Get Mystery Box with random crypto!

ኢትዮ መረጃ - NEWS

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethio_mereja_news — ኢትዮ መረጃ - NEWS
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethio_mereja_news — ኢትዮ መረጃ - NEWS
የሰርጥ አድራሻ: @ethio_mereja_news
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ሀገር: ኢትዮጵያ
ተመዝጋቢዎች: 58.41K
የሰርጥ መግለጫ

ኢትዮጵያን መውደድ ባትችል አትጥላት
ማክበር ባትችል አታዋርዳት
ማራመድ ባትችል አታዘግያት
መጠበቅ ባትችል አትበትናት።
ይህን በማድረግ ታሪክ ባትሠራም ታሪክ አታበላሽም።

ለአስታየት @ethio_merjabot
@biruke_promotion

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 12

2023-04-21 19:18:45
በትግራይ ክልል የንግድ ባዛር ሊካሄድ ነው 

የትግራይ ክልልን የንግድ እንቅስቃሴ ማነቃቃት አላማ ያደረገ የንግድ ባዛር መቀሌን ጨምሮ በአራት የክልሉ ከተሞች እንደሚካሄድ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል።

ባዛሩ ሚያዚያ 21 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ በመቀሌ ከተማ በይፋ እንደሚከፈትና በውቅሮ፣ አዲግራትና ማይጨው ከተሞችም እንደሚካሄድ ተመላክቷል። ከባዛሩ በተጨማሪ የፓናል ውይይት እንደሚደረግ ተጠቁሟል።
5.7K views16:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-21 08:27:07
ኢድ ሙባረክ

ውድ የኢትዮ መረጃ አባላት እንኳን ለ1 ሺህ 444ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን።

በዓሉ የሰላም የጤና የፍቅር የአንድነት ያድርግልን።

የዒድ አልፈጥር በዓል በድምቀት እየተከበረ ይገኛል።

የ2015 ዓ.ም የዒድ አልፈጥር በዓል በእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ በድምቀት እየተከበረ ነው።

1 ሺህ 444ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል በመላው ኢትዮጵያ በተለያዩ ሃይማኖታዊ ሥርዓቶች ነው እየተከበረ የሚገኘው።

የፌዴራል ጠቅላይ ሼሪዓ ፍርድ ቤት በዓሉ የሰላም፣ የደስታ፣ የመተዛዘን እና የመረዳዳት እንዲሆን የመልካም ምኞት መልዕክት አስተላልፏል።

በታላቁ የረመዷን ወር መጨረሻ የሚከበረውን የዒድ አልፈጥር በዓልን በሰላምና በመተሳሰብ እንዲሁም የተቸገሩ ወገኖችን በማገዝ ማሳለፍ እንደሚገባም ጥሪ አቅርቧል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
3.0K views05:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-20 20:43:13 አዲስ አበባ

ከለሊቱ 10 ሰዓት ጀምሮ መንገዶች ይዘጋሉ።

1444ኛው የኢድ አልፈጥር ረመዳን በዓል የኢድ ሶላት (በአዲስ አበባ ስታዲዮም እና አካባቢው) ተጀምሮ እሰከሚጠናቀቅ ለተሸከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶች የፀጥታ እና ደህንነት የጋራ ግብረኃይል ይፋ አድርጓል።

አሽከርካሪዎች የትራፊክ መጨናነቅ እንዳይፈጠር ከዚህ በታች የተዘረዘሩት መንገዶች የሚዘጉ መሆኑን በማወቅ አማራጭ መንገዶችን ተጠቀሙ ብሏል።

የሚዘጉ መንገዶች ፦

- ከቦሌ አየር መንገድ በሚሊኒየም አዳራሽ ወደ ስታዲዮም የሚወስደው መንገድ ደንበል ሲቲ ሴንተር ኦሎምፒያ አደባባይ አከባቢ፤

- ከመገናኛ ፣ በሃያ ሁለት ወደ መስቀል አደባባይ እንዲሁም ከቦሌ መድሃኒያለም፣ በአትላስ ሆቴል ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ኡራኤል ቤተ-ክርስቲያን አካባቢ፤

- ከአራት ኪሎ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ባሻ ወልዴ ችሎት ወይም ፓርላማ መብራት፤

- ከፒያሣ አካባቢ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ቸርችል ጎዳና ቴዎድሮስ አደባባይ፤

- ከተክለ ሀይማኖት በሜትሮሎጂ ወደ ስታዲዮም የሚወስደው መንገድ ሜትሮሎጂ መስሪያ ቤት አካባቢ፤

- ከተክለ ሀይማኖት ፣ በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል የሚወስደው መንገድ ጥቁር አንበሳ የኋላ በር አካባቢ፤

- ከሲኒማ ራስ በጎላ ሚካኤል ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ጎላ ሚካኤል መስቀኛ፤

- ከጌጃ ሰፈር ፣ ጤና ጥበቃ፣ ብሄራዊ ቲያትር የሚወስደው መንገድ ጎማ ቁጠባ፤

- ከባሻ ወልዴ ችሎት በኦርማ ጋራዥ ወደ ፍል ውሃ መስኪድ የሚወስደው መንገድ ንግድ ማተሚያ ቤት ፤

- ከጎፋ በቅዱስ ቂርቆስ ቤ/ክ ወደ ለገሐር አዲሱ መንገድ የሚወስደው መንገድ ቅዱስ ቂርቆስ ቤ/ክ መስቀለኛው ላይ፤

- ከጦር ኃይሎች ፣ ልደታ ፣ ፖሊስ  ሆስፒታል ሜክሲኮ አደባባይ ፤

- ከሳሪስ በጎተራ ወደ መስቀል አደባባይ ለቀላል መኪና የቀድሞ አራተኛ ክፍለ ጦር አካባቢ እንዲሁም ለከባድ መኪና አጎና ሲኒማ አካባቢ #ይለፍ_ለሌላቸው ተሽከርካሪዎች ከለሊቱ 10 ሰዓት ጀምሮ ዝግጅቱ እስከሚጠናቀቅ ድረስ ዝግ ይሆናሉ።

ህብረተሰቡ የትራፊክ ፖሊስ አባላት በሚጠቁሙት አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀም እና ለትራፊክ ፖሊስ አባላት ትዕዛዝ አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርግ ግብረኃይሉ ጥሪ አቅርቧል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
8.9K viewsedited  17:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-20 20:09:31
እውነተኛ ጥቆማ!

የእውነት ምንም ውሸት አልተቀላቀለበትም
በትኩሱ ስለወቅታዊ ጉዳይ ፈጣን እና ታማኝ መረጃ ለማግኘት ይሄንን  ቻናል ዝምብላቹህ ተቀላቀሉ!!

እስኪ አንዴ ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን join

https://t.me/+NQ96aCgCktQ0MDg0
https://t.me/+NQ96aCgCktQ0MDg0
8.2K views17:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-20 19:05:00
የዒድ አልፈጥር በዓል ነገ መሆኑ ታውቋል።

የሸዋል ወር ጨረቃ  በሳኡዲ አረበያ ዛሬ ሀሙስ በመታየቷ የዒድ አልፈጥር በዓል ነገ ጁምዓ / አርብ ይውላል።

እንኳን 1 ሺህ 444ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
9.1K viewsedited  16:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-20 15:31:07
አራት የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን በፌስቡክ ማንነቱን ቀይሮ በመተዋወቅ‘‘ካናዳ እና እንግሊዝ እወስዳችኋለው’’በማለት ጾታዊ ግንኙነት እንዲፈጽሙ አድርጓል የተባለው ግለሰብ በጽኑ እስራትና በገንዘብ ተቀጣ።

ግለሰቡ ከግማሽ ሚሊየን ብር በላይ ገንዘብ እና 20 ግራም ወርቅ ተቀብሎ የማታለል ወንጀል ፈጽሟል ተብሎ ነው በጽኑ እስራትና በገንዘብ እንዲቀጣ የተወሰነው።

የቅጣት ውሳኔውን የወሰነው የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቦሌ ምድብ 2ኛ አርቲዲ ወንጀል ችሎት ሲሆን÷ተከሳሹ ታዲዮስ ዘላለም በአዲስ አበባ ከተማ አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 06 ነዋሪ ነው።

ተማሪዎችን በማህበራዊ ትስስር ገጽ “ናቲ መላኩ”ብሎ ማንነቱን ቀይሮ በካናዳ ነዋሪ በመምሰል ከተዋወቃቸው በኋላ ‘’ካናዳና እንግሊዝ እወስዳችኋለው’’ብሎ የማታለል ተግባር መፈጸሙ በክሱ ተመላክቷል።

ከዚህም በኋላ ተከሳሹ ከካናዳ ወደ አዲስ አበባ እንደመጣ በማስመሰል በግንቦትና በሰኔ ወር 2014 ዓ.ም በተለያዩ ቀናቶች ለ4 የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የግል ተበዳዮች ስልክ ይደውላል፡፡

በዚህም'' ከእንግሊዝ ኤምባሲ ጉዳይ የሚፈጽምላችሁ ሰው ይመጣል፤ አሻራ የሚወሰደው ከዘር ፈሳሽ እና ከወርቅ ስለሆነ አልጋ ይዛችሁ ጠብቁ በማለት'' የግል ተበዳዮች በተለያየ ቀናቶች በቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 13 አልጋ ይዘው እንዲጠብቁ ማድረጉ በክሱ ተጠቅሷል።

አልጋ እንዲይዙ ካደረገ በኋላ ማንነቱን ቀይሮ ወደ አልጋ ቤት በመሄድ የግብረስጋ ግንኙነት እንዲፈጽሙ ማድረጉም በክሱ ተመላክቷል።

በቅጣት አወሳሰን መመሪያ ቁጥር 2/2006 መሰረት በደረጃ ስድስት በዕርከን 25 መነሻ በ7 ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ የተወሰነ ሲሆን÷በዕርከን 3 መሰረት ደግሞ በ3 ሺህ ብር የገንዘብ እንዲቀጣ ተወስኗል።

FBC 9(በታሪክ አዱኛ)
@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
2.3K viewsedited  12:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-20 15:01:27
መንግስት በሱዳን የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን ሁኔታ በቅርበት እየተከታተለ መሆኑን አስታወቀ

የኢፌዴሪ መንግሥት በሱዳን ባለው ወቅታዊ የፀጥታ ሁኔታ ምክንያት በሀገሪቱ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን ሁኔታ በቅርበት እየተከታተለ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በዋናው መስሪያ ቤት እና ካርቱም በሚገኘው የኢትዮጵያው ኤምባሲ አማካኝነት የኢትዮጵያውያንን ደኅንነት ለመጠበቅ እየሠራ መሆኑ ተገልጿል፡፡

የሚመለከታቸው ሴክተር መስሪያ ቤቶች እና አጎራባች ክልሎች አባል የሆኑበት ግብረ ኃይል በሀገር አቀፍ ደረጃ መቋቋሙ ተጠቁሟል፡፡

አስፈላጊ መረጃዎችን በቀጣይ እንደሚያሳውቅም ነው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የገለጸው፡፡

#Ethiopia
@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
2.9K views12:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-20 08:15:03 መከላከያ ሠራዊት ትናንት ዲሽቃ፣ ሞርታርና ሌሎች የቡድን ጦር መሳሪያዎችን ከሕወሃት መረከብ መጀመሩን ፋና ብሮድካስት ዘግቧል።

የቡድን ጦር መሳሪያዎቹ ልዩ ስሙ ደንጎላት በተባለ ቦታ ላይ የተሰበሰቡ እንደኾኑ ዘገባው ጠቅሷል። የቡድን መሳሪያዎች ርክክብ እስከ ሚያዝያ 16 ይቀጥላል መባሉን ዘገባው ጠቅሷል።

ሠራዊቱ በመጀመሪያው ዙር ከባድ የጦር መሳሪያዎችንና በሁለተኛው ዙር የአየር ኃይል መሳሪያዎችን ከሕወሃት ኃይሎች መረከቡ ይታወሳል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
6.4K views05:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-19 14:28:03 አንዱዓለም አራጌ ከኢዜማ መልቀቃቸውን አስታወቁ!

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) መስራቾች ውስጥ አንዱ የሆኑት ጉምቱው ፖለቲከኛ አንዱዓለም አራጌ ከፓርቲው መልቀቃቸውን አስታውቀዋል።አንዱዓለም በተረጋገጠው የማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባሰፈሩት የደብዳቤ ጽሁፍ፤ ኢዜማን ከመጠንሰስ እስከ መመሥረት፣ ከምሥረታ በኋላም ወረዳቸውን በአባልነት እንዲሁም ፓርቲውን በአመራርነት እስከማገልገል የዘለቀ አቅም የፈቀደውን እንቅስቃሴ ማድረጋቸውን አስታውሰዋል።

አክለውም “የፖለቲካው - አውሎ - ነፋስ ገና ከሩቅ ግሳንግሱን እየጠራረገ ሲመዘገዘግ፣ የለም የፓርቲያችንን ቁመናና አሰሳለፍ ከወዲሁ እናስተካክል የሚል ተማጽኖ ከማቅረብም ባለፈ፤ በአባላት ፊት ቀርቤ ብሟገትም የሚገባውን ድጋፍ ባለማግኘቴ ውሳኔያቸውን በጸጋ ተቀብዬ በአባልነት መቀጠሌ ይታወቃል።“ ሲሉም ገልጸዋል።

“በዕለት ከዕለት ውሎዬ የማገኛቸው ዜጎች አሁንም የፓርቲው አመራር እንደሆንኩ እንደሚቆጥሩ ለመረዳት ችያለሁ።“ ያሉት አንዱዓለም፤ “በመሆኑም በሌለሁበት እርምጃ የውግዘትም ሆነ የውዳሴው ተቋዳሽ ለመሆን አልሻም። ስለሆነም ከዚህ በላይ ሳልዘገይ ነገሮች እንደየዘርፋቸው ማሰቀመጥ ተገቢ ሆኖ አግኝቸዋለሁ።“ ብለዋል።

አንዱዓለም በጽሁፋቸው አክለውም፤ “በሌላ በኩል እንደጠበኩት ኢዜማን አይነ -ግቡና ዘመን ተሻጋሪ ለማድረግ የሰነቅነው ህልም እውን ይሆናል ወይ? በሚለው ጉዳይ ላይ ደጋግሜ የሠራሁት የሁኔታ ትንታኔ አዎንታዊ ምላሽ ሊያስገኝልኝ ባልቻለት ሁኔታ፤ ኢዜማ ውስጥ መቀጠሉ ትርጉም የሚሰጥ ሆኖ አገኘሁትም። በመሆኑም ይህን በመስለ ሁኔታ ተጨማሪ ቀናትን በኢዜማ ጣራ ሥር መቀጠል የሚያስችለኝ አንዳች አይነት ምክንያት አልቀረኝም።“ ሲሉ ከፓርቲው በገዛ ፍቃዳቸው መልቀቃቸውን አስታውቀዋል።

[Addis Maleda]
@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
5.6K views11:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-18 20:25:49
#Update

በሱዳን እየተካሄደ ባለው ውጊያ ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ በርካታ ሰላማዊ ሰዎች እየተገደሉ ናቸው።

በሱዳን የኢትዮጵያ ኤምባሲ ፤ በሱዳን እየተካሄደ ባለው ውጊያ በርካታ ሲቪሎች ለጉዳት መዳረጋቸውና ህይወትም እየተቀጠፈ መሆኑን ገልጿል።

ከእነዚህ መካከል #ኢትዮጵያውያን እንደሚገኙበት መረጃዎች እንደደረሱት አመልክቷል።

ኤምባሲው ምን ያህል ኢትዮጵያውያን እንደሞቱ እና እንደተጎዱ በዝርዝር አልገለፀም።

ነገር ግን በኢትዮጵያውያን ሞት እና ጉዳት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እደተሰማው እና ለሟች ቤተሰቦች እና ወዳጅ ዘመዶቻቸው መፅናናትን ተመኝቷል።

" ይህን አስቸጋሪ ጊዜ ለማለፍ ኢትዮጵያዊን የተቻላቸውን ሁሉ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ በድጋሜ እናሳስባለን " ብሏል።

መረጃ ለመለዋወጥ እና ለምክክር የኤምባሲው ባልደረባ የሆኑትን አቶ ነጅብ አብደላ በስልክ ቁጥር +249911646547 ማነጋገር እንደሚቻል በሱዳን ካርቱም የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ አሳውቋል።

በሌላ በኩል ፥ ከትላንት ምሽት አንስቶ በሱዳን የማህበራዊ መገናኛዎች ላይ አንድ ቪድዮ ሲሰራጭ ነበር (ከላይ ተያይዟል) ።

ቪድዮው በመድፍ የተመታ ቤትን የሚያሳይ ሲሆን በቤቱ ውስጥ የሚኖሩት ኢትዮጵያውያን እንደነበሩና ሁሉም ወዲያው ህይወታቸው እንዳለፈ ተነግራል። ቁጥራቸው ምን ያህል እንደሆነ የተገለፀ ነገር የለም።

ስለተሰራጨው ቪድዮ እና ስለደረሰው ጉዳት ትክክለኝነት በሱዳን የኢትዮጵያ ኤምባሲ ያለው ነገር የለም።

በሰዳን እየተካሄደ ያለው ውጊያ በከተማ ውስጥ እየተደረገ መሆኑ በዛው የሚኖሩ የሀገራችንን ዜጎች ጨምሮ የመላው ሱዳናውያንን ደህንነት አደጋ ላይ ጥሏል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
2.5K viewsedited  17:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ