Get Mystery Box with random crypto!

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiobooks — ከስነ-ፅሁፍ ዓለም
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiobooks — ከስነ-ፅሁፍ ዓለም
የሰርጥ አድራሻ: @ethiobooks
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 12.79K
የሰርጥ መግለጫ

የስነ-ፅሁፍ ቻናላችንን
👉 https://t.me/Ethiobooks ተቀላቀሉ።
ለማንኛውም አስተያየት እና ማስታወቂያ
👉 @firaolbm
@tekletsadikK
እናመሰግናለን።
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 8

2023-04-03 10:01:58 (የዐባይ ውኃ ብልሃርዚያ ያስይዛል!?)

«እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በ2018 ዓ.ም. ሽራይን አብደል ዋሂድ የተባለች የግብፅ ታዋቂና ተወዳጅ ዘፋኝ በተባበሩት ዐረብ ኢሚሬትስ ውስጥ ታላቅ ኮንሰርት ተዘጋጅቶላት ታዋቂ የሆነውንና ስለ ዐባይ ወንዝ ግርማና ፍቅር የሚያወሳውን ዘፈኗን ለአድናቂዎቿ ታቀነቅናለች። የዘፈኑ መጠሪያ "Haven't You Ever Drunk from the Nile?" የሚል ሲሆን፤ የዘፈኑ ይዘት ከሞላ ጎደል "ከዐባይ ውኃ የጠጣ ሰው የትም ቢሆን ተመልሶ መምጣቱ አይቀርም" የሚል ነው።

ዘፈኑን በስሜት ዘፍና ስትጨርስ አድናቂዎቿ እንድትደግምላቸው በጩኸትና ፉጨት ይጠይቃሉ። ጥያቄውን ተቀብላ ደግማ ዘፈነች። አሁንም ስትጨርስ እንደገና እንድትዘፍን ለሦስተኛ ጊዜ ተጠየቀች። በዚህ ጊዜ ከመደጋገም ይልቅ ወደ ሌሎች ዘፈኖቿ መሄድ ስለፈለገች ጉዳዩን በቀልድ መልክ ለታዳሚዎቿ፦ "ወዳጆቼ! የዐባይን ውኃ ደጋግሞ መጠጣት ብልሃርዚያ ያስይዛል፤ ስለዚህ ይቅርባችሁ። ይልቅ ሌላ የምንጭ ውኃ ጠጡ።" አለች።

ይህንን እንደተናገረች ከኢሚሬትስ እስከ ግብፅ ካይሮ፣ ከተራ ሙዚቃ አድናቂ እስከ ሀገሪቱ ፖለቲከኞች ጆሮ ወሬው በብርሃን ፍጥነት ተዳረሰ።

ሽራይን ታላቁን ወንዝ ዐባይን በመድፈሯና ክብሩን ዝቅ በማድረጓ ተከሰሰች። ኮንሰርቷ እንዲቋረጥ ተደረገ። የግብፅ ከፍተኛው ፍርድ ቤት የእስር ብይን አስተላለፈባት። አየህ የዐባይን ክብር በግብፅ!» ...

«እኛ ሀገር የራሳችንን ድክመት ወደ ወንዙ አስተላልፈን፦ 'ዐባይ ማደሪያ የለው ግንድ ይዞ ይዞራል!' በማለት እንሳለቃለን። እውነታው ግን ለዐባይ ማደሪያ ያልሰጠነው እኛ ነን። እናም የችጋር ግንድ ይዘን የምንዞር እኛ እንጂ እርሱማ አስዋን ላይ ማደሪያ ከተበጀለት ቆየ እኮ!» ...

«እናም ስለ ውኃ ባለን ደካማ የሥነ-ልቡና ውቅር ምክንያት ኢትዮጵያ ሀገራችን የዚህ ተአምራዊ ፍጥረት መፍለቂያና ማከማቻ ብትሆንም፤ አሁንም ድረስ ውኃ ታቅፈን በድርቅ እንሰቃያለን፣ ኃይል ቀብረን በጨለማ እንኖራለን።» ...

«ልብ በል! ... ከኢትዮጵያ ወደ ሌላ የሚፈስ እንጂ ከሌላ ወደ ኢትዮጵያ የሚመጣ ወንዝ አንድም የለም። ኢትዮጵያ ወንዞቿ ከተቀደሰው ማህፀኗ ፈልቀው ከእርሷ ወጥተው የሚሄዱ እንጂ ከሌላ ቦታ መንጭተው የሚመጡ አይደሉም። የኢትዮጵያ ወንዞች ደግሞ አፈርና ማዕድን የታደሉ የእናት ጡት ማለት ናቸው። የኢትዮጵያ ወንዞችና ጅረቶች ከአካል ከገላዋ የሚመነጩ፣ ከውስጥ ከሕዋሷ የሚቀዱ፤ ለእኛ እንዲሆኑን፣ እንዲያሳድጉን፣ እንዲያጎለምሱን ከፈጣሪ የተሰጡን ስጦታዎች ነበሩ።» ...
>>>
━━━━━━━━
ሚተራሊዮን
ዓለማየሁ ዋሴ እሸቴ
ጥር 2014 ዓ.ም.
187 - 189

https://t.me/Ethiobooks
698 viewsተስፋዬ መብራቱ, edited  07:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-01 12:00:19 ሞህሴን ፋክሪዛዴህ - 3 የመጨረሻው!
431 viewsተስፋዬ መብራቱ, 09:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-01 11:30:18 ሞህሴን ፋክሪዛዴህ - 2
482 viewsተስፋዬ መብራቱ, 08:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-01 11:00:16 ሞህሴን ፋክሪዛዴህ - 1
515 viewsተስፋዬ መብራቱ, 08:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-01 10:54:24
  ሞህሴን ፋክሪዛዴህ ማሃባዲ
             ━━━━━━
      «ሳይንቲስቱ ለምን ሞተ?»
            @ethiobooks
529 viewsተስፋዬ መብራቱ, 07:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-01 10:54:06
482 viewsተስፋዬ መብራቱ, 07:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-31 09:00:52
ይሄ ጫማ እኔ ነኝ
══✦══
አሌክስ አብርሃም
'
ከላይ ከባድ ሸክም ግዙፍ የሰው ኪሎ
ከታች ደግሞ መሬት ያውም መሬት ግሎ
በሁለቱ መሀል ይህ ጫማ ተጣብቆ
ያረጀ ዕለት ነው የሚጣለው ወልቆ
.
እናም
.
ይሄ
ይህ ጫማ እኔ ነኝ
የሰዎችን ሀሳብ በግድ የተጫንኩኝ
ከሕይወት እግር ላይ እስክጣል ወልቄ
ከባለ ጊዜ'ና ህሊናዬ መሀል ያለሁ ተጣብቄ።
═══════

https://t.me/Ethiobooks
455 viewsተስፋዬ መብራቱ, 06:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-29 12:00:08
ጥ ር ስ



ጥርስና ከናፍር፣ ቢደጋገፍ ያምር።


ያለ ጥርስ ቆሎ፣ ያለ ጓድ አምባጓሮ።


የጥርስ እድፍ፣ የራስ ጉድፍ።


ጥርሰ ገጣጣ ሲሞት፣ የሳቀ ይመስላል።


ያላንድ የላት ጥርስ፣ በዘነዘና ትነቀስ።


ጥርሴስ ልማዱ ነው፣ ዓይኔን አታስቀው።


የጥርስ ደም ሆነባት።


በኔውም ጥርስ አልተሳቀበትም።


ከጥርስ መንጋጋ፣ ከመኝታ አልጋ።


ልጅ ከጦረው፣ ጥርስ የጦረው።


ጥርስ ያደቃል፣ ጥርስ ያደምቃል።


የሞኝን ጥርስ ብርድ ፈጀው።


ጥርስ የሌላት ጥርስ ያላትን አነካከስ አስተማረች።


ያለ ጥርስ አይነክሱ፣ ያለ ዳኛ አይከሱ።


ጥርስ የገባ ስጋ ሆነ።


የተነቃነቀ ጥርስ፣ ሳይወልቅ አይቀርም።


የምበላው ሳጣ፣ ልጄ ጥርስ አወጣ።


በሰም ያጣበቁት ጥርስ፣ ቢስቁበት አያደምቅ፣ ቢያኝኩበት አያደቅ።

      
   ነገር በምሳሌ
@ethiobooks
371 viewsተስፋዬ መብራቱ, 09:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-28 10:00:19 ሙ ጀ ሌ
═ ✦ ═

ሙጀሌ የእግርን ጣት ስር ቦርቡራ ገብታ ውስጥ ውስጡን የእግርንና አልፎ አልፎም የእጅን ጥፍሮች ጭምር የምትነቃቅል ጠንቀኛ መቅሰፍት ናት። በተደጋጋሚ በሙጀሌ የተጠቃ እግር ቅርጹ ስለሚለወጥ አያምርም (ውበቱን ያጣል)። ደገኛ ወንድ፤ ሴት ለማጨት ቆላ የወረደ እንደሆነ (ሙጀሌ በቆላ ነው የሚገኘው) በቅድሚያ የሚያየው የሴቷን እግር ነው። ከዚህ በመነሳት ይመስላል ሙጀሌን "ጋብቻ ከልክል" ይሏታል።

ከዕለታት በአንዱ ቀን አንዱ ደገኛ ሴት ልጅ ለማጨት ቆላ ይወርዳል። ልጅቷን ሲያያት በጣም ቆንጆ ናት። ቀስ እያለ ከራስ ጠጒሯ ጀምሮ እየተመለከተ እግሯ ላይ ሲደርስ እንደፈራው ሆኖ አገኘውና ያ በርቶ የነበረው ፊቱ ጥ'ቁር አለ። ቆንጆዋም የሰውየውን ሁኔታ ስትከታተል ነበረችና ሁኔታው ገብቷት
"እነዚህ የደጋ ሰዎች ውሻ ይመስል የሰው እግር መመልከት ይወዳሉ።" አለች ይባላል።
~
በተመሳሳይ አንዱ ደገኛ ቆላ ወርዶ ከወገብዋ በላይ ይህ ቀረሽ የማትባል ወጣት አግኝቶ ለጋብቻ ሊጠይቃት ፈልጎ ጠጋ ሲላት እግሯ በሙጀሌ እንዳይሆን ሆኖ ቢያገኘው ጊዜ፦
ሲሰራሽ ዋለና እግዜር ቢታክተው፣
ከወደ እግርሽ ሲደርስ አለሽ እንደመተው፤
በሙጀሌ ካስማ የተመታው ጣትዋ፣
ወረንጦ ለሌለው አይድሩም እናትዋ።
በማለት ገጠመ። አጅሪትም የዋዛ አልነበረችምና፦
እንዳሻህ ተናገር ዕድሜ ለኮፍ ጫማ፣
ውስጡን ማን አየልህ ያንተን እግርማ።
በማለት መለሰችለት። (ኮፍ ጫማ - ቦቲ ጫማ፣ ሽፍን ጫማ ማለት ነው።)
━━━━━━━━
ኅብረ-ብዕር - ሦስተኛ መጽሐፍ
ካሕሳይ ገብረእግዚአብሔር

https://t.me/Ethiobooks
652 viewsተስፋዬ መብራቱ, edited  07:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-27 10:00:15

❝ተውኔት በመደምደሚያ ትርዒት እንደሚዘጋ ሁሉ፣ የሕይወት ጉዞም በእርጅና ምዕራፍ ይቋጫል።❞
          ማርኩስ ቱልዩስ ሲሰሮ


❝የራስህ መግቢያ በር በቆሻሻ ተሞልቶ ሳለ፣ የጎረቤትህ ጣራ ላይ ስላለው በረዶ አቤቱታ አታሰማ።❞
          ኮንፉሺየስ


❝ "መሸነፍ" የሚለው ቃል ትክክለኛ ትርጉሙ "መውደቅ" ሳይሆን "ወድቆ መቅረት" ነው።❞
          ሜሪ ፒክፈርድ


❝የታላላቅ ሰዎች ሕልም ባለበት አይገታም፤ ነገር ግን ከነበረበት እየላቀ ይጎመራል።❞
          አልት ራድ ሎርድ


❝ድርጊት የሚፈጠረው ከመሰረታዊ ፍላጎታችን ውስጥ ነው።❞
          ሐሪ ኤ ኦቨርትሪት


❝የመጪውን ጊዜ መተንበያ ምርጡ ጊዜ፣ ጊዜውን ራሱን መፍጠር ነው።❞
          ፒተር ድራከር


❝አፍቅሮ መለየት አንጀት ቢያሳርርም፣
ጭራሽ ካለማፍቀር ሳይሻል አይቀርም።❞
          አልፍሬድ ቴኒስን

      
     ጥቅሶች
@ethiobooks
218 viewsተስፋዬ መብራቱ, 07:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ