Get Mystery Box with random crypto!

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiobooks — ከስነ-ፅሁፍ ዓለም
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiobooks — ከስነ-ፅሁፍ ዓለም
የሰርጥ አድራሻ: @ethiobooks
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 12.79K
የሰርጥ መግለጫ

የስነ-ፅሁፍ ቻናላችንን
👉 https://t.me/Ethiobooks ተቀላቀሉ።
ለማንኛውም አስተያየት እና ማስታወቂያ
👉 @firaolbm
@tekletsadikK
እናመሰግናለን።
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2023-07-15 10:45:44
ኒል አርምስትሮንግ እና
አፖሎ 11 - ጉዞ ወደ ጨረቃ
━━━━━━
@ethiobooks
1.3K viewsተስፋዬ መብራቱ, 07:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-15 09:38:14
╔══ ══╗
ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

'
የቻናላችን

https://t.me/Ethiobooks ቤተሰብ ይሁኑ፣ ለወዳጅ ጓደኞችዎም 'share' ያድርጉ።


ለማንኛውም አስተያየት፣ ስነ-ፅሁፋዊ ጥቆማና ማስታወቂያ ፦
@firaolbm እና
@tekletsadikK ን ተጠቀሙ።
በአክብሮት እንቀበላለን።

አብረን እንዝለቅ።
@ethiobooks
╚══ ══╝
1.3K views06:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-12 10:00:16 እስኪ እንመሰጋገን
═══✦═══
➠ ➠ ➠
ፊቷ በእሳት የተቃጠለ እናት የነበረችው አንድ ልጅ ነበረ። ምንጊዜም ሲወራ የሚሰማው ስለ እናቱ የተቃጠለ ፊት ስለነበረ በእናቱ ያፍር ነበር። ለጓደኞቹም ስለ እናቱ አይናገርም፣ እናቱም ከጓደኞቹ ጋር እንድትገናኝ አይፈልግም ነበር። በኋላም አድጎ ትልቅ ደረጃ ላይ ሲደርስ እናቱን የቤት ሠራተኛዬ ናት ብሎ ነበር የሚያስተዋውቃት። እናቱም ነገሩ ሁሉ ከምትታገሠው በላይ ሲሆንባት አንድ ቀን ጠራችው።

«ለመሆኑ ፊቴ ለምን እንደተቃጠለ ታውቃለህን?» ስትል ጠየቀችው። እርሱም ምንም እንደማያውቅ ነገራት። እርሷም እንዲህ አለችው፤ «ልጅ ሆነህ አንተን ቤት ውስጥ አስተኝቼ ከውጭ እህል ሳሰጣ እሳት ተነሣ። የእሳቱ ነበልባልም በአንድ ጊዜ ቤቱን ሞላው።

እኔም ያንተ መቃጠል ስላሳሰበኝ እየጮኽኩ ወደ ውስጥ ገብቼ በልብስ ሸፍኜ አንተን አወጣኹህ። አንተን አድናለሁ ብዬ እኔ ተቃጠልኹ። ዐየኽ፣ ያን ጊዜ ለራሴ ባስብ ኖሮ እተውኽና ትቃጠል ነበር። እኔ ግን ከራሴ በላይ ላንተ በማሰቤ በእሳት ውስጥ ገብቼ አወጣኹህ። የእኔ ውበት ካንተ ላይ ነው፤ ያንተ ጠባሳ ደግሞ ከእኔ ላይ ነው።» ብላ ነገረችው።

ጠባሳችንን ተሸክመው ምስጋናውን ያጡ ስንት ወገኖቻችን አሉ። ክፉ ክፉውን ብቻ እየተነጋገርን ለማመስገን፣ ለማክበር፣ ለማድነቅ፣ ለማበረታታት ዕድልኮ አላገኘንም። እስኪ በዓመት አንድ ቀን የምስጋና ቀን ይኑረን።

በመንግሥት ደረጃ፣ በፓርቲ ደረጃ፣ በአካባቢ፣ በትምህርት ቤት፣ በቤተሰብ መልካም የሠሩ፣ ለሕይወታችን መቃናት አስተዋፅኦ ያደረጉ፣ በበጎ ሐሳባቸው እና በበጎ ሥራቸው አርአያ የሚኾኑ፣ ለአገራቸውና ለሕዝባቸው የሚችሉትን ሁሉ ያደረጉ ሰዎች የሚመሰገኑበት ቀን

የግድ ተስማምተን፣ ኮሚቴ አቋቁመን መምረጥ የለብንም። የሚያደርገው ካለ ግን እሰየኹ። በግላችን፣ በአካባቢያችን፣ በቤተሰባችን እኛ፣ መልካም ሠርቷል፣ መልካም ሥራውንም ልናደንቅለት፣ ልናውቅለት ይገባል። "በርታ ጠንክር" ልንለው ያስፈልጋል፤ የምንለውን ሰው ቢቻል በአካል፣ ባይቻል በስልክና በደብዳቤ «እግዜር ይስጥልን» የምንልበት - የምስጋና ቀን

በቤተሰብ ደረጃ በዚያ ዓመት በጠባዩ፣ በሥራው፣ በትምህርቱ ወዘተ... የተሻለ ኾኖ የተገኘውን ከማመስገን ጀምሮ ሌላው ቀርቶ ባል እና ሚስት እንኳን መጨቃጨቅ አቁመው አንዱ ለሌላው ያደረጉላቸውን በጎ ነገር የሚያወሩበት የሚያደንቁበት ቀን። ከመመራረር፣ ከመተቻቸት፣ ከመሰዳደብ፣ ከመወራረፍ በጎ በጎውን የምናወራበት ቀን። ...

አበው «ወድሶ ለሰብእ በዘኢኮነ ድልወ» ይላሉ። ይኸውም "ሰውን በማይ'ገባው ነገር እንኳን ቢኾን አመስግነው" ማለት ነው። "ሳላደርግ እንዲህ ያመሰገነኝ ባደርገውማ ይበልጥ እመሰገናለሁ" ብሎ እንዲተጋ!
━━━━━━━━
የሁለት ሀውልቶች ወግ እና ሌሎች
ዳንኤል ክብረት
ገፅ 174 -176
2002 ዓ.ም

https://t.me/Ethiobooks
472 viewsተስፋዬ መብራቱ, edited  07:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-10 11:30:28 ጁልየስ ኔሬሬ - 2 የመጨረሻው!
109 viewsተስፋዬ መብራቱ, 08:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-10 11:00:06 ጁልየስ ኔሬሬ - 1
165 viewsተስፋዬ መብራቱ, 08:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-10 10:51:53
ጁ ል የ ስ ኔ ሬ ሬ
━━━━━
«በምርጫ አስተማሪ፣
በግዴታ ፖለቲከኛ»
@ethiobooks
175 viewsተስፋዬ መብራቱ, 07:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-09 09:01:53
በ1840 ዓ.ም. ለመጀመሪያ ጊዜ አኔስቴሲያ ወይም በቀዶ ጥገና ሕክምና ጊዜ ሕመም የማያሰማው መድኃኒት ተፈልስፎ በወጣበት ጊዜ ሴቶች በምጥ ጊዜ እንዳይጠቀሙበት በማለት የእንግሊዝ ቄሶች ተቃውሞ አቀረቡ።

ለዚህም ያቀረቡት ማስረጃ «የመጀመሪያዋ ሴት ሔዋን የተከለከለውን ቅጠል በልታ በተረገመች ጊዜ "ልጆችን በጭንቅ ትወልጃለሽ" ተብላ ስለተረገመች ጭንቋን የሚያስወግድ መድኃኒት ማድረግ የለባትም።...» የሚል ነበር።

በዚህ ሁኔታ ሕዝቡና ቄሶች በመከራከር ላይ እንዳሉ በ1853 ዓ.ም. ንግሥት ቪክቶሪያ በምጥ ተያዙ። ንግሥቲቱ ሰባተኛ ልጃቸውን ለመውለድ ምጥ በተያዙበት ጊዜ በአኔስቴሲያ ተጠቀሙ። ይህ ከሆነ በኋላ ክርክሩ ቆመ። ከዚያም በኋላ ሁሉም ሴቶች መጠቀም ጀመሩ።
            ✦     ✦     ✦

የእግሊዝ ንግሥት የነበሩት ንግሥት ቪክቶሪያ እናታቸው የጀርመን ልዕልት ናቸው። በዚህ ምክንያት ቪክቶሪያ በጀርመንኛ ቋንቋ እየተነጋገሩ አደጉ። በእንግሊዞች ላይ በነገሡም ጊዜ እንግሊዘኛ ቋንቋን ማጥናት ጀመሩ።

ንግሥት ቪክቶሪያ 64 ዓመት በእንግሊዝ ሕዝብ ላይ ነግሠው ሲቆዩ እንግሊዘኛ ቋንቋን አጣርተው መናገር አይችሉም ነበር።
━━━━━━━━
ጳውሎስ ኞኞ
ስድስተኛው አስደናቂ ታሪኮች

https://t.me/Ethiobooks
647 viewsተስፋዬ መብራቱ, 06:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-07 10:00:03 ከፍቶሽ እንዳላይ
══ ❁ ══
ዳን አድማሱ
@ethiobooks

ከፋኝ ያንቺን እንባ ከዓይንሽ ሳየው
አዝኗል ለካስ ልብሽ ደስታም የለው
እንኳን አዝነሽለት ይህን ዓለም
ስቆም የሚሞላ ከቶ አይደለም
ለሀዘን ፊት አትስጪው ጭራሽ
ሕይወት ላትኖሪያት ደግመሽ
ለኔ ደስታዬ ነው ብታዪ
ምንም ዓይኔ ከፍቶሽ ባላይ

ጊዜን ላይገዛ ሰው ላይመልሰው
ቢያዝን ቢጨነቅ ትርጉም ላይሰጠው
ያልፋል ይሄ ቀን አንቺን ያለፋው
እስከዚያው ዓይንሽ ማንባቱ ይብቃው

ቀኑም ቢጨልም ሰማዩም ቢመሽ
ጠዋት ይሆናል ይነጋል አይዞሽ
ነገን ለሚያስብ ተስፋን ላዘለ
ሲያድር ከዛሬ ሌላ ቀን አለ
[ከፍቶሽ እንዳላይ ... እንዳላይ
አዝነሽ እንዳላይ ... እንዳላይ] 2×


ከፋኝ ያንቺን እንባ ከዓይንሽ ሳየው
አዝኗል ለካስ ልብሽ ደስታም የለው
እንኳን አዝነሽለት ይህን ዓለም
ስቆም የሚሞላ ከቶ አይደለም
ለሀዘን ፊት አትስጪው ጭራሽ
ሕይወት ላትኖሪያት ደግመሽ
ለኔ ደስታዬ ነው ብታዪ
ምንም ዓይኔ ከፍቶሽ ባላይ

ፀሐይ ባትወጣ ቢያይል ደመናው
ቢከብድሽ እንኳን እሾህ ጋሬጣው
ለቀን አለቃም ቀን አለውና
አሮጌው በአዲስ ይተካል ገና

ቀኑም ቢጨልም ፀሐዩም ቢመሽ
ጠዋት ይሆናል ይነጋል አይዞሽ
ነገን ለሚያስብ ተስፋን ላዘለ
ሲያድር ከዛሬ ሌላ ቀን አለ
[ከፍቶሽ እንዳላይ ... እንዳላይ
አዝነሽ እንዳላይ ... እንዳላይ] 6×||


@ethiobooks
985 viewsተስፋዬ መብራቱ, 07:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-07 09:45:05
878 viewsተስፋዬ መብራቱ, 06:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-05 16:00:12 «ግን ለካንስ ልጅቷ ጽጌረዳ አልያዘችም። የልጅቷ ውበት ወደኔ አቅጣጫ ከመምጣቷ ጋር ተደማምሮ... ዋናውን ነገር፣ ጽጌረዳውን አለመያዟን ረስቼዋለሁ። ወደ ልጅቷ አንድ ተጨማሪ እርምጃ ጠጋ እንዳልኩ፣ 'ወደኔ አቅጣጫ ነው ካፒቴን?' በሚል አስተያየት የጎንዮሽ አይታኝ ወደ ጎን ታጠፈች።

«ይሄኔ ነው ታዲያ ሆሊስ ሜይነልን ያየሁዋት። ልጅቷ በመጣችበት አቅጣጫ ኮቷ ላይ ቀይ ጽጌረዳ አድርጋ ቆማለች። በግምት በ40ዎቹ መጨረሻ አካባቢ ያለች ሴት ነች። ሽበት የወረሰው ጸጉሯ ካረጀ ባርኔጣዋ ተርፎ ይታያል። ድብልብል እግሯ ሶል አልባ ጫማዋ ውስጥ ተሰንቅሯል። ቆንጅዬዋ ልጅ እየተውረገረገች በጎን በኩል አልፋኝ እየሄደች ነው።

«ልቤ ለሁለት ተከፈለ፡፡ በአንድ ጎን ይህቺን አሮጊት ወዲያ ብለህ ቆንጅዬዋን ልጅ ተከተላት ሲለኝ፣ ሌላኛው ደግሞ 'አይሆንም ላለፉት 13 ወራት የልብህ ወዳጅ ሆና ወደ ሰነበተችው ከፊት ለፊትህ ቀይ ጽጌረዳ ይዛ ወደምትጠብቅህ ወደ ሆሊስ ሜይነል ሂድ' ይለኛል። አላመነታሁም። ቆንጅዬዋን ልጅ ትቼ ወደ ሆሊስ ሜይነል አቅጣጫ ቀረብኩ። ሆሊስ ባለችበት ቆማ ቀዩን ጽጌረዳ እንደያዘች እየጠበቀችኝ ነው።

«መጨማደድ የጀመረው ፊቷ እርጋታ ሰፍኖበታል። ምንም እንኳ የወጣትነት እሳታቸው ቢዳፈን አይኖቿ ሞቃትና ሩህሩህ ብርሃናቸውን ይረጫሉ፡፡ በቆዳ የተጠረዘውንና ለትውውቃችን መሰረት የሆነውን ያንን ከምንም በላይ የማስበልጠውን መጽሐፍ ይዣለሁ፡፡ ቢሆንም ግን ሆሊስ እንዲህ በዕድሜ የገፋች ሴት ትሆናለች ብዬ ስላልጠበቅኩ ውስጥ ውስጡን ክፉኛ ተከፍቼያለሁ። ግን መከፋቴን ለመደበቅ እየታገልኩ ወደ ሆሊስ ቀረብ ብዬ፣ “ካፒቴን ጆን ብላንቻርድ ነኝ” አልኳት…“ባልሳሳት ሚስ ሜይነል ነሽ። ስለተገናኘን በጣም ደስ ብሎኛል። እራት አብረን መብላት እንችላለን?”

«ይሄኔ የሴትየዋ ፊት ይህ ነው በማይሉት መደነቅና ግራ መጋባት እንደተጥለቀለቀ "ጉዳዩ ምን እንደሆነ አላውቅም የኔ ልጅ... ብቻ አሁን ያለፈችዋ... ባለ ወርቃማ ጸጉሯ ቆንጅዬዋ ልጅ ነች… ይህንን አበባ ያዢ ብላ የሰጠችኝ። ጉዳዩ ጨዋታ ብጤ ነው... ማረጋገጥ የምፈልገው ነገር ስላለ ነው፤ ነው ያለችኝ። እራት ከጋበዘሽ ዋናውን ጎዳና ተሻግሮ ባለው ሬስቶራንት ውስጥ እንደምጠብቀው ንገሪው ብላኛለች። እኔ ነገሩ ምኑም አልገባኝም የኔ ልጅ።" 

«ሚስ ሜይነል በፈጠረችው ጥበብ ተደምሜ ቀረሁ። ለነገሩኮ እውነተኛው የልብ መንገድ በግልጽ በሚታየው ውጫዊ መብረቅረቅ መች ይታለልና። ሆ ሴይ እንዳለው “ማንን እንዳፈቀርክ ንገረኝና ማን እንደሆንክ እነግርሃለሁ።” ነው ነገሩ። የሚስ ሜይነል ጥበብ ነፍሴን እያሞቀው ጎዳናውን አቋርጬ ወደ ሬስቶራንቱ አቀናሁ…!»
━━━━━━━━
ግሩም የዓለማችን ምርጥ ታሪኮች
ህዳር 2010 ዓ.ም.

https://t.me/Ethiobooks
1.2K viewsተስፋዬ መብራቱ, 13:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ