Get Mystery Box with random crypto!

EOTC TV

የቴሌግራም ቻናል አርማ eotctvchannel — EOTC TV E
የቴሌግራም ቻናል አርማ eotctvchannel — EOTC TV
የሰርጥ አድራሻ: @eotctvchannel
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 33.58K

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 9

2023-04-10 22:14:15

4.8K viewsEOTC TV, 19:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-10 22:13:48

4.0K viewsEOTC TV, 19:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-08 18:33:52
7.2K viewsEOTC TV, 15:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-08 18:33:40 ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ ወደቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌም ለሚጓዙ የምእመናን መተሰቢያ ድርጅት አባላት ጸሎትና ቡራኬ አስተላለፉ።
++++++++++++++++++++++++++++++++
ቅዱስነታቸው ጸሎተ ቡራኬውን የሰጡት መጋቢት 30 ቀን 2015 ዓ/ም በመንበረ ፓትርያርክ ጽርሐ ተዋሕዶ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ለተገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መታሰቢያ ድርጅት አባላት ሲሆን ወደ ቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌም ለሚጓዙ ተሰላሚ ምእመናን ወምእመናት ነው።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምእመናን መታሰቢያ ድርጅት ለኢየሩሳሌም የቦርድ ጽሕፈት ቤት ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ፣ ፓትርያርክ ባቀረበው የመልካም ምኞት መልእክት የምእመናን መታሰቢያ ድርጅቱ ያከናወናቸውን መንፈሳዊ የሥራ ተግባራት፣በቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌም ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ገዳማት በዘንድሮው 2015 ዓ/ም የሚያበረክተውን ከሰባት መቶ ኪሎ ግራም በላይ የምግብ ቁሳቁስ ፣ለገዳማቱ መብት የሚያከናውነውን የጥብቅና ሥራ እና ወዘተ ያከናወናቸውን የሥራ ተግባራት አብራርቷል።
ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ ለተሳላሚ ምእመናን ባስተላለፉት አባታዊ መልእክት የምእመናን መታሰቢያ ድርጅቱ በቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌም ለሚገኙ ገዳማት ብዙ አገልግሎት የሰጠ ሲሆን ለወደፊቱም ብዙ የሚጠበቅበት ድርጅት ነው ብለዋል።
በመጨረሻም ቅዱስነታቸው ለተሰበሰበው ተሳላሚ ምእመናን ጉዟችሁ የተባረከ ይሁን በማለት ጸሎትና ቡራኬ ሰጥተው አሰናብተዋል።
መጋቤ ምስጢር ሣህሉ አድማሱ
6.7K viewsEOTC TV, 15:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-07 22:59:20
1.7K viewsEOTC TV, 19:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-07 22:58:30 የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት (EOTC TV) ለመቄዶንያ አረጋውያንና አእምሮ መርጃ ሕሙማን ተቋም 372,000.00 ብር ድጋፍ አደረገ።
በመ/ር አቤል አሰፋ
(EOTC TV//ኢኦተቤ ቴቪ //መጋቢት ፳፱ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም )
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት (EOTC TV) ለመቄዶንያ አረጋውያንና አእምሮ መርጃ ሕሙማን ማኅበር ለሚያስገነባው ሕንጻ የሁለት በርና መስኮት ማሠሪያ ብር 372,000.00 (ሦስት መቶ ሰባ ሁለት ሺህ ብር) በማዕከሉ በመገኘት አስረክቧል።
ድጋፉን የድርጅቱ የበላይ ኃላፊ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ እና ዋና ሥራ አስኪያጁ ሊቀ ማእምራን ፋንታሁን ሙጩ እንዲሁም የድርጅቱ ሠራተኞች ለክብር ዶ/ር ብንያም አስረክበዋል።
የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት (EOTC TV) በምእመናን በጎ አድራጎት ራሱን እያጠናከረ የሚገኝ ድርጅት ነው ያሉት ሊቀ ማእምራን ፋንታሁን ሙጩ ሆኖም ወንጌልን በተግባር ለሚያስተምረው ለዚህ ተቋም ድጋፍ ማድረግ ሃይማኖታዊ ግዴታችን በመሆኑ ከሌለን ላይ ልናካፍል ተገደናል ብለዋል።
መቄዶንያ የአረጋውያን እና የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል በጅምር ላይ ያለውን ህንጻ በማጠናቀቅ ወደ ሥራ እንዲገባ ለማድረግ የ1 ሚልዮን ዶላር ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር በዶንኪ ትዩብ ሲዘጋጅ የድርጅቱ የበላይ ኃላፊ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ በሰጡት መመሪያ የሁለት በርና መስኮት ማሠሪያ ብር 372,000.00 (ሦስት መቶ ሰባ ሁለት ሺህ ብር) ቃል የተገባ መሆኑን ያስታወሱት ዋና ሥራ አስኪያጁ ; ድጋፉን ለማስረከብ በማዕከሉ ተገኝተው በመጎብኘታቸው የተሰማቸውን ደስታ ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት (EOTC TV) የበላይ ኃላፊ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ ለአረጋውያኑና ለአእምሮ ሕሙማኑ የማጽናኛ ትምህርት አስተምረዋል። ብፁዕነታቸው ተቀባይ ሳይሆን ሰጪ መስጠት በመቻሉ ሊያመሰግን ይገባል ብለዋል በትምሕርታቸው ። ሜቄዶንያ መሥራች ልጃችን ብንያም እንደ ቅዱስ እስጢፋኖስና ቅዱስ ጴጥሮስ ሐዋርያዊ የአንድነት ኑሮን በመመስረት ተቋሙን ለዚህ አብቅቷል ይህንን ማስቀጠል የእያንዳንዱ ዜጋ ኃላፊነት ነው ብለዋል ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ ። ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻቸውን በማስተባበር ተጨማሪ የገንዘብ እርዳታ ለማድረግ ቃል የገቡ ሲሆን። አገልጋይ ካህናት በማዕከሉ በመገኘት መንፈሳዊ አገልግሎት እንዲሰጡም ጥሪ አቅርበዋል።

መቄዶንያ የአረጋውያን እና የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል ሃይማኖታዊ እና ሰብአዊ አገልግሎቱን እንዲያስተዋውቅ በሣምንት 1 ቀን ነጻ የ 30 ደቂቃ የአየር ሰዓት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት (EOTC TV) ተሰጥቶታል።
የክብር ዶ/ር ቢንያም በዕለቱ ለኢኦተቤ ቴቪ ምስጋና አቅበዋል። መቄዶንያ የሚያስገነባው ተቋም ከ2.3 ቢልዮን ብር በላይ የሚፈጀ G+12 ዘመናዊ ሆስፒታልና የአረጋውያን መኖሪያ ህንጻ በተጀመረ በ4 ውስጥ ግንባታው 70% መጠናቀቁ በመግጽ።
ከ7,500 በላይ አረጋውያንና የአዕምሮ ህሙማንን በውስጡ በመያዝ አገልግሎት እየሰጠ የሚገኘው ማዕከሉ በቀጣይ 20 ሺህ ለማድረስ የታቀደ መሆኑን ገልጸዋል። ማዕከሉ በቀን አንድ ሚልዮን ብር ወጪ እንዳለው የተጠቆሙት የክብር ዶ/ር ቢንያም ሁሉም ኢትዮጵያዊ በመሳተፍ የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ ጠይቀዋል።

EOTC TV
+++++++++++++++++++++++++++++++++++++



"የቤተክርስቲያን የሆነውን ብቻ"
የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት
የዲጂታል ሚዲያ ገጾች
ለመረጃ +251985585858
➽ የዩቲዮብ ገጻችን
http://www.youtube.com/c/eotctv
➽ የፌስ ቡክ ገጻችንን
https://www.facebook.com/eotctvchannel
➽የቴሌግራም ገጻችን
https://t.me/eotctvchannel
➽ የቲክ ቶክ ገጻችን
https://vm.tiktok.com/ZMFSxXdUf/
➽ የዩቲዮብ ገጻችን Eotc tv 2



➽የትዊተር ገጻችን
https://twitter.com/EotcT/
➽የኢንስታግራም ገጻችን
https://www.instagram.com/p/CknRF0MtB77/?igshid=MDJmNzVkMjY=
1.7K viewsEOTC TV, 19:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-06 12:33:38 በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ለሕዝብና መንግሥታዊ የሚዲያ ተቋማት ከመንበረ ፓትርያርክ እስከ አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ድረስ የዘገባ ፈቃድ ተሰጠ።
በመ/ር አቤል አሰፋ
(EOTC TV//ኢኦተቤ ቴቪ //መጋቢት ፳፰ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም )
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ተከስቶ ከነበረው ችግር ጋር ተያይዞ ሚዛናዊ የሚዲያ ሽፋን ባልሰጡ የሕዝብና መንግሥታዊ የብዙኃን መገናኛ ተቋማት ላይ ከቤተክርስቲያኗ ከምእመናንና ከኢትዮጵያ ሚዲያ ካውንስል ቅሬታ ሲቀርብ ቆይቷል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞ ቤተክርስቲያኗ አብረዋት ከሚሠሩ የብዙኃን መገናኛዎች ጋር ባደረገችው ስምምነት ለተወሰኑ የብዙኃን መገናኛዎች ፈቃድ መስጠቷ የሚታወቅ ነው።
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ መጋቢት ፳፰ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ምበጻፈው ደብዳቤ ለኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ለዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ለሁሉም ክልላዊ መንግሥታት የሚዲያ ተቋማት የዘገባ ፈቃድ ሰጥቷል።

ግንኙነት መምሪያ በደብዳቤው ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ቤተክርስቲያናችን የገጠሟትን ችግሮች አስመልክቶ ቤተከተርስቲያናችን በምትፈልገው መንገድ የደረሱባትን ችግሮች የሚገልጹ ዘገባዎች ባለመሠራታቸው ክፍተቶች መፈጠሩን ገልጿል።

መምሪያው ቤተከተርስቲያኗ የሀገር ባለውለታ መሆኗን በመግለጽ የብዙኃን መገናኛ ተቋማት የፈጠሩት የሚዛናዊና ፍትሐዊ የሚዲያ ሽፋን ክፍተት መሞላት እዳለበት ቤተክርስቲያን በጽኑእ ታምናለች ብሏል፡፡ ለሕዝብና መንግሥታዊ የሚዲያ ተቋማት በቤተክርስቲያኗ የሚደረጉ መንፈሳዊና ማኀበራዊ አገልግሎቶችን ከመንበረ ፓትርያርክ እስከ አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ድረስ ያለምንም መሸራረፍ የቤተክርስቲያናችን ዶግማና ቀኖና እዲሁም ሕግጋት በማክበር ዘገባዎችንና ፕሮግራሞችን መሥራት እንዲችሉ የተፈቀደላቸው መሆኑነን አስታውቋል።

EOTC TV
+++++++++++++++++++++++++++++++++++++



"የቤተክርስቲያን የሆነውን ብቻ"
የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት
የዲጂታል ሚዲያ ገጾች
ለመረጃ +251985585858
➽ የዩቲዮብ ገጻችን
http://www.youtube.com/c/eotctv
➽ የፌስ ቡክ ገጻችንን
https://www.facebook.com/eotctvchannel
➽የቴሌግራም ገጻችን
https://t.me/eotctvchannel
➽ የቲክ ቶክ ገጻችን
https://vm.tiktok.com/ZMFSxXdUf/
➽ የዩቲዮብ ገጻችን Eotc tv 2



➽የትዊተር ገጻችን
https://twitter.com/EotcT/
➽የኢንስታግራም ገጻችን
https://www.instagram.com/p/CknRF0MtB77/?igshid=MDJmNzVkMjY=
1.3K viewsEOTC TV, 09:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-05 00:12:25

4.3K viewsEOTC TV, 21:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-05 00:12:06

4.3K viewsEOTC TV, 21:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-03 20:59:26
4.5K viewsEOTC TV, 17:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ