Get Mystery Box with random crypto!

ESAT (ኢሳት🇪🇹)®

የሰርጥ አድራሻ: @esat_tv1
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 246.66K
የሰርጥ መግለጫ

ለማንኛውም አስተያየት እና ጥቆማ 👉 @Esat_tv_comment_bot
🇪🇹ኢሳት የኢትዮጵያ አይን እና ጆሮ🇪🇹

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 146

2022-05-28 08:24:06
ባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ (ባልደራስ) ከፍተኛ አመራሩ አቶ ስንታየሁ ቸኮል በባህር ዳር ከተማ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን አሳውቋል

ፓርቲው አመራሩ በአንደኛ ፖሊስ ጣቢያ መታሰሩን ነው ያመለከተው።

አቶ ስንታየሁ ቸኮል ከጥቂት ወራት በፊት ከረጅም ጊዜ እስር መለቀቃቸው የሚዘነጋ አይደለም።

@Esat_tv1
@Esat_tv1
50.8K views05:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-28 08:24:03
የስራ ማግኛ ኦንላይን ፕላትፎርም /ሊንኮችህ/ ዝርዝር ለማግኘት

Join our telegram

https://t.me/+x8RIy5m4HlxiNGRk
49.6K views05:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-28 08:23:54
አዳማ

በአዳማ ከተማ በሁሉም የስራ ዘርፎች የሚወጡ የስራ ማስታወቅያዎችን፤ "Adama jobs" መተግበርያን ከ google play store በማውረድ ወይም የቴሌግራም ቻናላችንን በመቀላቀል ይከታተሉ።

Application https://play.google.com/store/apps/details?id=com.yach.seraadama

telegram channel https://t.me/adamaJob
48.0K views05:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-27 16:02:24
የአፍሪካ ሕብረት ልዩ የመሪዎች ጉባኤ በኢኳቶሪያል ጊኒ መካሄድ ጀመረ

በትናትናው ዕለት ኢኳቶሪያል ጊኒ የገቡት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በዛሬው እለት በጀመረው የአፍሪካ ሕብረት ልዩ የመሪዎች ጉባኤ ላይ ተሳታፊ ናቸው።

የህብረቱ ጉባኤ በአህጉሪቱ የተጋረጠውን ወቅታዊ የሰብአዊ ተግዳሮቶችን ለመፍታት የአፍሪካ መሪዎች ባደረጉት ጥረት ላይ ይመክራል ተብሎ ይጠበቃል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1
37.2K views13:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-27 13:54:23
ፑቲን ሩሲያ ዓለምን ከአስከፊው የምግብ ቀውስ ለመታደግ ዝግጁ መሆኗን ተናገሩ

የሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሜር ፑቲን ሩሲያ ዓለምን ከአስከፊው የምግብ ቀውስ ለመታደግ ዝግጁ መሆኗን ተናግረዋል።

ነገር ግን ሩሲያ ይህንን ልታደርግ የምትችለው ምዕራባውያን በሩሲያ ላይ የጣሏቸውን ማዕቀቦችን ሲያነሱ ብቻ ነው ብለዋል። ፑቲን ይህን ያሉት ከጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጋር ውይይት ባደረጉበት ወቅት ነው።

@Esat_tv1
@Esat_tv1
44.6K views10:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-27 13:52:22
የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በጋዜጠኛ ያየሰው ሽመልስ ላይ የ10 ቀናት የምርመራ ጊዜ ፈቀደ

ያየሰው የተጠረጠረው “ኹከት እና ብጥብጥ በማነሳሳት ወንጀል” መሆኑን መርማሪ ፖሊስ ለፍርድ ቤቱ ገልጿል። “ኢትዮ ፎረም” የተሰኘው የዩቲዮብ መገናኛ ብዙኃን አዘጋጅ የነበረው ያየሰው በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በቁጥጥር ሥር የዋለው ትላንት ሐሙስ ግንቦት 18 ቀን 2014 ነበር። የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ያየሰውን ዛሬ አርብ ግንቦት 19 ፍርድ ቤት ያቀረበው ሲሆን የ14 ቀናት የምርመራ ጊዜ ጠይቆበታል። ጋዜጠኛ ያየሰውን ወክለው በችሎቱ የተገኙት ጠበቃው ታደለ ገብረመድህን፤ የተጠየቀው የምርመራ ጊዜ ውድቅ ተደርጎ ደንበኛቸው በዋስትና እንዲለቀቅ ጠይቀዋል።

የግራ ቀኙን አስተያየት ያደመጠው የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት፤ መርማሪ ፖሊስ የጠየቀውን የምርመራ ጊዜ በአራት ቀናት አሳንሶ 10 የምርመራ ቀናትን መፍቀዱን ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ዘግቧል። በጽህፈት ቤት በኩል የተካሄደውን የዛሬውን የችሎት ውሎ ጋዜጠኛ ያየሰው በአካል ተገኝቶ መከታተሉም ታውቋል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1
41.2K views10:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-27 13:52:21
የስራ ማግኛ ኦንላይን ፕላትፎርም /ሊንኮችህ/ ዝርዝር ለማግኘት

Join our telegram

https://t.me/+x8RIy5m4HlxiNGRk
37.4K views10:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-27 13:52:11
በርሶ ፎቶ በፍቅረኛዎ ፎቶ ወይም በሚያደንቁት ሰው ምስል አሳምረን እንሰራለን! ከ ናተ ሚጠበቀው ፎቶውን መላክ ብቻ ነው

ስልክ 0949378569
0918698501

ማሰራት የምትፈልጉ ፎቶአቹን በዚህ Username ላኩልን
@Yaska_yasa
@Smith_Rio

የተሰሩ ሰዓቶችን ለመመልከት

https://t.me/joinchat/AAAAAFGMUgiL2c0_OopkxQ
40.0K views10:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-26 21:07:33 አቶ ጃዋር መሀመድ (የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ ምክትል ሊቀመንበር) ከእስር ከተፈቱ በኃላ ለመጀመሪያ ጊዜ " ለኡቡንቱ ቲቪ " የማህበራዊ መገናኛ ከሰጡት ቃለ ምልልስ የተወሰደ

በዚሁ ቃለ ምምልስ ወቅት አቶ ጃዋር ከተጠየቁት ጥያቄዎች አንዱ እሳቸውን በተመለከተ ሲናፈሱ የነበሩ አሉባልታዎችን እንዲያጠሩ ነው " አቶ ጃዋር ከገዢው ፓርቲ ጋር መስራት ጀምሯል፣ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር ተገናኝቷል የተፈታውም ለዚህ ነው ፤ አሁንም እየሰራ ያለው የመንግስትን ስራ ነው " ስለሚባሉት ጉዳዮች ግልፅ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

አቶ ጃዋር መሀመድ ፦

" እኔም ሰማቸዋለሁ አሉባልታዎቹን ። እኔ ከማንም ጋር የግል ቁርሾ የለኝም። የታሰርኩትም ቢሆን በፖለቲካ ልዩነት እንጂ በግል ፀብ አይደለም።

ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር አልተገናኘንም፤ ሊያገኘኝ ከፈለገ ግን ሁሌም ዝግጁ ነኝ። ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር ብቻ ሳይሆን / ከዐቢይ ጋር ብቻ ሳይሆን ከመሮም ጋር፣ ከደብረፅዮንም ጋር ከሁሉም በአሁን ወቅት በሀገራችን ባለው ግጭት ውስጥ እየተሳተፉ ካሉ ኃይሎች ጋር ተገናኝቶ ሀገራችንን ከጦርነት አስወጥቶ ወደ ሰላም እና ልማት ለመመለስ እድሉ ከተገኘ ከማናቸውም ጋር ለመስራት፣ ከማናቸውም ጋር ለመተባበር ፣ ከማናቸውም ጋር ለመነጋገር በማንኛውም ቦታ እና ሁኔታ ለመነጋገር ዝግጁ ነኝ።

እኔ ማልፈቅደው ግን ከማናቸውም ጋር አብሬ ጦርነት ማፋፋም አልፈልግም፤ ከማናቸውም ጋር።

ሁሉም በጦርነት ውስጥ እየተሳተፉ ያሉ ይሁኑ በጦርነት ውስጥ እያልተሳተፉ ያሉ ምሁራን እና ሊህቃን ወደ ሰላም ጠረጴዛ መምጣት አለባቸው ብዬ አምናለሁ፤ ከአንዳቸውም ጋር ግላዊ ጠብ የለኝም።

ስለዚህ ገዥው ፓርቲ ሀገር እየገዛ ነው ያለው ፤ ሀገር እያስተዳደረ ነው ያለው ፣ ሀገሪቷ ለገባችበት ችግር ትልቁን ድርሻ የሚወስደው ገዢው ፓርቲ ነው፤ እንደመሪም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ነው ፤ ወደመፍትሄ የምንገባ ከሆነ የእነሱ ተሳትፎ፣ የእነሱ ፍቃደኝነት ወሳኝ ነው።

ስለዚህ እንደ ፖለቲካ ፓርቲ አመራርም እንደ እዚህች ሀገር ዜጋም በሰላም ጉዳይ ላይ የሀገራችንን እጣፈንታ ወደፊት ማስተካከል ላይ ከገዢው ፓርቲም ጋር ሆነ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር ሆነ፣ የተለያዩ ድርጅቶች ከሚመሩ ቅድም እንዳልኩት ከደብረፅዮን ሆነ ፣ ከፃድቃን ሆነው፣ ከመሮም ሆነ፣ ከገመቹ ሆነ፣ ከተፈራ ማሞ ሆነ ፣ ከይልቃል ከፋለ ጋርም ሆነ ከማንኛውም ጋር ለመስራት ዝግጁ ነኝ፤ የሀገራችን አመራርም ለዚህ መዘጋጀት መቻል አለበት።

ሀገራችን ያለችበት ሁኔታ ለምን ከእከሌ ጋር ተነጋገርክ፣ እከሌ ሳይጣን ነው እከሌ መልአክ ነው በማለት እንደማያዋጣ ላለፉት 4 ፣ ላለፉት 2 ዓመታት ግልፅ ሆኗል።

ስለዚህ አሁንም ደግሜ የምለው ከማንኛውም የፖለቲካ ኃይል ጋር ፣ ከማንኛውም የፖለቲካ አመራር ጋር ህዝባችንን አሁን ከገባበት መቀመቅ እና ሰቆቃ ለማውጣት መስራት ያስፈልጋል።

እዚህ ላይ ግልፅ ማድረግ የምፈልገው ከማኛውም ኃይል ጋር እንሰራለን እንደ ድርጅትም እንደ ግለሰብም እንደ አመራርም፤ ሀገራችንን እና ህዝባችንን ወደ ሰላም መንገድ ወደ ልማት እንዲመለሱ ባለኝ እውቀት እና ባለኝ ተሰሚነት መጥቀም እፈልጋለሁ።

ነገር ግን ለማንም ድርጅት ሆነ ግለሰብ መጠቀሚያ መሆን አልፈልግም ፤ ለማንም የጦር ማገዶ መሆን አልፈልግም ፣ የማንንም አንባገነናዊ አካሄድን፤ የማንም ጦረኛ አካሄድን መደገፍ አልፈልግም።

ወደ ሰላም መምጣት ከሚፈልግ አካል ጋር ለመስራት ዝግጁ ነኝ፣ ይሄ ደግሞ ኩነኔ አይደለም ይሄ ትክክለኛ ነው ብዬ የማምነው ፤ ስለዚህ ጦርነቱ መቆም አለበት ጦርነት ቆሞ ወደ ድርድር መምጣት አለብን ቴክኒካል ነገሮች መነሳት አለባቸው ስለዚህ ለመነጋገር ጋሬጣ ሆነው ያሉ ነገሮች ተሰባብረው ድልድይ ተመስርቶ ሁላችንም ወደመነጋገር መግባት አስፈላጊ ነው። "

@Esat_tv1
@Esat_tv1
28.1K viewsedited  18:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-26 13:38:04
ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በፀጥታ ኃይሎች መወሰዱ ታወቋል

የፍትሕ መፅሔት ማኔጂንግ ኤዲተር ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በፀጥታ ኃይሎች መወሰዱን ወንድሙ ታሪኩ ደሳለኝ እና የስራ ባልደረቦቹ ገልፀዋል። ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በቢሮው በነበረበት ወቅት በሁለት ተሽከርካሪ የመጡ መደበኛ (ሲቪል) የለበሱ የፀጥታ ኃይሎች ከቢሮው እንደወሰዱት ታውቋል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1
50.9K views10:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ