Get Mystery Box with random crypto!

ESAT (ኢሳት🇪🇹)®

የሰርጥ አድራሻ: @esat_tv1
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 246.66K
የሰርጥ መግለጫ

ለማንኛውም አስተያየት እና ጥቆማ 👉 @Esat_tv_comment_bot
🇪🇹ኢሳት የኢትዮጵያ አይን እና ጆሮ🇪🇹

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 143

2022-06-04 15:50:18
አቶ ደመቀ መኮንን ወደ ትግራይ ክልል የሚሄደውን የሰብአዊ ድጋፍ ለማቀላጠፍ የሚደረገውን ጥረት ተመለከቱ

በጉብኝቱ የክልሉ ርዕሰ-መስተዳድር አቶ አወል አርባ እንዲሁም ሌሎች የፌዴራል እና የክልል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን መንግሥት ወደ ትግራይ ክልል የሚላኩ ሰብአዊ እርዳታዎች ለማሳለጥ እያደረገ ከሚገኘው ሁሉን አቀፍ ጥረት በተጓዳኝ አሸባሪው ህወሓት ለጥፋት ዓላማው ሊጠቀምባቸው የሚችሉ ቁሳቁሶች እንዳይተላለፉ በትኩረት እንዲሠራ ማሳሰባቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1
43.7K views12:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-04 09:20:01
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን አፋር ሠመራ ገቡ

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ሠመራ ሱልጣን አሊሚራህ ሃንፈሬ አየር ማረፊያ ሲደርሱ የአፋር ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ አወል አርባ እና ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች አቀባበል አድርገውላቸዋል።

በአፋር ክልል በሚኖራቸው ቆይታ ከክልሉ አመራሮች ጋር በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት እንደሚያደርጉ እንደሚጠበቅ ኢዜአ ዘግቧል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1
52.9K views06:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-04 09:19:57
የሊንኮቹን ዝርዝር ለማግኘት

Join our telegram

https://t.me/+x8RIy5m4HlxiNGRk
49.5K views06:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-03 19:41:06 የፊታችን ዕሁድ በመስቀል አደባባይ ለሚካሄደው የፖሊስ አመራርና አባላት የምስጋናና የእውቅና አሰጣጥ መርሃ ግብር የሚዘጉ መንገዶችን የአዲስ አበባ ፖሊስ ይፋ አደረገ

በዚህም መሰረት ፦

ከቦሌ አየር መንገድ በሚሊኒየም አዳራሽ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ደንበል ሲቲ ሴንተር (ኦሎፒያ አደባባይ)

ከመገናኛ ፣በሃያ ሁለት ወደ መስቀል አደባባይ እንዲሁም ከቦሌ መድሃኔዓለም፣ በአትላስ ሆቴል ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ኡራኤል ቤተ-ክርስቲያ አካባቢ በላይና በታች

ከአራት ኪሎ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ገብርኤል መሳለሚያ አካባቢ

ከቸርችል ጎዳና በሃራምቤ ሆቴል ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ፖስታ ቤት

ከተክለ ሀይማኖት በሜትሮሎጂ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ሜትሮሎጂ መስሪያ ቤት አካባቢ

ከተክለ ሀይማኖት ፣ በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ወደ ኢሚግሬሽን የሚወስደው መንገድ ጥቁር አንበሳ የኋላ በር

ከሳሪስ በጎተራ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ለከባድ መኪና አጎና አካባቢ ለቀላል መኪና የቀድሞ አራተኛ ክፍለ ጦር

ከጦር ኃይሎች ፣ ልደታ ፣ ፖሊስ ሆስፒታል ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ ሜክሲኮ አደባባይ

ከሚክሲኮ አቅጣጫ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ ለገሃር መብራት

ከሰንጋ ተራ በቴሌ ባር ለሚመጡ አሽከርካሪዎች በድሉ ህንፃ አካባቢ

ከንግድ ማተሚያ ቤት በውስጥ ለውስጥ ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ኦርማ ጋራዥ አካባቢ

ከሸራተን ወደ አምባሳደር ለሚመጡ ፍል ውሃ አካባቢ

ከካዛንቺስ በኩል ወደ ፍል ውሃ ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ኢንተርኮንቲኔንታል ሆቴል አካባቢ ቅዳሜ ለዕሁድ አጥቢያ ከለሊቱ 10፡30 ሰዓት ጀምሮ ዝግጅቱ እስከሚጠናቀቅ ድረስ ለተሽከርካሪ ዝግ ይሆናል።

ህብረተሰቡ የትራፊክ ፖሊስ አባላት በሚጠቁሙት መሰረት አማራጭ መንገዶችን በመጠቀም አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርድ የአዲስ አበባ ፖሊስ መልዕክት አስተላልፏል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1
31.3K views16:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-03 16:04:41
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የተለያዩ ሹመቶችን ሰጡ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) በዛሬው እለት የተለያዩ ሹመቶች ሰጥተዋል።

በዚሁ መሰረት፣
1. አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን - የጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሔራዊ ደህንነት አማካሪ ሚኒስትር

2. አቶ ካሊድ አብዱራህማን - በጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ የፕሮጀክቶች ክትትል

3. አቶ ወንድሙ ሴታ - የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ

4. አቶ ሄኖስ ወርቁ - የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን ምከትል ዋና ዳይሬክተር ሆነው ተሹመዋል።

በተጨማሪም የሚከተሉት ሸመቶች እንዲጸድቁ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትን ጠይቀዋል

1. ወ/ሮ መሰረት ዳምጤ - የፌደራል ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት ዋና ኦዲተር

2. አቶ አበራ ታደሰ - የፌደራል ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት ምክትል ዋና ኦዲተር

@Esat_tv1
@Esat_tv1
42.7K views13:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-03 14:34:09
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ለስትራቴጅክ አመራሮቹ የማዕረግ ዕድገት ሰጠ

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ፣ ከአዲስ አበባ ፖሊስና ከድሬደዋ፣ እንዲሁም ከአፋርና ከቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል ፖሊስ ለተውጣጡ ለስትራቴጅክ አመራሮች የማዕረግ እድገት ሰጠ።

በሥነ ስርአቱ ላይ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አቶ ደመቀ መኮንን ተገኝተዋል።የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በህዝብና በሀገር የተሰጠውን ሙያዊና ሀገራዊ ግደታን በየእለቱ መስዋዕትነት በመክፈል እየሠራ መሆኑን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመለሽ ገ/ሚካኤል ገልጸዋል።

በማዕረግ አሰጣጡ ከኮማንደር ወደ ረዳት ኮሚሽነርነት ማዕረግ 43፣ ከረዳት ኮሚሽነር ወደ ምክትል ኮሚሽነር 12 አመራሮች፤ በድምሩ 55 አመራሮች የማዕረግ ዕድገት እንዳገኙም አስታውቀዋል።አመራሮቹ ባላቸው ከፍተኛ የትምህርት ዝግጅት፣ በያዙት ማዕረግ ከአራት ዓመት በላይ የቆዩ፣ በመምሪያ ኃላፊነትና ከዚያ በላይ የኃላፊነት ደረጃ ያላቸው፣ በተግባር ተፈትነው ባስመዘገቡት የሥራ አፈፃፀም ብቃት እንዲሁም በሠራዊቱ ዘንድ ባላቸው መልካም ፖሊሳዊ ስብዕና አርአያነት መመዘኛዎችን ያለፉ መሆናቸውን ገልጸዋል።

የእለቱ የክብር እንግዳ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ክቡር አቶ ደመቀ መኮንን ለከፍተኛ የፖሊስ መኮንኖች ማዕረግ ሰጥተው ባስተላለፉት የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክትና የስራ መመሪያ የተሰጣችሁን ሀገራዊና ሙያዊ ግዴታ በመወጣት በመላ ሀገሪቱ ተሰማርተው የህግ የበላይነት እንዲረጋገጥ በከፍተኛ መስዋዕትነት ላስመዘገቡት ከፍተኛ ድል በመብቃታችሁና ለዚህ ታላቅ ክብር ስለደረሳችሁ እንኳን ደስ አላችሁ፤ ኢትዮጵያም ደስ ብሏታል ብለዋል፡፡

@Esat_tv1
@Esat_tv1
43.5K views11:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-03 11:28:03
የሚኒስትሮች ምክር ቤት የ2015 የፌዴራል መንግስት ረቂቅ በጀት 786 ነጥብ 61 ቢሊየን ብር እንዲሆን ውሳኔ አሳለፈ

ከ2014 በጀት ዓመት በጀት ጋር ሲነጻጸር የብር 111.94 ቢሊዮን ወይም የ16.59 በመቶ እድገት አሳይቷል፡፡

የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 9ኛ መደበኛ ስብሰባ በ2015 የፌዴራል መንግስት ረቂቅ በጀት ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል፡፡

@Esat_tv1
@Esat_tv1
44.5K viewsedited  08:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-03 11:28:00
ETHIO FITNESS & NUTRITION (EFN ) አዳማ

በአጭር ጊዜ የሰውነታችንን ጡንቻ በፍጥነት ለማሳደግ ፣ የተስተካከለ አቋም ለማግኘት እና የሰውነት ክብደት መጨመሪያ እና መቀነሻ ፕሮቲን ፓውደር።

PLATINUM MASS ( 1KG)
WHEY CORE ( 908G)
MONOHYDRATE CRATINE ( 300G)
WHEY CORE ( 2.27KG)

Adress : አዳማ ፖስታ ቤት ሶሬቲ ህንፃ ፊትለፊት ጀርመን ሲቲ ሞል 1ኛ ፎቅ ሱቅ ቁጥር 110

Call +251966113766 ወይም በነፃ ስልክ መስመር ወደ ጥሪ ማእከላችን ይደውሉልን 9369

Inbox @ETHIO_FITNESS_NUTRITION

Join https://t.me/+UsMPjkAqaNVxN4Sl
43.6K views08:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-03 11:27:34
የስራ ማግኛ ኦንላይን ፕላትፎርም /ሊንኮችህ/ ዝርዝር ለማግኘት

Join our telegram

https://t.me/+x8RIy5m4HlxiNGRk
42.8K views08:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-02 16:29:21
በደሴ ከተማ ህገወጥ የትምባሆ ምርት ተያዘ

የደሴ ከተማ ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ እና የደሴ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ከብሄራዊ ትምባሆ ድርጅት ጋር በመተባበር በኮንትሮባንድ ንግድ የገቡና የተለያዩ ህገወጥ የትምባሆ ምርቶችን በቁጥጥር ስር አውሏል፡፡

በደሴ ከተማ ሸርፍተራ ፣መናሀሪያ ፣ቧንቧውሃና ተቋም አካባቢዎች ሱቅ ላይ ህጋዊ አስመስለው በመሸጥ ላይ እያሉ በተደረገው ኦፕሬሽን ስራ ከ311 ካርቶን እስቴካ በላይ ህግወጥ የተለያዩ የሲጋራ ምርቶች ተይዟዋል፡፡

የተያዘው ህገወጥ የሲጋራ ምርት በአዋጅ ለብሄራዊ ትምባሆ ድርጅት የትምባሆ ምርቶችን እንዲመራ በተሰጠዉ ስልጣን መሰረት የትምባሆ ድርጅት ያስቀመጠውና ህጋዊነት በመተላለፍ በህገወጥ መንገድ ለህ/ሰቡ ሲሸጡ የተያዙ ሲሆን ኮንትሮባንድ በማስገባት በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ የሆነ ኪሳራ የሚያስከትል ነው።

የተያዘው ህገወጥ የሲጋራ ምርት በገንዘብ ከ155,500 ብር በላይ የሚገመት ሲሆን ህገወጥ ተግባሮችን ማህበረሰቡ ለፀጥታ አካላት ጥቆማ በመስጠት በሰው ህይወትና በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ ኪሰራ የሚያስከትል የኮንትሮባንድ እንቅስቃሴን በጋራ የመከላከል ስራ እንዲሰራ የደሴ ከተማ ፖሊስ መምሪያ አሳስቧል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1
37.4K views13:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ