾማለን። ለፋሲካ ወደ ቤተክርስትያን መሄድ የተለመደ ነው። ትላልቆቹ ኃጢአታቸውን ከተናዘዙ በኋላ ስንት መስገድ እንዳለባቸው ሲነገራቸው፣ እኛ ደግሞ ተሰባስበን አንዱ የሌላውን ኃጢአት እያጋለጠ ስግደቱን ወደ ስፖርት ቀይረን ስንሰግድ ውለን እንገባለን። እግዚአብሔርም አልተቆጣንም። ...

በኛ ዘመን ልጆች ካባትና እናታቸው ጋር ወይም ከትላልቆቹ ሰዎች ጋር አብረው መብላት ክልክል ስለነበረ ቅልጥሙና የዶሮው ቆዳ ለኛ አይደርሰንም። እኔ ልጄን ሳሳድግ ጥሩ ጥሩውን ብልት እየመረጥኩ ስሰጠውና የፈለገውን ብስኩት፣ ጀላቲና ፉርኖ ገዝቼ ሳበላው ዕድለኛ መሆኑን የሚያውቅ አልመሰለኝም።

የዶሮ ዳቦ የሚደፋው ለፋሲካ ስለነበር ዕድል ያጋጠመው ዕንቁላል ያገኛል። ሌሊት ተነስተን ለማስፈሰክ ጠዋት ስንነሳ ፍትፍታችንን ግጥም አድርገን መብላት ነው። እኔ ከዶሮ ወጥ ይልቅ የሥጋ ወጥ የምመርጠው በእንጀራ የሚጠቀለል የተከተፈ ሥጋ ስለሚገኝበት ነው።
በዚያ በልጅነት ዕድሜ ቤተሰቦቻችን ናቸው ግብረ ገብን፣ ጨዋነትን፣ ታዛዥነትንና ሰው አክባሪነትን ያስተማሩን። ለኑሮ አስፈላጊ የሆኑትን ፀባይና ልምድ ያወረሱን።
>>>
━━━━━━━━
የፒያሳ ልጅ
ገፅ 25 - 27

https://t.me/Ethiobooks
745 viewsተስፋዬ መብራቱ, 06:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-16 07:28:55
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታይ ቤተሰቦቻችን!
እንኳን ለ2015 ዓ.ም. የጌታችን፣ የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳኤ በአል አደረሳችሁ!

ዓውደ ዓመቱ
የሰላም፣
የደስታና
የጤና
እንዲሆንላችሁ ልባዊ ምኞታችንን እንገልፃለን።

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

https://t.me/Ethiobooks
831 viewsተስፋዬ መብራቱ, 04:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-14 12:00:51 የ ጅ ራ ፍ ን ቅ ሳ ት
━━━━━━
ኤፍሬም ስዩም
@ethiobooks
586 viewsተስፋዬ መብራቱ, 09:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-13 17:22:31
ጉ ል ባ ን
═ ✦ ═

ጉልባን ከባቄላ ክክ፣ ከስንዴ ወይንም ከተፈተገ ገብስ ጋር አንድ ላይ ተቀቅሎ የሚዘጋጅና የጸሎተ ሐሙስ ዕለት የሚበላ ንፍሮ ነው። በጸሎተ ሐሙስ በቤት ውስጥ ከሚፈጸሙ ተግባራት አንዱ ጉልባን ማዘጋጀት ነው።

ጉልባን እስራኤላውያን ከግብጽ ባርነት ሲወጡ በችኮላ መጓዛቸውን የምናስታውስበት ከእስራኤላውያን የመጣ ትውፊታዊ ሥርዓት ነው። በአገራችን ኢትዮጵያ አብዛኞቹ የትውፊት ክንዋኔዎች የብሉይ ኪዳን መነሻ ስላላቸው ይህ ሥርዓት ዛሬም በኢትዮጵያውያን ምእመናን ዘንድ ይከበራል።፡

ጉልባን እስራኤላውያን ከባርነት በወጡ ጊዜ አቡክተው፣ ጋግረው መብላት አለመቻላቸውን ያስታውሰናል። በወቅቱ ያልቦካውን ሊጥ እየጋገሩ ቂጣ መመገብ፣ ንፍሮ ቀቅለው ስንቅ መያዝ የመንገድ ተግባራቸው ነበር። ይህን ታሪክ ለማሰብም በሰሙነ ሕማማት በተለይም በጸሎተ ሐሙስ ቂጣና ጉልባን ይዘጋጃል።

በጸሎተ ሐሙስ የሚዘጋጀው ጉልባንና ቂጣ ጨው በዛ ተደርጎ ይጨመርበታል። ይኸውም ጨው ውኃ እንደሚያስጠማ ዅሉ፣ ጌታችንም በመከራው ወቅት ውኃ መጠማቱን ለማስታወስ ነው።
━━━━━━━━
ምንጭ፦ ዊኪፒዲያ

https://t.me/Ethiobooks
401 viewsተስፋዬ መብራቱ, 14:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ