Get Mystery Box with random crypto!

Ministry of Education Ethiopia

የሰርጥ አድራሻ: @ethio_moe
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 82.27K
የሰርጥ መግለጫ

This is Ministry of Education's Official Telegram Channel.
For more updates please visit www.facebook.com/fdremoe

Ratings & Reviews

5.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

3

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 32

2022-09-30 14:47:24
ትምህርት ሚኒስቴር እና ሰላም ሚኒስቴር በጋራ
ለመስራት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ።
------------------------------------------------------------------
ትምህርት ሚኒስቴር ከሰላም ሚኒስቴር ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሟል።

ስምምነቱንም የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ እና የሰላም ሚኒስትሩ አቶ ብናልፍ አንዷለም ተፈራርመዋል።

በስምምነቱ ወቅት ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ ሰላምን ለማረጋገጥ የሞራል መሰረት ያለውና በምክንያታዊነት የሚያምን ዜጋ መፍጠር እንደሚገባ ገልፀዋል ፡፡

በዚህ ዓመት ወደ ስራ በገባው አዲሱ ስርዓተ ትምህርት ግብረ ገብነት ትምህርት እንዲሰጥ መደረጉን የጠቆሙት ሚኒስትሩ ከሰላም ሚኒስቴር ጋር ተደረገው ስምምነትም ይህን በማጠናከር ሰላምን በዘላቂነት ለማስፈን እንደሚያስችል ተናግረዋል፡፡

ግብረገብነትና ምክንያታዊነት በጋራ አብሮ የመኖር ዋነኛ መሰረቶች በመሆናቸው ውጤታማና ሰፊ ስራ መስራት እንደሚጠይቅም ሚኒስትሩ ተናግረዋል ፡፡

የሰላም ሚኒስትሩ አቶ ብናልፍ አንዷለም በበኩላቸው የዜጎችን አስተሳሰብና አመለካከት፡ ባህሪ ለመቀየር እና የሰላም ባለቤት እንዲሆኑ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባ ገልፀዋል፡፡

ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር ዛሬ የተፈረመው የጋራ መግባቢያ ሰነድ ዓላማም በሀገሪቱ ባሉ ሁሉም ትምህርት ቤቶች አጠቃላይ የሰላም ግንባታ ዙሪያ ተቀናጅቶ በጋራ አብሮ ለመስራት እንደሚያስችልም ተናግረዋል፡፡

ሰላም በዘላቂነት የማስፈን ስራ ለአንድ ተቋም ወይም አካል ብቻ ሳይን በጋራና በመደጋገፍ የሚሰራ ስራ መሆኑንም ሚኒስትሩ ጠቁመዋል፡፡

ትምህርት ሚኒስቴር በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት በስነ-ምግባር የታነፀ ትውልድ ለማፍራት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል::
7.2K views11:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-26 16:30:31
የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤታማ እንዲሆን የኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች ሚናቸውን በተገቢው ሊወጡ እንደሚገባ ተገለጸ፡፡
--------------------------//---------------
የ2014 ዓ.ም 12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና በሚፈለገው ደረጃ ውጤታማ እንዲሆን የኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች እና ሚድያዎች ሚናቸውን በተገቢው ሊወጡ እንደሚገባ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ፒኤችዲ) ገልጸዋል፡፡

የትምህርት ሚኒስቴር ህዝብ ግንኙነትና ኮሙዩኒኬሽን ስራ አስፈፃሚ ከክልል እና ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የህዝብ ግንኙነትና ኮሙዩኒኬሽን ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ጋር በተለያዩ ወቅታዊ የዘርፉ ጉዳዮች ላይ ምክክር አካሂዷል፡፡

መድረኩ በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት፣ የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና፣ የተማሪዎች ምዝገባ የምገባ እና በጦርነት የተጎዱ ትምህርት ቤቶች በሚመለከቱ ርዕሰ ጉዳዮች ተግባቦት ላይ ያተኮረ ነው ።

ከ12ኛ ክፍል ፈተና በተመለከተ ተፈታኝ ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲዎቹ ፈተናውን ለመፈተን ሲመጡ ማድረግ ያለባቸውንና የሌለባቸውን የተከለከሉ ጉዳዮች እና አጠቃላይ ዝግጅቶችን በሚመለከት ማብራሪያ ተሰጥቷል፡፡

በመድረኩ የተገኙት የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር እሸቱ ከበደ የ2014ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና በውጤታማነት እንዲጠናቀቀቅ የኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች ለሚድያዎች ትክክለኛውን መረጃ ለህበረተሰቡ ተደራሽ በማድረግ ሚናቸውን ሊወጡ ይገባል ብለዋል፤

https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid02sxuFPu7Zxy7juFrmnGbhx1AdjB3nBQgSxzTsm6gj8m5xBFaCv8EF781dscVoWJYcl&id=100064682287722
3.5K views13:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-26 15:23:50
እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ አደረሳችሁ!

እ.ኤ.አ.በ2013 በተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ የሳይንስ እና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ)በማይዳሰስ ቅርስነት የተመዘገበው የመስቀል ደመራ በዓል ሕዝቦችን በማቀራረብ፣ መንፈሳዊ ዕሴቶችን በመጨመር ማኅበራዊ ፋይዳው የጎላ፣ በቱሪስት መዳረሻነቱም ገቢ በማስገኘት ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከተ የሚገኝ ነው።

በድጋሚ እንኳን አደረሳችሁ !

ትምህርት ሚኒስቴር!
3.8K views12:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-25 15:47:04 " ሪፖርተር ጋዜጣ በትምህርት ዘርፍ የሙስና ሥጋት የሆኑ ጉዳዮችን የሚለይ ጥናት ሪፖርት፣ በአግባቡ ሳይገነዘብ የጥናቱ ይዘትም ሆነ ውጤት የማይዳስሰውን ያወጣው ሪፖርት፣ የኮሚሽኑን እና የተቋማትን ዕውነታ ስለማይወክል ተገቢውንና ተጨባጭ መረጃ ላይ የተመሠረተ ማድረግ ያስፈልጋል። በሙስና መከላከል የሚዲያ ሚና ከፍተኛ መሆኑን እየተገነዘብን፣ በቀጣይም በተጨባጭ መረጃ ላይ የተመሰረተ የሚዲያ ሥራ በቅንጅት እንሥራ!"

ሳሙኤል ኡርቃቶ (ፒኤችዲ)
የፌደራል ስነምግባርና ጸረሙስና ኮሚሽነር

https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid0fREaNGwBza3CLbij4TP5EsxWhvqPppvMdXcJM9kHjrvpno43EMWvCZScm27reobcl&id=100069422490377
324 views12:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-23 15:57:53
ልዩ ፍላጎት ያላቸውን ተማሪዎች የትምህርት ሁኔታ ለማሻሻል ሁሉም ርብርብ ሊያደርግ እንደሚገባ ተጠቆመ
---------------------------------------------
(መስከረም 13/2015 ዓም ) 3ኛው አገር አቀፍ የልዩ ፍላጎት/አካቶ ትምህርት ጉባኤ እየተካሄደ ይገኛል፡፡

የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ፋንታ ማንደፍሮ ( ዶ/ር ) ጉባኤውን ሲከፍቱ ባስተላለፉት መልእክት የልዩ ፍላጎት ያላቸው ተማሪዎችን የትምህርት ሁኔታ ማሻሻል የሁሉንም ባለድርሻዎች ርብርብ ይሻል::

በመሆኑም ሁሉም ባለድርሻዎች ለልዩ ፍላጎትና ለአካቶ ትምህርት መሻሻል ቀጣይነት ያለው ርብርብ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ሚኒስትር ደኤታው አስገንዝበዋል፡፡

በ6ኛው የትምህርት ልማት ዘርፍ መርሃ-ግብር ለልዩ ፍላጎትና አካቶ ትምህርት ጉዳዮች ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት ከባለዘረፈ ብዙ ጉዳቶች አንዱ ሆኖ እንዲካተት መደረጉንም ሚኒስትሩ ተናግረዋል፡፡

መንግስት ለአካል ጉዳተኞች ትምህርት ትኩረት የሚሰጠውና ተግባራዊ የሚያደርገው ዓለም አቀፍ ስምምምነቶችን ስለተቀበለ ብቻ ሳይሆን ያላቸውን እምቅ ክህሎትና ችሎታ ተጠቅመው የሀገር ልማትና እድገት ላይ የራሳቸውን አሻራ እንዲያስቀምጡት ጭምር ነው ብለዋል፡፡

በፊላንድ መንግስትና በዓለም ባንክ ትብብር በዘርፉ በተሰራው ስራም በአንደኛ ደረጃ የልዩ ፍላጎት ተማሪዎች ተሳትፎ በ2006 ዓ.ም. ከነበረበት ሰባ ሺ አራት መቶ ሰባ ሰባት በሰባት ዓመታት ውስጥ በ3 እጥፍ በማደግ በ2013 ዓም. ወደ 233ሺ 310 ማሳደግ መቻሉንም አመልክተዋል፡

https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid02iBLMnTZL2rukWhnbMhUyYxerpRXZQ9XCu25sWpMUBeJAD9UvHNSyhHThnFEB7wj5l&id=100064682287722
6.1K views12:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-21 14:05:21
የትምህርት ሚኒስቴር ፣ ዩኒቨርስቲዎች እና ተጠሪ ተቋማት ለአገር መከላከያ ሰራዊት ከሁለት መቶ አስራ አንድ ሚሊየን ብር በላይ የገንዘብና የአይነት ድጋፍ አደረጉ
---------------------------------------------
የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱን በመወከል ድጋፉን ባስረከቡበት ወቅት ይህ ድጋፍ በጀግናው የአገር መከላከያ ሰራዊታችን እየተከፈለ ካለው ዋጋ እና ልናደርግ ከሚገባን ድጋፍ አንጻር ትንሽ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ትምህርት ሚኒስቴር፤ተጠሪ ተቋማትና ዩኒቨርሲቲዎች በአሁን ወቅት በአሸባሪ ኃይሎች አገራችን ላይ የተከፈተውን ጥቃት በመመከት ላይ የሚገኘው ጀግናውን የአገር መከላከያ ሠራዊታችንን በተጠናከረ መልኩ በቀጣይነት እንደሚደግፍም ገልጸዋል፡፡

ዶ/ር ሳሙኤል አክለውም የትምህርት ዘርፉ ከረጅም ጊዜ አንጻር ለሰላም ዋጋ የሚሰጥ ትውልድ የማፍራት ኃላፊነቱ አጠናክሮ ከመወጣት ጎን ለጎን የሀገር መከላከያን ለማዘመን መንግሥት እያካሄደ ባለው የለውጥ ሂደት ላይ በተለይ ዩኒቨርሲቲዎች የሚጠበቅባቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራ ገልጸዋል፡፡

የአገር መከላከያ ሚኒስቴርን በመወከል ድጋፉን የተረከቡት የመከለከያ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ማርታ ሉዊጂ የትምህርት ሚኒስቴር ያደረገው የገንዘብና የአይነት ድጋፍ ለሌሎች ተቋማትም አርኣያ ሊሆን የሚችል መሆኑን ጠቅሰው እንዲህ አይነቱ ድጋፍ በቀጣይም ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡

ለሠራዊቱ የተደረገው ድጋፍ የ210,960,000 (ሁለት መቶ አሥር ሚሊዮን ዘጠኝ መቶ ስልሳ ሺ) ብር በጥሬ ገንዘብና ቀሪው በአይነት ለሠራዊቱ ስንቅ የሚሆኑ ደረቅ ምግቦችና ለሴት የመከላከያ ሠራዊት የሚውሉ የጽዳት መጠበቂያ ቁሳቁሶች ናቸው፡፡
8.6K views11:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-19 09:53:37
ውድ ተማሪዎች እና መምህራን!

የ2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ዛሬ የተጀመረ ሲሆን ተማሪዎች እና መምህራን እንዲሁም የትምህርት ማህበረሰብ እንኳን ለ 2015ዓ.ም የትምህርት ዘመን በሰላም አደረሳችሁ እንላለን።

ሁላችንም እድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህፃናትን ወደ ትምህርት ቤት በመላክ የበኩላችንን እንወጣ!!!

መልካም የትምህርት ዘመን

ትምህርት ሚኒስቴር!
12.1K views06:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-16 13:09:49
ያጋጠመንን የትምህርት ጥራት ችግር ለማሻሻልና ደረጃውን የጠበቀ ትምህርት ለመስጠት አዲሱ ስርዓተ ትምህርት ቁልፍ ሚና እንደሚኖረው ተገለጸ፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
የትምህርት ሚኒስቴር በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት ትግበራ ፣ በ2015 ዓ.ም ትምህርት አጀማመር እና በተዛማጅ ጉዳዮች ላይ ለጋዜጠኞች ማብራሪያ ሰጥቷል፡፡

በያዝነው 2015 ዓ.ም ተግባራዊ የሚደረገው አዲሱ ስርአተ ትምህርት ተገቢውን ዕውቀትና ክህሎት ከስነ ምግባር ትምህርት ጋር አጣምሮ ለመስጠት የሚያስችል በመሆኑ በትምህርት ዘርፉ የሚታዩ ክፍተቶችን ለመሙላት ቁልፍ ሚና እንደሚኖረው በትምህርት ሚኒስቴር የተፈጥሮ ሳይንስ ትምህርት ሠርዓተ ትምህርት ዴስክ ሃላፊ ወ/ሮ ዛፉ አብርሃ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አብራርተዋል፡፡
ወ/ሮ ዛፉ ከዚህ በፊት የነበረው ስርዓተ ትምህርት የነበሩበት ክፍተቶች በጥናት የተለየ መሆኑንም አክለው ገልፀዋል፡፡

በመሆኑም አዲሱ ስርዓተ ትምህርት ሀገር በቀል እውቀትን ፣ ቴክኖሎጂ አጠቃቀምን ፣ እንዲሁም ተግባር ተኮር ትምህርትን ከስነ ምግባር ትምህርት ጋር አቀናጅቶ ለመስጠት እንዲያስችል ተደርጎ የተቀረጸ በመሆኑ በእውቀትና ከህሎት የታነጸ ትውልድ ከመገንባት አንጻር ፋይዳው የጎላ መሆኑን አብራርተዋል ፡፡
ሙሉ ዜናውን በሚከተለው ሊንክ ያገኙታል

https://www.facebook.com/100064682287722/posts/pfbid0rh53zprg4s4T1qoppp3is7PYqB5tgsJvEcRviizXEn2XCNCdkHqJoxAATJwRL2Ahl/
15.5K views10:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-14 11:19:10
የ12ኛ ክፍል ፈተናን በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ መስጠቱ በርካታ ጠቀሜታዎች እንዳሉት ተገለፀ፡፡
---------------------------------------
በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በዩኒቨርሲቲዎች መሰጠቱ በርካታ ጠቀሜታዎች እንደሚኖሩት  የፈተናዎች አገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር እሸቱ ከበደ ገልፀዋል፡፡

የፈተና ስርቆትና ኩረጃ  ላይ ከፍተኛ ቁጥጥር በማድረግ ተማሪዎች የራሳቸውን ብቻ እንዲሰሩ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ ፈተናውን በማጓጓዝ ወቅት የሚያጋጥሙ ችግሮችንም ለመፍታት ትልቅ እገዛ እንዲሚኖረውም አብራርተዋል፡፡

ተማሪዎችን በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ መፈተኑ የፈተናውን ሂደት ለማበላሸት ጥረት ከሚያደርጉ ሰዎችም ለመጠበቅ ከፍተኛ ጠቀሜታ እንደሚኖረው ገልፀዋል፡፡

ከዚህም በተጨማሪ ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ መፈተናቸው ቀድመው ዩኒቨርሲቲዎቹን በአካል እንዲያውቋቸው ያደርጋልም ብለዋል።

ለፈተናው ተማሪዎች ተገቢውን ዝግጅት እንዲያደርጉና ወላጆችም አስፈላጊውን ድጋፍ ለልጆቻቸው እንዲያደርጉ ዋና ዳይሬክተሩ ጠይቀዋል።

የ2014ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በሁለት ዙር በዩኒቨርሲቲዎች ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ እንዳለ ይታወቃል፡፡
22.2K views08:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-10 22:05:56
መልካም አዲስ አመት!

Happy New Year!

አዲሱ አመት የሰላም፣ የጤና፣ የብልጽግና እንዲሆንላችሁ እንመኛለን!
3.0K views19:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ