Get Mystery Box with random crypto!

Ministry of Education Ethiopia

የሰርጥ አድራሻ: @ethio_moe
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 82.27K
የሰርጥ መግለጫ

This is Ministry of Education's Official Telegram Channel.
For more updates please visit www.facebook.com/fdremoe

Ratings & Reviews

5.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

3

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 28

2022-10-22 11:07:50
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በቀዳማዊት እመቤት ጽ/ቤት በጅማ ዞን የተገነባውን ኢፋ አኮ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መርቀው ከፈቱ
---------------------------------

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው በቀዳማዊት እመቤት ጽ/ቤት በኦሮሚያ ክልል ጅማ ዞን ነዲ ግቤ ወረዳ የተገነባውን ኢፋ አኮ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መርቀው ከፍተዋል።

ትምህርት ቤቱ የተገነባው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከመደመር መጽሐፍ ሽያጭ ያገኙትን ገቢ ለትምህርት ቤት ማሠሪያ እንዲሆን ለቀዳማዊት እመቤት ጽ/ቤት ባደረጉት ድጋፍ አማካኝነት ነው።

ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው የተማረ ዜጋን በብዛት ለማፍራት አቅደው በየአከባቢው ትምህርት ቤት እያስገነቡ ይገኛሉ።

ዛሬ የተመረቀው ትምህርት ቤትም በቀዳማዊት እመቤት ጽ/ቤት ተገንብተው ከተመረቁት መካከል 25ኛው ትምህርት ቤት ሆኗል።

ትምህርት ቤቱ 18 መማሪያ ክፍሎችን ጨምሮ የላይበራሪ እና የላቦራቶሪ ማዕከላትን የያዘ ሲሆን ግንባታውን ለማጠናቀቅ ስምንት ወራትን እንደወሰደም ተገልጿል።

በቀዳማዊት እመቤት ጽ/ቤት አማካኝነት እስካሁን 25 ትምህርት ቤቶች በመላ ሀገሪቱ ተገንብተው የተመረቁ ሲሆን አንድ ግንባታው የተጠናቀቀ እና ሌላ በግንባታ ላይ ያለው ትምህርት ቤት ጋር ጽ/ቤቱ በአጠቃላይ 27 ትምህርት ቤቶችን መገንባት ችሏል።

ምንጭ -ኢቢሲ
11.8K viewsedited  08:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-21 17:18:45
9.9K views14:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-21 12:25:54
የ2014 ዓም. 12ኛ ክፍል መልቀቂያ አገር አቀፍ ፈተና ተጠናቀቀ

--------------------------------------------------------------------------

ጥቅምት 11/2015ዓም (ትምህርት ሚኒስቴር) በሁለት ዙር ሲሰጥ የነበረው የ2014 ዓም 12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ተጠናቋል።

ለመጀመሪያ ጊዜ በዩኒቨርስቲዎች ውስጥ በሁለት ዙር ሲሰጥ በነበረው የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከ 900ሺህ በላይ ተማሪዎች በ130 የፈተና ጣቢያዎች ተፈትነዋል።

ፈተናው በመጀመሪያዉ ዙር የማህበራዊ ሳይንስ ፈተና ሂደት ካጋጠሙና በመጀመሪያዉ ዙር ማጠቃለያ ከተገለጹ ችግሮች ዉጪ በታቀደው መሰረት በስኬት የተጠናቀቀ ሲሆን የሁለተኛ ዙር ተፈታኞችም ከዛሬ ጀምሮ ወደ የአካባቢያቸው መመለስ ጀምረዋል።

ዩኒቨርስቲዎች ለፈተናው ውጤታማነት ያደረጉት ዝግጅት እና በፈተና አሰጣጥ ሂደት ላይ የነበራቸው አስተዎፆ ከፍተኛ የነበረ ሲሆን ተፈታኞችም የፈተና ስርዓቱን ባከበረ መልኩ ፈተናቸውን ሲወስዱ ቆይተዋል።

ለዚህም የትምህርት ሚኒስቴር ለወላጆች፣ ተፈታኝ ተማሪዎች እና ፈታኝ መምህራን ፣ጣቢያ አስተባባሪዎች ፣ሱፐርቨይዘሮች ፣ የጸጥታ አካላት እና በየደረጃው ለፈተናው ስኬታማነት የበኩላቸውን ለተወጡ አካላትም ላቅ ያለ ምስጋናውን ያቀርባል።

የዘንድሮው የፈተና አሰጣጥ ሂደት የፈተና ስርቆት እና ኩረጃን በማስቀረት ሂደት የነበረው አስተዎፆ ውጤታማ መሆኑ የታየበት እንደነበረም ለማወቅ ተችሏል።

በቀጣይም የፈተና አሰጣጥ ስርዓቱን በማሻሻል የተሻለ እና በራሱ የሚተማመን ትውልድን ለመፍጠር በትኩረት የሚሰራ ይሆናል።

የፈተናዉን አጠቃላይ ሂደት በሚመለከት ዝርዝር መረጃዎችን በቀጣይ የምናሳዉቅ ይሆናል፡፡
10.2K viewsedited  09:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-20 16:36:27
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የተሰጥኦ ማበልጸጊያ ትምህርት ቤትን መርቀው ከፈቱ
———————————————
የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በቡራዩ ከተማ የተገነባውን የተሰጥኦ ማበልጸጊያ ትምህርት ቤት መርቀው ከፍተዋል።

የተሰጥኦ ማበልጸጊያ ትምህርት ቤቱ ልዩ ችሎታ ያላቸው ኢትዮጵያውያን ተሰጥኦዋቸውን የሚያወጡበት መሆኑ ተገልጿል፡፡

አሁን ላይ በኢትዮጵያ በተለያየ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እና ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ በርካታ ባለተሰጥኦዎች መኖራቸው ተመላክቷል፡፡

እነዚህ ባለተሰጥኦዎች ያላቸውን ተሰጥኦ አበልጽገው ወደ ምርትና አገልግሎት ለመቀየር ሲያስቡ የትምህርት ቆይታቸውን ማጠናቀቅ ግድ ይላቸዋል፣ አሊያም ምቹ ሁኔታ ሳይፈጠርላቸው ባክነው ይቀራሉ።

ዛሬ የተመረቀው የተሰጥኦ ማበልጸጊያ ትምህርት ቤትም ይህንን ችግር የሚቀርፍ መሆኑ ነው የተገለጸው፡፡

ትምህርት ቤቱ ባለተሰጥኦዎችን በመለየት ከመደበኛ መማር ማስተማር ሳይለዩ ልዩ ተሰጥኦዋቸውን የሚያበለጽጉበት ነው ተብሏል፡፡

ህንጻው ማደሪያ፣ የመመገቢያ አዳራሽ፣ የአስተዳደር ህንጻ ፣ የህክምና ማዕከል፣ መማሪያ ክፍሎች፣ ቤተ ሙከራ ፣ ቤተ መጽሐፍ እና ወርክ ሾፖች ያሉት መሆኑም ተጠቁሟል፡፡

በተጨማሪም ሁሉንም አገልግሎቶች የሚሰጡ ግብዓቶች የተሟሉለት መሆኑ በምረቃ መርሐ ግብሩ ላይ ተገልጿል፡፡
8.6K views13:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-19 18:50:05
የ2014ዓም 12ኛ ክፍል የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች የሁለተኛ ቀን ፈተና በሰላም ተጠናቋል ።

ጥቅምት 09/2015 ዓም.፣ (ትምህርት ሚኒስቴር ) የ2014ዓም 12ኛ ክፍል የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች የሁለተኛ ቀን ፈተና በሰላም የተጠናቀቀ ሲሆን በነገው እለትም የሚቀጥል ይሆናል።
12.9K viewsedited  15:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-11 13:44:02
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በትናንትናዉ እለት በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ አደጋ የደረሰባቸዉን ተማሪዎች ጠየቁ
---------------------------------------------------------------------

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በትናንትናዉ ዕለት አደጋ የደረሰባቸዉን በሃዋሳ ዩኒቨርስቲ የሚፈተኑ የ2014 ዓም 12ኛ ክፍል ተፈታኞች ደህንነት ለመጠየቅ ዛሬ ጠዋት ሀዋሳ ሪፌራል ሆስፒታል ተገኝተዋል፡፡

“አሁን ዋናዉ የእናንተ ማገገም ነዉ፡፡ ለፈተናዉ አትጨነቁ” በማለትም የተጎዱ ተማሪዎች በጤንነታቸዉ ዙሪያ እንዲያተኩሩ መክረዋል፡፡

በትናንትናዉ እለት ህይወቱ ላለፈዉ ተማሪም የተሰማቸዉን ከፍተኛ ሀዘን ገልጸዉ ለተማሪዉ ወላጆች እና ቤተሰቦች መጽናናትን ተመኝተዋል፡፡

በደረሰዉ ጉዳት እንደአገር እናዝናለን፡፡ ነገር ግን ሂደቱ የፈተና ስርዓቱ ከስርቆት ተጠብቆ ተማሪዎች በራሳቸዉ ጥረት ዉጤታማ እንዲሆኑ እና የተሻለች አገር የመገንባት በመሆኑ በዚህ ተስፋ መቁረጥ የለብንም ብለዋል፡፡ ወላጆችም ይህንን ተረድተዉ ከትምህርት ማህበረሰቡ ጋር በጋራ እንዲቆሙ ጠይቀዋል፡፡

የተከሰተዉ የድልድይ መደርመስ አደጋ ወደ ከፋ ደረጃ እንዳይሸጋገር ተማሪዎቹን ለማዳን ለተረባረቡ የጤና ተቋማት ፣ የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ማህበረሰብ እና የአካባቢዉ ነዋሪዎች ምስጋና አቅርበዋል፡፡

በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ትናንት በደረሰዉ አደጋ ምክንያት ተቋርጦ የነበረዉ ፈተና ዛሬ የተጀመረ ሲሆን ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ የፈተና አሰጣጡንም ጎብኚተዋል፡፡
4.5K views10:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-11 10:49:25
ሁለተኛ ቀኑን በያዘው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በመገኘት የፈተና አሰጣጡን እየጎበኙ ነው።

ምንጭ -ኢቢሲ
4.6K viewsedited  07:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-10 17:52:07
የመስከረም 30/2015 ዓም. የ2014 ዓም የ12ኛ ክፍል ማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ፈተና በሰላም ተጠናቀቀ
……..……..……..……..……..

በዛሬዉ እለት የተጀመረዉ 12ኛ ክፍል ማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች የመጀመሪያ ዕለት ፈተና በሰላም ተጠናቋል፡፡

በዕለቱ ሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ከተፈጠረዉ አሳዛኝ ክስተት እና በመቅደላ አምባ ዩኒቨርስቲ ፈተና ሳይፈተኑ ከወጡ ተማሪዎች ሪፖርት ዉጪ አጠቃላይ ሂደቱ በመላ አገሪቱ ፈተና ከሚሰጥባቸዉ 130 የፈተና ጣቢያዎች በ128ቱ ጣቢያዎች ሙሉ በሙሉ የተሳካ ነበር፡፡

ከዩኒቨርስቲዎቹ የተገኘዉ መረጃ እንደሚያመለክተዉ ፈተናዉ ፈተና በተሰጠባቸው ሁሉም ዩኒቨርስቲዎች በሰላም የተጠናቀቀ ሲሆን ተማሪዎች በነገዉ እለት ለሚኖራቸዉ ፈተና ዝግጅት እያደረጉ ይገኛሉ፡፡

የኢፌደሪ ትምህርት ሚኒስቴር በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ለደረሰዉ ጉዳት በድጋሚ ልባዊ ሀዘኑን ይገልጻል፡፡
2.6K views14:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-10 15:18:33
በወለጋ ዩኒቨርስቲ ጊምቢ ካምፓስ የ12ኛ ክፍል ፈተና በሰላም እየተሰጠ ይገኛል።

የወለጋ ዩኒቨርስቲ ጊምቢ ካምፓስ የ12ኛ ክፍል በመጀመሪያ ዙር ከ1,600 በላይ የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኝ ተማሪዎችን ተቀብሎ እያስፈተነ ይገኛል።

ተማሪዎቹ የመጀመሪያውን ክፍል ፈተና በሰላም መፈተናቸውም ተገልጿል።

የ2014ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተናን ከኩረጃና ከስርቆት በፀዳ መልኩ በዩኒቨርሲቲ እንዲሠጥ ከፍተኛ ዝግጅት ሲደረግ ቆይቷል።

ተፈታኝ ተማሪዎችም ተረጋግተው ፈተናቸውን እየወሰዱ እንደሚገኙም ተገልጿል።
3.1K viewsedited  12:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-10 12:47:27
መስከረም 30/2015 ዓም. የ2014 ዓም የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የከሰዓት በፊት ፈተናቸዉን በሰላም አጠናቀቁ

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ ፤ የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ፤ የአጠቃላይ ትምህር ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ፋንታ ማንደፍሮ የ12ኛ ክፍል ፈተና አሰጣጥን በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተገኝተው ተመልክተዋል።
3.5K views09:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ